TIKVAH-MAGAZINE
199K subscribers
18.9K photos
292 videos
70 files
2.48K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

#ኢትዮጵያ

ያግኙን +251913134524
加入频道
#የዛሬ (መስከረም 25/2015)

🕊 የአፍሪካ ኅብረት #የሰላም_ንግግሩን የሚመሩ አካላትን፤ ቀንና ስፍራን አሳውቆ የሰላም ውይይቱ እንዲጀመር ኦፊሴላዊ ጥሪ አቅርቧል። ይህንን አስመልክቶ የፌዴራል መንግስት በደቡብ አፍሪካ ከጥቅምት 18 ጀምሮ የተጠራውን የሰላም ድርድር መቀበሉን በይፋ ሲያሳውቅ ህወሓትም በዚሁ ድርድር ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኑን ዛሬ ምሽት አሳውቋል። ህውሓት ተጨማሪ ተዋናዮች ዝርዝር፣ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ሚና እንዲሁም የሎጅስቲክስ ፤ የጉዞ እና የደህንነት ዝግጅቶችን በተመለከተ ማብራሪያ እኝዲሰጠው ጠይቋል።

💬 "ወላጆች የልጆቻችሁን ጉዳይ በሚመለከት በቀጥታ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር፤ የምንነግራችሁ ቁጥሮች አሉ፣ የምንልካቸው የአካባቢው ትምህርት ተወካዮች አሉ በዛ በኩል መገናኘት ያስፈልጋል። አንድ ነገር ቢፈጠር #በእርግጠኝነት የምንነግራችሁ ፤ ከእኛ ውሸት አትጠብቁ የሆነውን ነገር ይሄ ነው የሆነው ብለን እንነግራችኃለን። ምንም የምንደብቅበት ምክንያት የለም።" ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ (የትምህርት ሚኒስትር) ለብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ከተናገሩት የተወሰደ

🇰🇪 የኬንያ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ የመጀመሪያ የአፍሪካ ሀገር ጉዟቸውን ወደ #ኢትዮጵያ ያደርጋሉ። ፕረዚደንቱ ነገ በአዲስ አበባ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ እንደሚታደሙ የተነገረ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ይመክራሉ ተብሏል።

💐 በአዲስ አበባ ትናንት ምሽት ከሌሊቱ 10:00 አካባቢ ባልታወቀ ምክንያት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 ልዩ ቦታው ወንጌላዊት አካባቢ በተፈጠረ የመሬት መደርመስ በደረሰ የመሬት መደርመስ የሁለት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በሌሎች ሁለት ሰዎች ላይ መጠነኛ ጉዳት በመድረሱ በህክምና እየተረዱ ይገኛሉ ተብሏል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethmagazine