#AskAAU
በሀገሪቱ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ 75ኛው የአልማዝ እዩቤልዩ በዓሉን ለማክበር ዝግጅት ላይ ይገኛል።
አንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ራስ ገዝ መሆኑን ተከትሎ የተለያዩ ተቋማዊ ሪፎርሞችን በማካሄድ ላይ ነው።
ታዲያ ይህ ልምምድ በሀገራችን የመጀመሪያው ከመሆኑም አንጻር እንዲሁም ተቋማዊ የአሰራር ለውጥ በሚኖርበት ወቅት ብዙ ግልጽ መደረግ ያለባቸው ጉዳዮች መኖራቸው እሙን ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ከዚህ ቀደም ከቤተሰቦቹ ሲቀርቡ በነበሩ ጥያቄዎች መነሻ በማድረግ ዩኒቨርስቲው በእስካሁኑ የራስ ገዝነት ጉዞው ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመሰጠት ፈቃደኝነቱን ገልጾልናል።
በመሆኑም የዩኒቨርስቲው ማኅበረሰብ ሰራተኞች፣ መምህራንና ተማሪዎች እንዲሁም በዚህ ሂደት ላይ ጥያቄና ማብራሪያ የምትፈልጉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች በሙሉ ጥያቄዎቻችሁን እንድታቀርቡ እንጠይቃለን።
ጥያቄዎቻችሁ ተሰብስበው ለዩኒቨርስቲው የበላይ አመራሮች የሚቀርቡና ምላሽ የሚሰጥባቸው ይሆናል።
ጥያቄዎችን ለማቅረብ @tikvahmagbot ይጠቀሙ።
#TikvahFamily🩵
@tikvahethmagazine
በሀገሪቱ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ 75ኛው የአልማዝ እዩቤልዩ በዓሉን ለማክበር ዝግጅት ላይ ይገኛል።
አንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ራስ ገዝ መሆኑን ተከትሎ የተለያዩ ተቋማዊ ሪፎርሞችን በማካሄድ ላይ ነው።
ታዲያ ይህ ልምምድ በሀገራችን የመጀመሪያው ከመሆኑም አንጻር እንዲሁም ተቋማዊ የአሰራር ለውጥ በሚኖርበት ወቅት ብዙ ግልጽ መደረግ ያለባቸው ጉዳዮች መኖራቸው እሙን ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ከዚህ ቀደም ከቤተሰቦቹ ሲቀርቡ በነበሩ ጥያቄዎች መነሻ በማድረግ ዩኒቨርስቲው በእስካሁኑ የራስ ገዝነት ጉዞው ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመሰጠት ፈቃደኝነቱን ገልጾልናል።
በመሆኑም የዩኒቨርስቲው ማኅበረሰብ ሰራተኞች፣ መምህራንና ተማሪዎች እንዲሁም በዚህ ሂደት ላይ ጥያቄና ማብራሪያ የምትፈልጉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች በሙሉ ጥያቄዎቻችሁን እንድታቀርቡ እንጠይቃለን።
ጥያቄዎቻችሁ ተሰብስበው ለዩኒቨርስቲው የበላይ አመራሮች የሚቀርቡና ምላሽ የሚሰጥባቸው ይሆናል።
ጥያቄዎችን ለማቅረብ @tikvahmagbot ይጠቀሙ።
#TikvahFamily🩵
@tikvahethmagazine