#Bonga 🦟
የካፋ ዞን የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽህፈት ቤት እስካሁን በተገኘው መረጃ ባለፉት አንድ ወር አጋማሽ 213 ሰዎች በከተማ አስተዳደሩ በወባ በሽታ መጠቃታቸውን አስታውቋል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ በሽታውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲያስችል ''ሱምሺልድ'' የተባለ አዲስ የኬሚካል ርጪት ሥራ ለመሥራት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን፤ በአሁን ሰዓትም ኬሚካሉን ቤት ለቤት ዞረው ለሚረጩ አካላት ስልጠና እየተሰጠ እንደሆነ የጽ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሪት መቅደስ ተረፈ ገልጸዋል።
በዚህም 20 ሰዎች ስልጠናውን እየወሰዱ ሲሆን ስልጠናው ሲጠናቀቅ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ የኬሚካል ርጭቱ ሥራ እንደሚጀመር አክለዋል፡፡
የከተማ አስተዳደሩ ነዋሪዎችም የአልጋ አጎበር በአግባቡ መጠቀምና በየአከባቢው ለወባ መራቢያ ምቹ የሆኑ ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን የማፋሰስና የመድፈን ሥራዎችን በትኩረት በመስራት የበሽታውን መከላከል ስራ መደገፍ እንዳለባቸው ጽህፈት ቤቱ አሳስቧል።
@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
የካፋ ዞን የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽህፈት ቤት እስካሁን በተገኘው መረጃ ባለፉት አንድ ወር አጋማሽ 213 ሰዎች በከተማ አስተዳደሩ በወባ በሽታ መጠቃታቸውን አስታውቋል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ በሽታውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲያስችል ''ሱምሺልድ'' የተባለ አዲስ የኬሚካል ርጪት ሥራ ለመሥራት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን፤ በአሁን ሰዓትም ኬሚካሉን ቤት ለቤት ዞረው ለሚረጩ አካላት ስልጠና እየተሰጠ እንደሆነ የጽ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሪት መቅደስ ተረፈ ገልጸዋል።
በዚህም 20 ሰዎች ስልጠናውን እየወሰዱ ሲሆን ስልጠናው ሲጠናቀቅ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ የኬሚካል ርጭቱ ሥራ እንደሚጀመር አክለዋል፡፡
የከተማ አስተዳደሩ ነዋሪዎችም የአልጋ አጎበር በአግባቡ መጠቀምና በየአከባቢው ለወባ መራቢያ ምቹ የሆኑ ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን የማፋሰስና የመድፈን ሥራዎችን በትኩረት በመስራት የበሽታውን መከላከል ስራ መደገፍ እንዳለባቸው ጽህፈት ቤቱ አሳስቧል።
@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
#Bonga 🛬
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ቦንጋ ከተማ ለሚገነባው ቀላል የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ቀዳማዊት እመቤተ ዝናሽ ታያቸው እና የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በተገኙበት የመሰረት ድንጋይ በዛሬው ዕለት ተቀምጧል።
@tikvahethmagazine
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ቦንጋ ከተማ ለሚገነባው ቀላል የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ቀዳማዊት እመቤተ ዝናሽ ታያቸው እና የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በተገኙበት የመሰረት ድንጋይ በዛሬው ዕለት ተቀምጧል።
@tikvahethmagazine