TIKVAH-MAGAZINE
199K subscribers
18.9K photos
292 videos
70 files
2.48K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

#ኢትዮጵያ

ያግኙን +251913134524
加入频道
#የዛሬ (መስከረም 21/2015)

🌳 የሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ ዛሬ በድምቀት ተከብሮ ውሏል። አስተዳደሩ በዓሉ ባህላዊ እሴቱንና ስርዓቱን በጠበቀ መልኩ #በሰላም ተከብሮ መጠናቀቁን ነው ያስታወቀው።

የግሸን ማርያም ዓመታዊ ንግስ በዓል በድምቀት #በሰላም ተከብሯል። በዘንድሮው በዓል 1.5 ሚሊዮን የሚደርስ ሰው መታደሙን የአምባሰል ወረዳ ባህል እና ቱሪዝም ፅህፈት ቤት አሳውቋል።

📣 ዛሬ ከመተሐራ ቤተሰቦች የመጣው መልዕክት ፤ ትላንት ከጠዋቱ መተሐራ አባድር 2ተኛ ካምፕ በሚባል አካባቢ ታጣቂዎች ገብተው #ከ10 በላይ ሰዎችን መገደላቸውን ፤ በዚህም ጥቃት ሳቢያ ደህንነታቸው አደጋ ላይ የወደቀባቸው ሰዎች መኖሪያቸውን ለቀው እንዲወጡ መገደዳቸውን ያመለክታል። የሟቾች ስርዓተ ቀብርም ዛሬ ተፈፅሟል ብለዋል። ከቀናት በፊት በአከባቢው በአጠቃላይ የደህንነት ጉዳይ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ስለመድረሱ በዝርዝር አመልክተው ነበር።

🔴 አማሮ ልዩ ወረዳ ጎልቤ ቀበሌ ልዩ ስሙ "መንደር" በተባለ ቦታ በመስከረም 19/2015 ዓ/ም በአንድ ቤተሰብ አባላት ውስጥ በ6 ሰዎች ላይ አጣዳፊ ተቅማጥና ትኩሳት በሽታ ምልክት መታየቱና ከዚህ ቤተሰብ አባላት ውስጥ አንድ ሰው ወደ ህክምና ማዕከል ሳይወሰድ በመቅረቱ ህይወቱ ማለፉ ተገልጿል። የበሽታው ምንነት #በላብራቶሪ እየተጣራ መሆኑ ተጠቅሷል።

🔺 በጋምቤላ ክልል ከ17 ወራት በኋላ #የጊኒዎርም በሽታ በአንድ ሰው ላይ መገኘቱን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። በሽታው በአቦቦ ወረዳ በእርሻ ኢንቨስትመንት በቀን ሰራተኝነት ስራ  በተሰማራ ግለሰብ ላይ እና  በጎግ በአቦቦ ወረዳ በ3 እንስሳት ላይ መገኘቱን ነው የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ታች ኮንግ ገልጸዋል።

የወልድያ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ም/ቤት ነባራዊ ሁኔታን ታሳቢ በማድረግ ተጨማሪ ክልክለዎችን አስተላልፏል። በዚህም ከነገ መስከረም 22  ቀን ጀምሮ #ጫት ወደ ከተማዋ ማስገባት፣ ጫት መቃም ሆነ ማስቃም በጥብቅ ተከልክሏል። በተጨማሪም የጎዳና ላይ ቁማር (ቢንጎ የመሳሰሉትን) መጫወት ተከልክሏል።

💬 ትላንት አርብ ወደ አዲስ አበባ ከተማ መግባት ሳይችሉ ቀርተው መንገድ ላይ እየተጉላሉ ከነበሩ መገደኞች መካከል የሆኑ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ዛሬ መንገዱ ተከፍቶ #በሰላም አዲስ አበባ መግባታቸውን በፅሁፍ መልዕክት አሳውቀዋል።

📢 የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ተግባራዊ ማድረጉ ይታወቃል። ከዚህ ጋር በተያያዘ፤ የታለመለት የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ የሆኑ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ተሽከርካሪዎች በሚጠቀሙት ነዳጅ ላይ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ #ያልተደረገ በመሆኑ ህብረተሰቡ ይህን አውቆ መንግስት ካስቀመጠው ታሪፍ ውጪ ባለመክፈል ተባባሪ እንዲሆን ጠይቋል።

🇪🇹 በአሰልጣኝ ውበቱ አባተ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለአልጄርያው የቻን አፍሪካ ዋንጫ ተጋጣሚውን አውቋል። በአልጀርስ በተካሄደው የእጣ ማውጣት ስነ-ስርዓት ዋልያዎቹ በምድብ አንድ ከአዘጋጇ ሀገር አልጄርያ ፣ ሞዛምቢክ እና ሊቢያ ጋር ተደልድላለች።

⚽️ የአምናው የሊጉ ሻምፒዮን ቅዱስ ጊዮርጊስ አዲስ አዳጊው ኢትዮጵያ መድህንን በሰፊ የግብ ልዩነት 7 ለ 1 በመርታት አመቱን በድል ጀምረዋል። ድሬዳዋ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ያደረጉት ጨዋታ ሁለት አቻ ተለያይተዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethmagazine