TIKVAH-MAGAZINE
#PositivePeaceBuilding ሰማንያ የሚሆኑ ወጣቶች በ16 ቡድን ተከፋፍለው የስዕል ውድድር ለማድረግ ተዘጋጅተዋል። ተወዳዳሪዎቹ አሸናፊ ለመሆን አወንታዊ የሰላም ግንባታ፤ የአብሮነትና የግጭት አፈታት ሚናን በሥዕል አጉልቶ ማሳየትና ማስተዋወቅ ይጠበቅባቸዋል። ለውድድር የሚያበቃቸውን የሥዕል ሥራም የፊታችን ቅዳሜና እሁድ መስከረም 14 እና 15 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ አለ የሥነ ጥበብ…
#የዛሬ (መስከረም 15/2014)
🗓 የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የኤሌክትሮኒክ የግዥ ሥርዓትን (e-GP) ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ገልጾ ከዚህ በፊት በባለስልጣን መ/ቤቱ ድረ-ገጽ ላይ የተመዘገቡ አቅራቢዎች ምዝገባቸው ተቀባይነት የሚኖረው የኤሌክትሮኒክ የግዥ ሥርዓትን (e-GP) መጠቀም ባልጀመሩ ተቋማት ብቻ እስከ ህዳር 30 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ መሆኑን አስገንዝቧል።
📰 ለመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚደረግ የበጀት ድጎማ ከመደበኛው ሥራ ይልቅ ከዋናው ተልዕኮ ውጪ ለሆነ #የፖለቲካ_ሥራ እንደሚውል በፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ያጠናውን ጥናት ዋቢ አድርጎ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ ሰርቶ ነበር። ኮሚሽኑ በበኩሉ ዘገባው ኮሚሽኑ በቅርቡ በትምህርት ዘርፍ ካስጠናው ጥናት ጋር የማይጣጣም ነው ሲል ቢያስተባብልም አድርጌዋለሁ ያለውን ጥናት (ትክክለኛውን ማለት ነው) በይፋ አላሰራጨውም።
🔥 በመስቀል አደባባይ የሚካሄደው የደመራ ፕሮግራምን መጠናቀቅ ተከትሎ በከተማው በተለያዩ ደብሮች እና መንደሮች ደመራ የማብራት ስነ-ስርዓት ይካሄዳል። ይህን ተከትሎ በየአካባቢው ደመራ ሲበራ ህብረተሰቡ ተገቢውን ጥንቃቄ ሊያደረግ እና በማንኛውም ሁኔታ ርችት መተኮስ ፍፁም ክልክል መሆኑ ተልጿል።
🇪🇹 ሀገራችን የምታስተናግደው የሴካፋ ከ 17ዓመት በታች ውድድርን ለመካፋል ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ጀምረዋል። በዛሬው ዕለትም የዩጋንዳ እና ጅቡቲ ብሔራዊ ቡድኖች አዲስ አበባ መግባታቸው ለማወቅ ተችሏል። በውድድሩ የሚሳተፉ #ስምንት ሀገራት ከነገ ጀምሮ የ "MRI" ምርመራን የሚያካሂዱ ይሆናል።
⚽️ የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ የአስራ ስድስተኛው የአዲስ አበባ ዋንጫ አሸናፊ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። መቻልን የገጠሙት ፈረሰኞቹ በሀብቶም ገብረ እግዚአብሔር ብቸኛ ግብ 1ለ0 አሸንፈዋል።
#Update: በታዳጊና ወጣት ሰዓሊያን መካከል አወንታዊ ሰላም ላይ ያተኮረ የስዕል ውድድር https://yangx.top/tikvahethiopia/73901?single
@tikvahethmagazine
🗓 የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን የኤሌክትሮኒክ የግዥ ሥርዓትን (e-GP) ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ገልጾ ከዚህ በፊት በባለስልጣን መ/ቤቱ ድረ-ገጽ ላይ የተመዘገቡ አቅራቢዎች ምዝገባቸው ተቀባይነት የሚኖረው የኤሌክትሮኒክ የግዥ ሥርዓትን (e-GP) መጠቀም ባልጀመሩ ተቋማት ብቻ እስከ ህዳር 30 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ መሆኑን አስገንዝቧል።
📰 ለመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚደረግ የበጀት ድጎማ ከመደበኛው ሥራ ይልቅ ከዋናው ተልዕኮ ውጪ ለሆነ #የፖለቲካ_ሥራ እንደሚውል በፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ያጠናውን ጥናት ዋቢ አድርጎ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ ሰርቶ ነበር። ኮሚሽኑ በበኩሉ ዘገባው ኮሚሽኑ በቅርቡ በትምህርት ዘርፍ ካስጠናው ጥናት ጋር የማይጣጣም ነው ሲል ቢያስተባብልም አድርጌዋለሁ ያለውን ጥናት (ትክክለኛውን ማለት ነው) በይፋ አላሰራጨውም።
🔥 በመስቀል አደባባይ የሚካሄደው የደመራ ፕሮግራምን መጠናቀቅ ተከትሎ በከተማው በተለያዩ ደብሮች እና መንደሮች ደመራ የማብራት ስነ-ስርዓት ይካሄዳል። ይህን ተከትሎ በየአካባቢው ደመራ ሲበራ ህብረተሰቡ ተገቢውን ጥንቃቄ ሊያደረግ እና በማንኛውም ሁኔታ ርችት መተኮስ ፍፁም ክልክል መሆኑ ተልጿል።
🇪🇹 ሀገራችን የምታስተናግደው የሴካፋ ከ 17ዓመት በታች ውድድርን ለመካፋል ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ጀምረዋል። በዛሬው ዕለትም የዩጋንዳ እና ጅቡቲ ብሔራዊ ቡድኖች አዲስ አበባ መግባታቸው ለማወቅ ተችሏል። በውድድሩ የሚሳተፉ #ስምንት ሀገራት ከነገ ጀምሮ የ "MRI" ምርመራን የሚያካሂዱ ይሆናል።
⚽️ የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ የአስራ ስድስተኛው የአዲስ አበባ ዋንጫ አሸናፊ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። መቻልን የገጠሙት ፈረሰኞቹ በሀብቶም ገብረ እግዚአብሔር ብቸኛ ግብ 1ለ0 አሸንፈዋል።
#Update: በታዳጊና ወጣት ሰዓሊያን መካከል አወንታዊ ሰላም ላይ ያተኮረ የስዕል ውድድር https://yangx.top/tikvahethiopia/73901?single
@tikvahethmagazine
Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA