#Assosa 📍
በጫት አጠቃቀም ገደብ ለመጣል እና ተዛማጅ ሱስ አምጭ ንጥረ ነገሮችን ለመከላከል በአሶሳ ከተማ አስ/ር ምክር ቤት ጸድቆ በወጣዉ መመሪያ ቁጥር 6/2013 ላይ ውይይት ተደርጓል።
መድረኩ የአሶሳ ከተማ አስ/ር ምክር ቤት ከተስፋ ብልጭታ በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር የተዘጋጀው ሲሆን የከተማ አስተዳደሩ አቃቤ ህግ መምሪያ ቃቤ ህግ አቶ ገመቹ በመመሪያው ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በመመሪያዉ መሰረትም፡-
#ጫት፡-
- ከት/ቤት 1ኪ/ሜ ርቀት፣ ከጤና ተቋማት 800 ሜትር፣ ከሲቪክ ማህበራትና ተቋማት 600 ሜትር በት/ቤቶችና የመንግስት ተቋማት አካባቢ በማንኛዉም ሁኔታ መሸጥ ክልክል ነዉ፡፡
- ከ21 ዓመት በታች የሆነ ዕድሜ ያለዉ የጫት ንግድ ፍቃድ ማዉጣት፣ ጫት መሸጥ፣ ማሸጥ እንዲገዛ መላክም ሆነ አብሮ መቃም አይቻልም፡፡
- ንግድ ፈቃድ ሰጭ አካል የጫት ንግድ ፈቃድ ሲሰጥ የተቀመጠዉን ርቀትና የእድሜ ገደብ አጣርቶ መሆን አለበት፡፡
- ማንኛዉም የመንግስትም ሆነ የግል ድርጅት ለጫት መሸጫ ማከራየት አይቻልም፡፡
- ማንኛዉም የመንግስት ሰራተኛ በስራ ሰዓት ጫት መቃም አይቻልም፡፡
- ማንኛዉም የጫት ነጋዴ ጫት ወደ ከተማ ሲያስገባ ገረባዉን እዛዉ አስቀርቶ የምትቃመዉን ቅጠል ብቻ መሆን አለበት፡፡
#ሺሻ
- ማንኛዉም ሰዉ በመኖሪያ ቤት፣ በንግድ ተቋማት በማንኛዉም የመንግስትም ሆነ የግል ድርጅት እና የከተማ ክልል ዉስጥ ሽሻና ተዛማጅ ሱስ አምጭ ነገሮች ማጨስም ሆነ ማስጨስ በምንም አይነት ሁኔታ አይፈቀድም፡፡
- ለሽሻና ተዛማጅ ሱሶች የሚያገለግሉ ዕቃዎችን ለሽያች ማቅረብ የተከለከለ ነዉ፡፡
የሚሉና መሰል ክልከላዎችና ገደቦች በመመሪያዉ መካተታቸዉ ተገልጿል ሲል የአሶሳ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል።
@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
በጫት አጠቃቀም ገደብ ለመጣል እና ተዛማጅ ሱስ አምጭ ንጥረ ነገሮችን ለመከላከል በአሶሳ ከተማ አስ/ር ምክር ቤት ጸድቆ በወጣዉ መመሪያ ቁጥር 6/2013 ላይ ውይይት ተደርጓል።
መድረኩ የአሶሳ ከተማ አስ/ር ምክር ቤት ከተስፋ ብልጭታ በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር የተዘጋጀው ሲሆን የከተማ አስተዳደሩ አቃቤ ህግ መምሪያ ቃቤ ህግ አቶ ገመቹ በመመሪያው ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በመመሪያዉ መሰረትም፡-
#ጫት፡-
- ከት/ቤት 1ኪ/ሜ ርቀት፣ ከጤና ተቋማት 800 ሜትር፣ ከሲቪክ ማህበራትና ተቋማት 600 ሜትር በት/ቤቶችና የመንግስት ተቋማት አካባቢ በማንኛዉም ሁኔታ መሸጥ ክልክል ነዉ፡፡
- ከ21 ዓመት በታች የሆነ ዕድሜ ያለዉ የጫት ንግድ ፍቃድ ማዉጣት፣ ጫት መሸጥ፣ ማሸጥ እንዲገዛ መላክም ሆነ አብሮ መቃም አይቻልም፡፡
- ንግድ ፈቃድ ሰጭ አካል የጫት ንግድ ፈቃድ ሲሰጥ የተቀመጠዉን ርቀትና የእድሜ ገደብ አጣርቶ መሆን አለበት፡፡
- ማንኛዉም የመንግስትም ሆነ የግል ድርጅት ለጫት መሸጫ ማከራየት አይቻልም፡፡
- ማንኛዉም የመንግስት ሰራተኛ በስራ ሰዓት ጫት መቃም አይቻልም፡፡
- ማንኛዉም የጫት ነጋዴ ጫት ወደ ከተማ ሲያስገባ ገረባዉን እዛዉ አስቀርቶ የምትቃመዉን ቅጠል ብቻ መሆን አለበት፡፡
#ሺሻ
- ማንኛዉም ሰዉ በመኖሪያ ቤት፣ በንግድ ተቋማት በማንኛዉም የመንግስትም ሆነ የግል ድርጅት እና የከተማ ክልል ዉስጥ ሽሻና ተዛማጅ ሱስ አምጭ ነገሮች ማጨስም ሆነ ማስጨስ በምንም አይነት ሁኔታ አይፈቀድም፡፡
- ለሽሻና ተዛማጅ ሱሶች የሚያገለግሉ ዕቃዎችን ለሽያች ማቅረብ የተከለከለ ነዉ፡፡
የሚሉና መሰል ክልከላዎችና ገደቦች በመመሪያዉ መካተታቸዉ ተገልጿል ሲል የአሶሳ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል።
@tikvahethmagazine @tikvahmagbot