TIKVAH-MAGAZINE
199K subscribers
18.9K photos
292 videos
70 files
2.48K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

#ኢትዮጵያ

ያግኙን +251913134524
加入频道
#AskAAU

በሀገሪቱ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ 75ኛው የአልማዝ እዩቤልዩ በዓሉን ለማክበር ዝግጅት ላይ ይገኛል።

አንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ራስ ገዝ መሆኑን ተከትሎ የተለያዩ ተቋማዊ ሪፎርሞችን በማካሄድ ላይ ነው።

ታዲያ ይህ ልምምድ በሀገራችን የመጀመሪያው ከመሆኑም አንጻር እንዲሁም ተቋማዊ የአሰራር ለውጥ በሚኖርበት ወቅት ብዙ ግልጽ መደረግ ያለባቸው ጉዳዮች መኖራቸው እሙን ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ከዚህ ቀደም ከቤተሰቦቹ ሲቀርቡ በነበሩ ጥያቄዎች መነሻ በማድረግ ዩኒቨርስቲው በእስካሁኑ የራስ ገዝነት ጉዞው ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመሰጠት ፈቃደኝነቱን ገልጾልናል።

በመሆኑም የዩኒቨርስቲው ማኅበረሰብ ሰራተኞች፣ መምህራንና ተማሪዎች እንዲሁም በዚህ ሂደት ላይ ጥያቄና ማብራሪያ የምትፈልጉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች በሙሉ ጥያቄዎቻችሁን እንድታቀርቡ እንጠይቃለን።

ጥያቄዎቻችሁ ተሰብስበው ለዩኒቨርስቲው የበላይ አመራሮች የሚቀርቡና ምላሽ የሚሰጥባቸው ይሆናል።

ጥያቄዎችን ለማቅረብ @tikvahmagbot ይጠቀሙ።

#TikvahFamily🩵

@tikvahethmagazine