#CholeraUpdate
በጎንደር ከተማ ሰሞኑን በተከሰተው የኮሌራ በሽታ ከ69 በላይ ሰዎች መያዛቸውን የጎንደር ከተማ ጤና መምሪያ ገልጿል፡፡ በከተማዋ የበሽታው ምልክት መታየት የጀመረው ከባለፈው ሐምሌ ወር አጋማሽ ጀምሮ መሆኑን የመምሪያው ኃላፊ በለጠ ፈንቴ ተናግረዋል።
ኃላፊው ከዚህ ቀደም በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ በሚገኘው በርሚል ጊዮርጊስ ገዳም ውስጥ ለጸበል በሄዱ ሰዎች ላይ ድንገተኛ ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ፤ ከጸበሉ ቆይተው ወደ ጎንደር ከተማ በመጡ ሰዎች አማካኝነት ወረርሽኙ መዛመቱን ነው የጠቆሙት።
በጸበል ቦታው በተከሰተ አጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት የአንድ እናት ሕይወት ማለፉን የጠቀሱት ኃላፊው፤ የሟች ቤተሰብ አስከሬኑን ወደ ጎንደር ከተማ ይዘው በመጡበት ወቅት በሽታው መዛመቱን አስረድተዋል።
በጎንደር ከተማ በተከሰተው የኮሌራ በሽታ እስካሁን የሞተ ሰው አለመኖሩን የገለጹት የጤና መምሪያው ኃላፊ፤ ከተያዙት ሰዎች ውስጥ እያገገሙ የሚወጡ ሰዎች ቢኖሩም በምትኩ ተይዘው የሚገቡ መኖራቸውን ተናግረዋል።
"በሽታው ከዚህ በላይ እንዳይስፋፋም ባለሙያዎችን በማዋቀር የመከላከል ሥራ እየተሰራ ነው።" ሲሉም አመላክተዋል።
በቋራ ወረዳ ከወራት በፊት በተከሰተ የኮሌራ በሽታ ከ1 ሺሕ 500 በላይ ሰዎች መያዛቸው እና የኹለት ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተጠቁሟል።
ይህን ተከትሎ በሽታው ወደ ሌሎች ቦታዎች እንዳይስፋፋ በሚል ወደ ቋራ ወረዳ መግባትና መውጣት ተከልክሎ ቢቆይም፤ ከባለፈው ሐምሌ ወር አጋማሽ ጀምሮ የእንቅስቃሴ ገደቡ እንዲነሳ በመደረጉ በሽታው ጎንደር ከተማ እንዲከሰት ምክንያት መሆኑ ነው የተጠቀሰው።
( ምንጭ: አዲስ ማለዳ )
✅️ @TikvahethMagazine
በጎንደር ከተማ ሰሞኑን በተከሰተው የኮሌራ በሽታ ከ69 በላይ ሰዎች መያዛቸውን የጎንደር ከተማ ጤና መምሪያ ገልጿል፡፡ በከተማዋ የበሽታው ምልክት መታየት የጀመረው ከባለፈው ሐምሌ ወር አጋማሽ ጀምሮ መሆኑን የመምሪያው ኃላፊ በለጠ ፈንቴ ተናግረዋል።
ኃላፊው ከዚህ ቀደም በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ በሚገኘው በርሚል ጊዮርጊስ ገዳም ውስጥ ለጸበል በሄዱ ሰዎች ላይ ድንገተኛ ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ፤ ከጸበሉ ቆይተው ወደ ጎንደር ከተማ በመጡ ሰዎች አማካኝነት ወረርሽኙ መዛመቱን ነው የጠቆሙት።
በጸበል ቦታው በተከሰተ አጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት የአንድ እናት ሕይወት ማለፉን የጠቀሱት ኃላፊው፤ የሟች ቤተሰብ አስከሬኑን ወደ ጎንደር ከተማ ይዘው በመጡበት ወቅት በሽታው መዛመቱን አስረድተዋል።
በጎንደር ከተማ በተከሰተው የኮሌራ በሽታ እስካሁን የሞተ ሰው አለመኖሩን የገለጹት የጤና መምሪያው ኃላፊ፤ ከተያዙት ሰዎች ውስጥ እያገገሙ የሚወጡ ሰዎች ቢኖሩም በምትኩ ተይዘው የሚገቡ መኖራቸውን ተናግረዋል።
"በሽታው ከዚህ በላይ እንዳይስፋፋም ባለሙያዎችን በማዋቀር የመከላከል ሥራ እየተሰራ ነው።" ሲሉም አመላክተዋል።
በቋራ ወረዳ ከወራት በፊት በተከሰተ የኮሌራ በሽታ ከ1 ሺሕ 500 በላይ ሰዎች መያዛቸው እና የኹለት ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተጠቁሟል።
ይህን ተከትሎ በሽታው ወደ ሌሎች ቦታዎች እንዳይስፋፋ በሚል ወደ ቋራ ወረዳ መግባትና መውጣት ተከልክሎ ቢቆይም፤ ከባለፈው ሐምሌ ወር አጋማሽ ጀምሮ የእንቅስቃሴ ገደቡ እንዲነሳ በመደረጉ በሽታው ጎንደር ከተማ እንዲከሰት ምክንያት መሆኑ ነው የተጠቀሰው።
( ምንጭ: አዲስ ማለዳ )
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
September 5, 2023
#CholeraUpdate
1️⃣
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከሐምሌ 24 ቀን፣ 2015 ዓ.ም አንስቶ በየኮሌራ ወረርሺኝ ከተከሰተ በኋላ በ3 ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ 9 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የክልሉ ጤና መሥሪያ ቤት አስታውቋል።
የጤና መሥሪያ ቤቱ የመርኃ ግብር ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ አብዱልሙኒየም አልበሽር ወረርሽኙ በከፍተኛ ሁኔታ በታየበት መተከል ዞን #ዳንጉር ወረዳ ውስጥ በሚገኙ የተወሰኑ ቀበሌዎችም በፀጥታ ችግር ምክንያት ማዳረስ አለመቻላቸውን አብራርተዋል።
በተጨማሪም አባይ ዳር የተባለ አንድ ቀበሌ ደግሞ በመንገድ እና ፀጥታ ችግር ሳቢያ ሙሉ በሙሉ የሕክምና ድጋፍ እንዳላገኙ ጠቁመዋል።
2️⃣
በዐማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን ውስጥ በተቋቋመ የኩመር መጠለያ ጣቢያ፣ የኮሌራ ወረርሽኝ እንደተከሠተና ዘጠኝ ሱዳናውያን ስደተኞች እንደሞቱ፣ 395 ሰዎች ደግሞ እንደታመሙ፣ የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር/UNHCR/ አስታውቋል።
3️⃣
በአማራ ክልል በ28 ወረዳዎች በተከሰተ የኮሌራ ወረርሽኝ ከ3ሺህ 8መቶ በላይ ሰዎች መጠቃታቸውን፣ ከ70 በላይ ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉን እንዲሁም በየቀኑ ከ15 እስከ 20 ሰዎች በአዲስ በበሽታው እንደሚጠቁ የክልሉ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር በላይ በዛብህ ተናግረዋል።
በክልሉ ባሕር ዳርና ጎንደር ከተማን ጨምሮ 9 ወረዳዎ፥ ዕድሚያቸው አንድ ዓመትና ከዚያ በላይ ለኾኑ ሰዎች ከመስከረም 5 እስከ መስከረም 10 ድረስ ለ1 ነጥብ 8 ሚሊየን ሰዎች የኮሌራ ክትባት ለመስጠት ታቅዷል ተብሏል።
መረጃው ከዶይቼ ቬሌ፣ ቪኦኤ፣ አሚኮ የተጠናቀረ ነው።
✅️ @TikvahethMagazine
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከሐምሌ 24 ቀን፣ 2015 ዓ.ም አንስቶ በየኮሌራ ወረርሺኝ ከተከሰተ በኋላ በ3 ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ 9 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የክልሉ ጤና መሥሪያ ቤት አስታውቋል።
የጤና መሥሪያ ቤቱ የመርኃ ግብር ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ አብዱልሙኒየም አልበሽር ወረርሽኙ በከፍተኛ ሁኔታ በታየበት መተከል ዞን #ዳንጉር ወረዳ ውስጥ በሚገኙ የተወሰኑ ቀበሌዎችም በፀጥታ ችግር ምክንያት ማዳረስ አለመቻላቸውን አብራርተዋል።
በተጨማሪም አባይ ዳር የተባለ አንድ ቀበሌ ደግሞ በመንገድ እና ፀጥታ ችግር ሳቢያ ሙሉ በሙሉ የሕክምና ድጋፍ እንዳላገኙ ጠቁመዋል።
በዐማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን ውስጥ በተቋቋመ የኩመር መጠለያ ጣቢያ፣ የኮሌራ ወረርሽኝ እንደተከሠተና ዘጠኝ ሱዳናውያን ስደተኞች እንደሞቱ፣ 395 ሰዎች ደግሞ እንደታመሙ፣ የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር/UNHCR/ አስታውቋል።
በአማራ ክልል በ28 ወረዳዎች በተከሰተ የኮሌራ ወረርሽኝ ከ3ሺህ 8መቶ በላይ ሰዎች መጠቃታቸውን፣ ከ70 በላይ ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉን እንዲሁም በየቀኑ ከ15 እስከ 20 ሰዎች በአዲስ በበሽታው እንደሚጠቁ የክልሉ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር በላይ በዛብህ ተናግረዋል።
በክልሉ ባሕር ዳርና ጎንደር ከተማን ጨምሮ 9 ወረዳዎ፥ ዕድሚያቸው አንድ ዓመትና ከዚያ በላይ ለኾኑ ሰዎች ከመስከረም 5 እስከ መስከረም 10 ድረስ ለ1 ነጥብ 8 ሚሊየን ሰዎች የኮሌራ ክትባት ለመስጠት ታቅዷል ተብሏል።
መረጃው ከዶይቼ ቬሌ፣ ቪኦኤ፣ አሚኮ የተጠናቀረ ነው።
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
September 16, 2023
#CholeraUpdate
በኢትዮጵያ የኮሌራ ወረርሽኝ ተባብሷል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (OCHA) ይፋ ባደረገው ሪፖርት ባሳለፍነው ሳምንት በኩመር የስደተኞች መጠለያ ወደ 400 የሚጠጉ ሰዎች በበሽታው መያዛቸውን ገልጿል።
በበሽታው የተያዙት ሰዎች ወደ ኩመር ኮሌራ ህክምና ማዕከል መግባታቸው ሲገለፅ በሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር ካለፈው ሳምንት ጋር ሲነፃፀር 50 በመቶ መጨመሩ ተገልጿል።
ሆስፒታሎች በአካባቢው የኮሌራ ህሙማንን ለማስተናገድ የሚያስችል ሁኔታ ላይ እንዳልሆኑ ሲገልፅ ምግብ እና ንፁህ የመጠጥ ውሃ አለመኖሩ በህብረተሰቡ ውስጥ የኮሌራ ስርጭትን እየጨመረው እንደሆነ ኦቻ አሳውቋል።
በኩመር የኮሌራ ሕክምና ማዕከል ዶክተር የሆኑት አብዱልባሪይ መሐመድ ከአናዶሉ ጋር ባደረጉት ቆይታ አፋጣኝ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ጠቁመው ብዙ ሰዎችን ለማስተናገድ የሚያስችል በቂ የሰው ኃይል ባለመኖሩ ሰዎች በየቀኑ እየሞቱ መሆኑን ተናግረዋል።
ዶ/ር አብዱልባሪይ ሁኔታው የታካሚዎችን ስቃይ እያከፋ እንደሆነ ሲገልፁ የምግብ እና ንጹህ ውሃ እጥረት በጣም አሳሳቢ በመሆኑ አስፈላጊውን የህክምና አገልግሎት ለመስጠት አስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው አስረድተዋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኢትዮጵያ እየተባባሰ የመጣው የኮሌራ ወረርሽኝ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት እየቀጠፈ በመሆኑ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አሳስቧል።
እንደ ዓለም ጤና ድርጅት የቅርብ ጊዜ መረጃ ከሆነ በኢትዮጵያ ውስጥ በሰባት ክልሎች ከ20ሺ በላይ ሰዎች በኮሌራ ሲያዙ 271 ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል።
✅️ @TikvahethMagazine
በኢትዮጵያ የኮሌራ ወረርሽኝ ተባብሷል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (OCHA) ይፋ ባደረገው ሪፖርት ባሳለፍነው ሳምንት በኩመር የስደተኞች መጠለያ ወደ 400 የሚጠጉ ሰዎች በበሽታው መያዛቸውን ገልጿል።
በበሽታው የተያዙት ሰዎች ወደ ኩመር ኮሌራ ህክምና ማዕከል መግባታቸው ሲገለፅ በሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር ካለፈው ሳምንት ጋር ሲነፃፀር 50 በመቶ መጨመሩ ተገልጿል።
ሆስፒታሎች በአካባቢው የኮሌራ ህሙማንን ለማስተናገድ የሚያስችል ሁኔታ ላይ እንዳልሆኑ ሲገልፅ ምግብ እና ንፁህ የመጠጥ ውሃ አለመኖሩ በህብረተሰቡ ውስጥ የኮሌራ ስርጭትን እየጨመረው እንደሆነ ኦቻ አሳውቋል።
በኩመር የኮሌራ ሕክምና ማዕከል ዶክተር የሆኑት አብዱልባሪይ መሐመድ ከአናዶሉ ጋር ባደረጉት ቆይታ አፋጣኝ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ጠቁመው ብዙ ሰዎችን ለማስተናገድ የሚያስችል በቂ የሰው ኃይል ባለመኖሩ ሰዎች በየቀኑ እየሞቱ መሆኑን ተናግረዋል።
ዶ/ር አብዱልባሪይ ሁኔታው የታካሚዎችን ስቃይ እያከፋ እንደሆነ ሲገልፁ የምግብ እና ንጹህ ውሃ እጥረት በጣም አሳሳቢ በመሆኑ አስፈላጊውን የህክምና አገልግሎት ለመስጠት አስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው አስረድተዋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኢትዮጵያ እየተባባሰ የመጣው የኮሌራ ወረርሽኝ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት እየቀጠፈ በመሆኑ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አሳስቧል።
እንደ ዓለም ጤና ድርጅት የቅርብ ጊዜ መረጃ ከሆነ በኢትዮጵያ ውስጥ በሰባት ክልሎች ከ20ሺ በላይ ሰዎች በኮሌራ ሲያዙ 271 ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል።
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
September 22, 2023
#CholeraUpdate
የዓለም ጤና ድርጅት እየተባባሰ የመጣውን የኮሌራ ስርጭት ለመከላከል 16 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ መልቀቁን አስታውቋል።
የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ከዓለም ጤና ድርጅት ድንገተኛ ፈንድ 16 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ መልቀቁን የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በአለም አቀፍ የጤና ጉዳዮች ላይ በመከረ የቨርቹዋል ስብሰባ ገልፀዋል።
ድርጅቱ የበሽታውን ስርጭት ለመግታት አስፈላጊ ድጋፎችን በማቅረብ ከአጋር አካላት ጋር በመስራት ኮሌራን ለመከላከል የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ዶ/ር ቴዎድሮስ ተናግረዋል።
ዶ/ር ቴዎድሮስ የበሽታውን ስርጭት ለመግታት 160 ሚሊዮን ዶላር እንዲለቀቅ ጥረት መደረጉን ጠቅሰው በአሁኑ ወቅት ከ16 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ ከ አለም ጤና ድርጅት የድንገተኛ አደጋ ፈንድ መለቀቁን አሳውቀዋል።
በአሁኑ ወቅት የኮሌራ በሽታ ስርጭት ከፍተኛ ስጋት ከሆነባቸው ሀገራት መሃከል ሃገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ ሄይቲ፣ ኢራቅ እና ሱዳን እንደሚገኙበት ነው የተጠቀሰው።
የዓለም ጤና ድርጅት በቅርብ ጊዜ ባወጣው መረጃ በኢትዮጵያ ውስጥ በሰባት ክልሎች ከ20ሺ በላይ ሰዎች በኮሌራ ሲያዙ 271 ሰዎች መሞታቸውን የተገለፀ ሲሆን ባሳለፍነው ሳምንት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (OCHA) በኢትዮጵያ የኮሌራ በሽታ ስርጭት መጨመሩን መግለፁም ይታወሳል።
✅️ @TikvahethMagazine
የዓለም ጤና ድርጅት እየተባባሰ የመጣውን የኮሌራ ስርጭት ለመከላከል 16 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ መልቀቁን አስታውቋል።
የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ከዓለም ጤና ድርጅት ድንገተኛ ፈንድ 16 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ መልቀቁን የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በአለም አቀፍ የጤና ጉዳዮች ላይ በመከረ የቨርቹዋል ስብሰባ ገልፀዋል።
ድርጅቱ የበሽታውን ስርጭት ለመግታት አስፈላጊ ድጋፎችን በማቅረብ ከአጋር አካላት ጋር በመስራት ኮሌራን ለመከላከል የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ዶ/ር ቴዎድሮስ ተናግረዋል።
ዶ/ር ቴዎድሮስ የበሽታውን ስርጭት ለመግታት 160 ሚሊዮን ዶላር እንዲለቀቅ ጥረት መደረጉን ጠቅሰው በአሁኑ ወቅት ከ16 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ ከ አለም ጤና ድርጅት የድንገተኛ አደጋ ፈንድ መለቀቁን አሳውቀዋል።
በአሁኑ ወቅት የኮሌራ በሽታ ስርጭት ከፍተኛ ስጋት ከሆነባቸው ሀገራት መሃከል ሃገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ ሄይቲ፣ ኢራቅ እና ሱዳን እንደሚገኙበት ነው የተጠቀሰው።
የዓለም ጤና ድርጅት በቅርብ ጊዜ ባወጣው መረጃ በኢትዮጵያ ውስጥ በሰባት ክልሎች ከ20ሺ በላይ ሰዎች በኮሌራ ሲያዙ 271 ሰዎች መሞታቸውን የተገለፀ ሲሆን ባሳለፍነው ሳምንት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (OCHA) በኢትዮጵያ የኮሌራ በሽታ ስርጭት መጨመሩን መግለፁም ይታወሳል።
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
September 29, 2023
TIKVAH-MAGAZINE
#CholeraUpdate 🇪🇹 በኢትዮጵያ በተከሰተው የኮሌራ ወረርሽኝ እስካሁን የ156 ሰዎችን ህይወት ቀጥፏል ሲል የመንግስታቱ ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት (UNOCHA) ሰሞኑን ባወጣው መረጃ አስታውቋል። በአሁኑ ወቅት የተከሰተው የኮሌራ ወረርሽኝ በምስራቅ አፍሪካ ሀገር ከተከሰቱት ረጅሙ አንዱ ነውም ተብሏል። የወረርሽኙ አጠቃላይ የገዳይነት መጠንም 1.36 በመቶ ሲሆን በዓለም አቀፍ…
#CholeraUpdate
በኢትዮጵያ በተከሰተው የኮሌራ ወረርሽኝ እስከ መስከረም 22 ባለው መረጃ 300 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል። በሐምሌ 5 በተመዘገበው መረጃ የሟቾች ቁጥር 172 ነበር።
የኮሌራ ተጠቂዎች ቁጥር ሐምሌ ወር ላይ ከነበረው 13,118 ጨምሮ አሁን ላይ 24,197 ሆኖ ተመዝግቧል።
በአንጻሩ የወረርሽኙ አጠቃላይ የገዳይነት መጠን (Case Fatality Rate) ሐምሌ ወር ላይ ከነበረው 1.36 በመቶ ወደ 1.24 ዝቅ ብሏል። ሆኖም ይህ ቁጥር በዓለም አቀፍ ደረጃ ስምምነት ከተደረሰበት የ 1 በመቶ መጠን ከፍ ያለ ነው።
አብዛኛዎቹ የኮሌራ ተጠቂዎች ሪፖርት የሚደረገው ከኦሮሚያ (33%) ሲሆን ከአማራ (19%)፣ ከሲዳማ (13%)፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ(12%)፣ ከድሬዳዋ (9%)፣ ከአፋር (7%)፣ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ (4%)፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝ (3%) እና ሀረሪ (1%) ቀጣዮችቹን ደረጃዎች በቅደም ተከተል ይይዛሉ።
እስካሁን ከ6 ሚሊዮን በላይ ሰዎች አንድ ዙር በአፍ የሚወሰድ የኮሌራ ክትባት መከተብ የቻሉ ሲሆን ይህም በሶማሌ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ፤ ሲዳማ፣ ኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች ባሉ 54 ወረዳዎች የተሰራጨ ነው።
የጸጥታ ገደቦች ቢኖሩም በአማራ ክልል በኩመር መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ 8,098 ስደተኞችን ጨምሮ ወደ 2 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ክትባት ወስደዋል ተብሏል።
በተጨማሪም ለአፋር፣ ለሲዳማ፣ ለደቡብ ኢትዮጵያ እና ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ተጨማሪ 1.5 ሚሊዮን ዶዝ ክትባት መፈቀዱም ተጠቅሷል።
[ በዚህ ዙሪያ በተከታታይ የተሰሩ ዜናዎችን ለማግኘት 👉 #CholeraUpdate ይጠቀሙ። ]
👋 @TikvahethMagazine
በኢትዮጵያ በተከሰተው የኮሌራ ወረርሽኝ እስከ መስከረም 22 ባለው መረጃ 300 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል። በሐምሌ 5 በተመዘገበው መረጃ የሟቾች ቁጥር 172 ነበር።
የኮሌራ ተጠቂዎች ቁጥር ሐምሌ ወር ላይ ከነበረው 13,118 ጨምሮ አሁን ላይ 24,197 ሆኖ ተመዝግቧል።
በአንጻሩ የወረርሽኙ አጠቃላይ የገዳይነት መጠን (Case Fatality Rate) ሐምሌ ወር ላይ ከነበረው 1.36 በመቶ ወደ 1.24 ዝቅ ብሏል። ሆኖም ይህ ቁጥር በዓለም አቀፍ ደረጃ ስምምነት ከተደረሰበት የ 1 በመቶ መጠን ከፍ ያለ ነው።
አብዛኛዎቹ የኮሌራ ተጠቂዎች ሪፖርት የሚደረገው ከኦሮሚያ (33%) ሲሆን ከአማራ (19%)፣ ከሲዳማ (13%)፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ(12%)፣ ከድሬዳዋ (9%)፣ ከአፋር (7%)፣ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ (4%)፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝ (3%) እና ሀረሪ (1%) ቀጣዮችቹን ደረጃዎች በቅደም ተከተል ይይዛሉ።
እስካሁን ከ6 ሚሊዮን በላይ ሰዎች አንድ ዙር በአፍ የሚወሰድ የኮሌራ ክትባት መከተብ የቻሉ ሲሆን ይህም በሶማሌ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ፤ ሲዳማ፣ ኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች ባሉ 54 ወረዳዎች የተሰራጨ ነው።
የጸጥታ ገደቦች ቢኖሩም በአማራ ክልል በኩመር መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ 8,098 ስደተኞችን ጨምሮ ወደ 2 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ክትባት ወስደዋል ተብሏል።
በተጨማሪም ለአፋር፣ ለሲዳማ፣ ለደቡብ ኢትዮጵያ እና ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ተጨማሪ 1.5 ሚሊዮን ዶዝ ክትባት መፈቀዱም ተጠቅሷል።
[ በዚህ ዙሪያ በተከታታይ የተሰሩ ዜናዎችን ለማግኘት 👉 #CholeraUpdate ይጠቀሙ። ]
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
October 7, 2023
TIKVAH-MAGAZINE
#CholeraUpdate በኢትዮጵያ በተከሰተው የኮሌራ ወረርሽኝ እስከ መስከረም 22 ባለው መረጃ 300 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል። በሐምሌ 5 በተመዘገበው መረጃ የሟቾች ቁጥር 172 ነበር። የኮሌራ ተጠቂዎች ቁጥር ሐምሌ ወር ላይ ከነበረው 13,118 ጨምሮ አሁን ላይ 24,197 ሆኖ ተመዝግቧል። በአንጻሩ የወረርሽኙ አጠቃላይ የገዳይነት መጠን (Case Fatality…
#CholeraUpdate
በአዲስ አበባ አንድ አንድ ቦታዎች የኮሌራ በሽታ መከሰቱን "ካፒታል" ስማቸዉ እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ምንጮቼ ያላቸውን በጤና ላይ የሚሰሩ መግንስታዊ ያለሆኑ ተቋማት (NGO) አረጋግጠዋል ሲል ዘግቧል።
ይህን አስመልክቶ "ካፒታል" ያናገራቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ምክትል የቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉጌታ እንዳለ "መረጃዉ ሀሰተኛ ነዉ" ወደ ከተማዋ እንዳይገባ አሁን ላይ እየሰራን" እንገኛለን ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
[ በዚህ ዙሪያ በተከታታይ የተሰሩ ዜናዎችን ለማግኘት 👉 #CholeraUpdate ይጠቀሙ። ]
👋 @TikvahethMagazine
በአዲስ አበባ አንድ አንድ ቦታዎች የኮሌራ በሽታ መከሰቱን "ካፒታል" ስማቸዉ እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ምንጮቼ ያላቸውን በጤና ላይ የሚሰሩ መግንስታዊ ያለሆኑ ተቋማት (NGO) አረጋግጠዋል ሲል ዘግቧል።
ይህን አስመልክቶ "ካፒታል" ያናገራቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ምክትል የቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉጌታ እንዳለ "መረጃዉ ሀሰተኛ ነዉ" ወደ ከተማዋ እንዳይገባ አሁን ላይ እየሰራን" እንገኛለን ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
[ በዚህ ዙሪያ በተከታታይ የተሰሩ ዜናዎችን ለማግኘት 👉 #CholeraUpdate ይጠቀሙ። ]
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
November 8, 2023
TIKVAH-MAGAZINE
#CholeraUpdate በአዲስ አበባ አንድ አንድ ቦታዎች የኮሌራ በሽታ መከሰቱን "ካፒታል" ስማቸዉ እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ምንጮቼ ያላቸውን በጤና ላይ የሚሰሩ መግንስታዊ ያለሆኑ ተቋማት (NGO) አረጋግጠዋል ሲል ዘግቧል። ይህን አስመልክቶ "ካፒታል" ያናገራቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ምክትል የቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉጌታ እንዳለ "መረጃዉ ሀሰተኛ ነዉ" ወደ ከተማዋ እንዳይገባ አሁን ላይ…
#CholeraUpdate
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከ 393 ሺ ለሚልቁ የህብረተሰብ ክፍሎች የኮሌራ በሽታ መከላከያ ክትባት ተደራሽ ለማድረግ ማቀዱን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታውቋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ማሙሽ ሁሴን በሽታው በ19 ወረዳዎች ላይ ተከስቶ የነበረ መሆኑን ጠቅሰው በየደረጃው በተደረገው ከፍተኛ ርብርብ 17 ወረዳዎችን ከወረርሽኙ ነፃ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል።
በአሁኑ ሰዓት በክልሉ 2 ወረዳዎች ላይ በሽታውን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር ከፍተኛ ጥረት በመደረግ ላይ መሆኑን ያነሱት ዳይሬክተሩ በአፍ የሚሰጠው የኮሌራ በሽታ መከላከያ ክትባት( OCV) ለ393,463 ያህል የህብረተሰብ ክፍሎች ለመስጠት መታቀዱን አስረድተዋል።
አክለውም፥ ዕድሜያቸው ከአንድ ዓመት በታች ከሆኑ ህጻናት በስተቀር ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የክትባቱ ተጠቃሚ መሆን እንደሚገባቸው ያሳሰቡ ሲሆን በክልሉ የክትባት ዘመቻውን ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አንስተዋል።
[ በዚህ ዙሪያ በተከታታይ የተሰሩ ዜናዎችን ለማግኘት 👉 #CholeraUpdate ይጠቀሙ። ]
👋 @TikvahethMagazine
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከ 393 ሺ ለሚልቁ የህብረተሰብ ክፍሎች የኮሌራ በሽታ መከላከያ ክትባት ተደራሽ ለማድረግ ማቀዱን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታውቋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ማሙሽ ሁሴን በሽታው በ19 ወረዳዎች ላይ ተከስቶ የነበረ መሆኑን ጠቅሰው በየደረጃው በተደረገው ከፍተኛ ርብርብ 17 ወረዳዎችን ከወረርሽኙ ነፃ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል።
በአሁኑ ሰዓት በክልሉ 2 ወረዳዎች ላይ በሽታውን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር ከፍተኛ ጥረት በመደረግ ላይ መሆኑን ያነሱት ዳይሬክተሩ በአፍ የሚሰጠው የኮሌራ በሽታ መከላከያ ክትባት( OCV) ለ393,463 ያህል የህብረተሰብ ክፍሎች ለመስጠት መታቀዱን አስረድተዋል።
አክለውም፥ ዕድሜያቸው ከአንድ ዓመት በታች ከሆኑ ህጻናት በስተቀር ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የክትባቱ ተጠቃሚ መሆን እንደሚገባቸው ያሳሰቡ ሲሆን በክልሉ የክትባት ዘመቻውን ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አንስተዋል።
[ በዚህ ዙሪያ በተከታታይ የተሰሩ ዜናዎችን ለማግኘት 👉 #CholeraUpdate ይጠቀሙ። ]
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
November 8, 2023
#CholeraUpdate: የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ የኮሌራ ወረርሽኝን ለመከላከል 1 ሚሊዮን ዩሮ እንደሚሰጥ አስታወቀ።
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ የሰዎችን ህይወት እየቀጠፈ ላለው የኮሌራ ወረርሽኝ ቀጣይነት ያለው ሰብዓዊ ምላሽ ለመስጠት አንድ ሚሊዮን ዩሮ አዲስ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚሰጥ አስታውቋል።
የአውሮፓ ህብረት ገንዘቡን የሚሰጠው ከድንገተኛ አደጋ ጊዜ መጠባበቂያ ፈንድ እንደሆነ ሲጠቀስ በህብረቱ የሰብአዊ መርሃ ግብር አካል ተደርጎ በሀገሪቱ በበሽታው በተጎዱ አካባቢዎችና በሀገሪቱ ውስጥ ለሚገኙ ተጋላጭ ማህበረሰቦች የሚውል እንደሆነ ተገልጿል።
የኮሌራ ወረርሽኝ በሀገሪቱ በግጭትና ከአየር ንብረት ጋር በተያያዘ ምክንያት ከፍተኛ የሰብአዊ ፍላጎት ባለባቸው አካባቢዎች እርዳታ መድረስ እንዳልቻለ ህብረቱ ሲጠቁም በ 2023 በኢትዮጵያ በግጭትና በድርቅ የተጎዱ ሰዎችን ለመደገፍ 82.5 ሚሊዮን ዩሮ ለኢትዮጵያ መስጠቱን የአውሮፓ ህብረት አስታውሷል።
በቅርቡ የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (OCHA) ባወጣው መረጃ ፥ በኢትዮጵያ ከጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በአፋር፣ በአማራ፣ በቤኒሻንጉል ጉምዝ፣ በመካከለኛው ኢትዮጵያ ክልል (CER) ፣ በሐረሪ፣ በሲዳማ፣ በሶማሌ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል (SER) በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም በ85 ወረዳዎች ከ24,700 በላይ ሰዎች የኮሌራ በሽታ እንደተገኘባቸው ተመዝግቧል።
👋 @TikvahethMagazine
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ የሰዎችን ህይወት እየቀጠፈ ላለው የኮሌራ ወረርሽኝ ቀጣይነት ያለው ሰብዓዊ ምላሽ ለመስጠት አንድ ሚሊዮን ዩሮ አዲስ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚሰጥ አስታውቋል።
የአውሮፓ ህብረት ገንዘቡን የሚሰጠው ከድንገተኛ አደጋ ጊዜ መጠባበቂያ ፈንድ እንደሆነ ሲጠቀስ በህብረቱ የሰብአዊ መርሃ ግብር አካል ተደርጎ በሀገሪቱ በበሽታው በተጎዱ አካባቢዎችና በሀገሪቱ ውስጥ ለሚገኙ ተጋላጭ ማህበረሰቦች የሚውል እንደሆነ ተገልጿል።
የኮሌራ ወረርሽኝ በሀገሪቱ በግጭትና ከአየር ንብረት ጋር በተያያዘ ምክንያት ከፍተኛ የሰብአዊ ፍላጎት ባለባቸው አካባቢዎች እርዳታ መድረስ እንዳልቻለ ህብረቱ ሲጠቁም በ 2023 በኢትዮጵያ በግጭትና በድርቅ የተጎዱ ሰዎችን ለመደገፍ 82.5 ሚሊዮን ዩሮ ለኢትዮጵያ መስጠቱን የአውሮፓ ህብረት አስታውሷል።
በቅርቡ የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (OCHA) ባወጣው መረጃ ፥ በኢትዮጵያ ከጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በአፋር፣ በአማራ፣ በቤኒሻንጉል ጉምዝ፣ በመካከለኛው ኢትዮጵያ ክልል (CER) ፣ በሐረሪ፣ በሲዳማ፣ በሶማሌ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል (SER) በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም በ85 ወረዳዎች ከ24,700 በላይ ሰዎች የኮሌራ በሽታ እንደተገኘባቸው ተመዝግቧል።
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
November 15, 2023
#CholeraUpdate
ኢትዮጵያን ጨምሮ 16 አገራት ዜጎቻችው በኮሌራ በሽታ እየተያዙ ባሉበት ሰዓት የአለም አቀፍ የጤና ተቋማት የኮሌራ ክትባት ክምችት ማለቁ ተሰምቷል።
የአለም አቀፍ የጤና ተቋማት ያከማቹት የኮሌራ በሽታ መጠባበቂያ ክትባት በኮሌራ ወረርሽኝ ለተጠቁ አገራት በመሰራጨቱ ምክንያት ከወዲሁ የክትባት ክምችቱ ማለቁን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጤና ኤጀንሲ እና የዓለም ጤና ድርጅት የኮሌራ ቡድን መሪ የሆኑት ፊሊፕ ባርባዛ አስታውቀዋል።
በዚህም በተያዘው አመት በኮሌራ የተጠቁ አገራት በሚፈልጉት የክትባት መጠን እና ባለው የአቅርቦት አቅም መካከል በሚፈጠር ክፍትት በትንሹ 50 ሚሊዮን የክትባት መጠን እጥረት እንደሚኖር ተጠቁሟል።
ኤምኤስኤፍ የተሰኘው ሰብአዊ አለም አቀፍ የህክምና ድርጅት አለም አቀፍ የጤና ተቋማት የሚያሰራጩት የኮሌራ ክትባት መሟጠጡ አሳሳቢ መሆኑን የገለፀ ሲሆን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሀገራት በበሽታው የተያዙ ስዎችን ሪፖርት እያደረጉ በመሆኑ፣ በርካታ ነባር እና አዳዲስ የኮሌራ ክትባት አምራቾች አስቸኳይ የአለም አቀፍ የክትባት አቅርቦትን ለማሳደግ ማገዝ አለባቸው ሲል አሳስቧል።
የኤምኤስኤፍ አለም አቀፍ የህክምና አስተባባሪ የሆኑት ዶ/ር ዳንኤላ ጋሮኔ በዓለም ዙሪያ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌን ጨምሮ 16 አገራት የኮሌራ ወረርሽኝ ሪፖርት እያደረጉ መሆናቸውን የገለፁ ሲሆን በዚህ ጊዜ የክትባቱ ክምችት መሟጠጥ አሳሳቢ እና አስጊ መሆኑን በመናገር አምራቾች የኮሌራ ክትባቶችን በአስቸኳይ ማምረት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
@TikvahethMagazine
ኢትዮጵያን ጨምሮ 16 አገራት ዜጎቻችው በኮሌራ በሽታ እየተያዙ ባሉበት ሰዓት የአለም አቀፍ የጤና ተቋማት የኮሌራ ክትባት ክምችት ማለቁ ተሰምቷል።
የአለም አቀፍ የጤና ተቋማት ያከማቹት የኮሌራ በሽታ መጠባበቂያ ክትባት በኮሌራ ወረርሽኝ ለተጠቁ አገራት በመሰራጨቱ ምክንያት ከወዲሁ የክትባት ክምችቱ ማለቁን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጤና ኤጀንሲ እና የዓለም ጤና ድርጅት የኮሌራ ቡድን መሪ የሆኑት ፊሊፕ ባርባዛ አስታውቀዋል።
በዚህም በተያዘው አመት በኮሌራ የተጠቁ አገራት በሚፈልጉት የክትባት መጠን እና ባለው የአቅርቦት አቅም መካከል በሚፈጠር ክፍትት በትንሹ 50 ሚሊዮን የክትባት መጠን እጥረት እንደሚኖር ተጠቁሟል።
ኤምኤስኤፍ የተሰኘው ሰብአዊ አለም አቀፍ የህክምና ድርጅት አለም አቀፍ የጤና ተቋማት የሚያሰራጩት የኮሌራ ክትባት መሟጠጡ አሳሳቢ መሆኑን የገለፀ ሲሆን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሀገራት በበሽታው የተያዙ ስዎችን ሪፖርት እያደረጉ በመሆኑ፣ በርካታ ነባር እና አዳዲስ የኮሌራ ክትባት አምራቾች አስቸኳይ የአለም አቀፍ የክትባት አቅርቦትን ለማሳደግ ማገዝ አለባቸው ሲል አሳስቧል።
የኤምኤስኤፍ አለም አቀፍ የህክምና አስተባባሪ የሆኑት ዶ/ር ዳንኤላ ጋሮኔ በዓለም ዙሪያ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌን ጨምሮ 16 አገራት የኮሌራ ወረርሽኝ ሪፖርት እያደረጉ መሆናቸውን የገለፁ ሲሆን በዚህ ጊዜ የክትባቱ ክምችት መሟጠጥ አሳሳቢ እና አስጊ መሆኑን በመናገር አምራቾች የኮሌራ ክትባቶችን በአስቸኳይ ማምረት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
@TikvahethMagazine
February 27, 2024
#CholeraUpdate
በኢትዮጵያ ባለፈው ወር ከአፍሪካ ሀገራት ከፍተኛ የኮሌራ ታማሚዎች ቁጥር እንደተመዘገበ ተነገረ
በአፍሪካ ባለፈው መጋቢት ወር በኮሌራ በሽታ ከተያዙ 14,441 አዲስ የኮሌራ ታማሚዎች መሃከል ከአህጉሪቱ ከፍተኛ ታማሚዎች የተመዘገቡባት ኢትዮጵያ መሆኗን የአለም ጤና ድርጅት ሪፖርት አመልክቷል።
በተጠቀሰው ወር በኢትዮጵያ 4009 ሰዎች በኮሌራ መያዛቸው ተነግሯል። በኮሌራ ከተያዙት ሰዎች ውስጥም 24 ሰዎች መሞታቸው ተጠቁሟል። በኢትዮጵያ ባለፉት 3 ወራት 9,429 ሰዎች በኮሌራ ተይዘው 111 ሰዎች መሞታቸውንም ሪፖርቱ አመልክቷል።
በአፍሪካ ከጃንዋሪ 1 ቀን 2023 እስከ ማርች 31 ቀን 2024 በጠቅላላው በ18 ሀገራት 271,119 ሰዎች በኮሌራ በሽታ ሲያዙ በተጠቀሰው ጊዜ በኢትዮጵያ 39,892 ሰዎች በበሽታው ተይዘው 524 ሰዎች መሞታቸውም ነው የተገለፀው።
@TikvahethMagazine
በኢትዮጵያ ባለፈው ወር ከአፍሪካ ሀገራት ከፍተኛ የኮሌራ ታማሚዎች ቁጥር እንደተመዘገበ ተነገረ
በአፍሪካ ባለፈው መጋቢት ወር በኮሌራ በሽታ ከተያዙ 14,441 አዲስ የኮሌራ ታማሚዎች መሃከል ከአህጉሪቱ ከፍተኛ ታማሚዎች የተመዘገቡባት ኢትዮጵያ መሆኗን የአለም ጤና ድርጅት ሪፖርት አመልክቷል።
በተጠቀሰው ወር በኢትዮጵያ 4009 ሰዎች በኮሌራ መያዛቸው ተነግሯል። በኮሌራ ከተያዙት ሰዎች ውስጥም 24 ሰዎች መሞታቸው ተጠቁሟል። በኢትዮጵያ ባለፉት 3 ወራት 9,429 ሰዎች በኮሌራ ተይዘው 111 ሰዎች መሞታቸውንም ሪፖርቱ አመልክቷል።
በአፍሪካ ከጃንዋሪ 1 ቀን 2023 እስከ ማርች 31 ቀን 2024 በጠቅላላው በ18 ሀገራት 271,119 ሰዎች በኮሌራ በሽታ ሲያዙ በተጠቀሰው ጊዜ በኢትዮጵያ 39,892 ሰዎች በበሽታው ተይዘው 524 ሰዎች መሞታቸውም ነው የተገለፀው።
@TikvahethMagazine
April 30, 2024
#CholeraUpdate 🇪🇹
ኢትዮጵያ በሐምሌ ወር ብቻ (በፈረንጆቹ) 2,086 የሚሆኑ ሰዎች በኮሌራ መያዛቸውንና እንዲሁም በበሽታው ሳቢያ ህይወታቸው ያለፈ 43 ሰዎች መኖራቸውን ሪፖርት ተደርጓል። የሞት ምጣኔውም 2.1% ሆኖ ተመዝግቧል።
ከባለፈው ወር ጋር ሲነጻጸር በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር 26 በመቶ ጭማሪ ያሳየ ሲሆን የሟቾች ቁጥርም በ 258 በመቶ ከፍ ብሏል።
በኢትዮጵያ ከታኅሣሥ መጨረሻ ጀምሮ እስከ ሐምሌ 21፣ 2016 ዓ.ም ድረስ በድምሩ 21,254 ሰዎች በኮሌራ መያዛቸው የተገለጸ ሲሆን፥ 182 ሰዎች ደግሞ ህይወታቸው አልፏል። በዚህ በ7 ወር ውስጥ ያለው የሞት ምጣኔም (CFR) 0.9 በመቶ መሆኑ ተጠቅሷል።
#አፍሪካ
ከታኅሣሥ መጨረሻ ጀምሮ እስከ ሐምሌ 21፣ 2016 ዓ.ም ድረስ የኮሌራ በሽታ በ14 የአፍሪካ ሀገራት ሪፖርት የተደረገ ሲሆን በድምሩ 111,168 የኮሌራ ተጠቂዎች ተመዝግበዋል።
በዚህ ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ሪፖርት የተደረገባት ሀገር ኢትዮጵያ (21,254 ኬዝ) መሆኗ ተገልጿል። ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) 20 659፤ እንዲሁም ዛምቢያ 20,219 ኬዞችን በማስመዝገብ ይከተላሉ።
በተመሳሳይ ጊዜ በአጠቃላይ 1,899 ሰዎች ከ12 የአፍሪካ ሀገራት በኮሌራ በሽታ የሞቱ ሲሆን በዛምቢያ ከፍተኛው ቁጥር ተመዝግቧል (637 ሞት)፣ ዚምባብዌ (399 ሞት)፣ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (274 ሞት) ተመዝግቧል።
በአንጻሩ ባለፈው ሐምሌ ወር ብቻ (በፈረንጆቹ) በአፍሪካ 7,241 ሰዎች በበሽታው መያዛቸውን ከ7 ሀገራት ሪፖርት የተደረገ ሲሆን ይህ ቁጥር ካለፈው ወር ጋር ሲነጻጸር የ9 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል።
ሆኖም በተጠቀሰው ጊዜ የሟቾች ቁጥር 162 ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን ይህም ካለፈው ወር ጋር ሲነጻጸር በ76 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። ከፍተኛው የሟቾች ቁጥር የተመዘገበው በናይጄሪያ (102) ሲሆን ኢትዮጵያ 43 ሰዎችን በበሽታው በማጣት ተከታይ ነች።
Source : WHO
@tikvahethmagazine
ኢትዮጵያ በሐምሌ ወር ብቻ (በፈረንጆቹ) 2,086 የሚሆኑ ሰዎች በኮሌራ መያዛቸውንና እንዲሁም በበሽታው ሳቢያ ህይወታቸው ያለፈ 43 ሰዎች መኖራቸውን ሪፖርት ተደርጓል። የሞት ምጣኔውም 2.1% ሆኖ ተመዝግቧል።
ከባለፈው ወር ጋር ሲነጻጸር በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር 26 በመቶ ጭማሪ ያሳየ ሲሆን የሟቾች ቁጥርም በ 258 በመቶ ከፍ ብሏል።
በኢትዮጵያ ከታኅሣሥ መጨረሻ ጀምሮ እስከ ሐምሌ 21፣ 2016 ዓ.ም ድረስ በድምሩ 21,254 ሰዎች በኮሌራ መያዛቸው የተገለጸ ሲሆን፥ 182 ሰዎች ደግሞ ህይወታቸው አልፏል። በዚህ በ7 ወር ውስጥ ያለው የሞት ምጣኔም (CFR) 0.9 በመቶ መሆኑ ተጠቅሷል።
#አፍሪካ
ከታኅሣሥ መጨረሻ ጀምሮ እስከ ሐምሌ 21፣ 2016 ዓ.ም ድረስ የኮሌራ በሽታ በ14 የአፍሪካ ሀገራት ሪፖርት የተደረገ ሲሆን በድምሩ 111,168 የኮሌራ ተጠቂዎች ተመዝግበዋል።
በዚህ ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ሪፖርት የተደረገባት ሀገር ኢትዮጵያ (21,254 ኬዝ) መሆኗ ተገልጿል። ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) 20 659፤ እንዲሁም ዛምቢያ 20,219 ኬዞችን በማስመዝገብ ይከተላሉ።
በተመሳሳይ ጊዜ በአጠቃላይ 1,899 ሰዎች ከ12 የአፍሪካ ሀገራት በኮሌራ በሽታ የሞቱ ሲሆን በዛምቢያ ከፍተኛው ቁጥር ተመዝግቧል (637 ሞት)፣ ዚምባብዌ (399 ሞት)፣ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (274 ሞት) ተመዝግቧል።
በአንጻሩ ባለፈው ሐምሌ ወር ብቻ (በፈረንጆቹ) በአፍሪካ 7,241 ሰዎች በበሽታው መያዛቸውን ከ7 ሀገራት ሪፖርት የተደረገ ሲሆን ይህ ቁጥር ካለፈው ወር ጋር ሲነጻጸር የ9 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል።
ሆኖም በተጠቀሰው ጊዜ የሟቾች ቁጥር 162 ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን ይህም ካለፈው ወር ጋር ሲነጻጸር በ76 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። ከፍተኛው የሟቾች ቁጥር የተመዘገበው በናይጄሪያ (102) ሲሆን ኢትዮጵያ 43 ሰዎችን በበሽታው በማጣት ተከታይ ነች።
Source : WHO
@tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
August 15, 2024
#CholeraUpdate
° " የኮሌራ ወረርሽኝ በአጭር ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ በመሠራጨት ላይ ነው " - የወልዲያ ከተማ ጤና መምርያ
° በወረርሽኙ የአንድ ሰው ሕይወት ሲያልፍ 85 ሰዎች ታመዋል፡፡
በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በወልዲያ ከተማ በተከሰተው የኮሌራ ወረርሽኝ፣ እስከ ማክሰኞ መስከረም 7 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ የአንድ ሰው ሕይወት ሲያልፍ፣ በወረርሽኙ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 85 መድረሱ ተገለጸ፡፡
ወረርሽኙ ጳጉሜን 4 ቀን 2016 ዓ.ም. በእቴጌ ጣይቱ ብጡል ክፍለ ከተማ አድማስ ባሻገር ተክለ ሃይማኖት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መከሰቱን፣ የወልዲያ ከተማ ጤና መምርያ ሜዲካል ኦፊሰር ሲስተር ዘሬ በቀለ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
የሁለት ሰዎችን ናሙና ወደ ደሴ ሆስፒታል ላቦራቶሪ በመላክ ወረርሽኙ መከሰቱ ተረጋግጧል ያሉት ሲስተር ዘሬ፣ ሁለቱ ሰዎች በበሽታው ተጠቅተው እንደነበር አክለዋል፡፡
ወረርሽኙ በፍጥነት በመዛመቱ 85 ሰዎች ታመው በሦስት ጤና ተቋማት ሕክምና እየተደረገላቸው ሲሆን ከታማሚዎቹ መካከል 11 ያህሉ በፅኑ መታከሚያ ከፍተኛ ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ሲስተር ዘሬ አክለዋል፡፡
በሕክምና መስጫዎች የመድኃኒት፣ የአልጋና የብርድ ልብስ እጥረት እንዳለ የተናገሩት ሲስተር ዘሬ፣ በሚመለከተው አካል ርብርብ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
@tikvahethmagazine
° " የኮሌራ ወረርሽኝ በአጭር ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ በመሠራጨት ላይ ነው " - የወልዲያ ከተማ ጤና መምርያ
° በወረርሽኙ የአንድ ሰው ሕይወት ሲያልፍ 85 ሰዎች ታመዋል፡፡
በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በወልዲያ ከተማ በተከሰተው የኮሌራ ወረርሽኝ፣ እስከ ማክሰኞ መስከረም 7 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ የአንድ ሰው ሕይወት ሲያልፍ፣ በወረርሽኙ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 85 መድረሱ ተገለጸ፡፡
ወረርሽኙ ጳጉሜን 4 ቀን 2016 ዓ.ም. በእቴጌ ጣይቱ ብጡል ክፍለ ከተማ አድማስ ባሻገር ተክለ ሃይማኖት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መከሰቱን፣ የወልዲያ ከተማ ጤና መምርያ ሜዲካል ኦፊሰር ሲስተር ዘሬ በቀለ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
የሁለት ሰዎችን ናሙና ወደ ደሴ ሆስፒታል ላቦራቶሪ በመላክ ወረርሽኙ መከሰቱ ተረጋግጧል ያሉት ሲስተር ዘሬ፣ ሁለቱ ሰዎች በበሽታው ተጠቅተው እንደነበር አክለዋል፡፡
ወረርሽኙ በፍጥነት በመዛመቱ 85 ሰዎች ታመው በሦስት ጤና ተቋማት ሕክምና እየተደረገላቸው ሲሆን ከታማሚዎቹ መካከል 11 ያህሉ በፅኑ መታከሚያ ከፍተኛ ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ሲስተር ዘሬ አክለዋል፡፡
በሕክምና መስጫዎች የመድኃኒት፣ የአልጋና የብርድ ልብስ እጥረት እንዳለ የተናገሩት ሲስተር ዘሬ፣ በሚመለከተው አካል ርብርብ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
@tikvahethmagazine
September 18, 2024
#CholeraUpdate
° ኢትዮጵያን ጨምሮ ሀገራት የአፍ ኮሌራ ክትባቶችን ጥያቄ ቢያቀርቡም ያለው ክምችት ማለቁን የአለም ጤና ድርጅት አስታውቋል።
የዓለም ጤና ድርጅት ከጥቅምት አራት ወዲህ በአለም አቀፍ ደረጃ በአፍ የሚወሰድ የኮሌራ ክትባት ክምችት ማለቁን እና ምንም ቀሪ ክትባቶች አለመኖራቸውን አስታውቋል።
የተባበሩት መንግስታት የጤና ኤጀንሲ በበኩሉ በወርሃዊ ሪፖርቱ እንዳሰፈረው ዓለም አቀፍ የክትባት ምርት ላይ በሙሉ አቅም እየተሰራ ቢሆንም ፍላጎቱ ከአቅርቦት በላይ እየሆነ ነው ብሏል።
እንደ ድርጅቱ መረጃ ከ ሐምሌ 26 እስከ ጥቅምት 4 ባለው ጊዜ ውስጥ የአለም አቀፍ የክትባት አቅርቦት አስተባባሪ ቡድን ከባንግላዲሽ፣ ሱዳን፣ ኒጀር፣ ኢትዮጵያ እና ምያንማር የአፍ ኮሌራ ክትባቶችን ጥያቄ ተቀብሏል።
ጥያቄዎቹ በድምሩ 8.4 ሚሊዮን ዶዝዎች ሲሆኑ ነገር ግን በክትባቶቹ እጥረት ምክንያት መላክ የተቻለው 7.6 ሚሊዮን ዶዝ ብቻ ነው።
የአለም ጤና ድርጅት "በመጪዎቹ ሳምንታት ውስጥ ተጨማሪ ክትባቶች ቢጠበቁም ይህ እጥረት ወረርሽኙን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ላይ ከፍተኛ ተግዳሮቶችን ከመፍጠሩ በተጨማሪም የበሽታውን ስርጭት ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት ያደናቅፋል" ብሏል።
እየተገባደደ በሚገኘው በፈረንጆቹ 2024 መስከረም 29 ድረስ ብቻ በአለም 439,724 የኮሌራ ተጠቂዎች የተመዘገቡ ሲሆን 3,432 ሰዎች ደግሞ በወረርሽኙ ሳቢያ ህይወታቸው አልፏል
እ.ኤ.አ. በ 2024 የተያዙት ሰዎች ቁጥር ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ16 በመቶ ያነሰ ቢሆንም በማቾች በኩል ግን የ 126 በመቶ ጭማሪ አለው።
በመስከረም ወር ብቻ ከ14 ሀገራት 47,234 አዳዲስ የኮሌራ ተማሚዎች ተመዝግበዋል።
@tikvahethmagazine
° ኢትዮጵያን ጨምሮ ሀገራት የአፍ ኮሌራ ክትባቶችን ጥያቄ ቢያቀርቡም ያለው ክምችት ማለቁን የአለም ጤና ድርጅት አስታውቋል።
የዓለም ጤና ድርጅት ከጥቅምት አራት ወዲህ በአለም አቀፍ ደረጃ በአፍ የሚወሰድ የኮሌራ ክትባት ክምችት ማለቁን እና ምንም ቀሪ ክትባቶች አለመኖራቸውን አስታውቋል።
የተባበሩት መንግስታት የጤና ኤጀንሲ በበኩሉ በወርሃዊ ሪፖርቱ እንዳሰፈረው ዓለም አቀፍ የክትባት ምርት ላይ በሙሉ አቅም እየተሰራ ቢሆንም ፍላጎቱ ከአቅርቦት በላይ እየሆነ ነው ብሏል።
እንደ ድርጅቱ መረጃ ከ ሐምሌ 26 እስከ ጥቅምት 4 ባለው ጊዜ ውስጥ የአለም አቀፍ የክትባት አቅርቦት አስተባባሪ ቡድን ከባንግላዲሽ፣ ሱዳን፣ ኒጀር፣ ኢትዮጵያ እና ምያንማር የአፍ ኮሌራ ክትባቶችን ጥያቄ ተቀብሏል።
ጥያቄዎቹ በድምሩ 8.4 ሚሊዮን ዶዝዎች ሲሆኑ ነገር ግን በክትባቶቹ እጥረት ምክንያት መላክ የተቻለው 7.6 ሚሊዮን ዶዝ ብቻ ነው።
የአለም ጤና ድርጅት "በመጪዎቹ ሳምንታት ውስጥ ተጨማሪ ክትባቶች ቢጠበቁም ይህ እጥረት ወረርሽኙን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ላይ ከፍተኛ ተግዳሮቶችን ከመፍጠሩ በተጨማሪም የበሽታውን ስርጭት ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት ያደናቅፋል" ብሏል።
እየተገባደደ በሚገኘው በፈረንጆቹ 2024 መስከረም 29 ድረስ ብቻ በአለም 439,724 የኮሌራ ተጠቂዎች የተመዘገቡ ሲሆን 3,432 ሰዎች ደግሞ በወረርሽኙ ሳቢያ ህይወታቸው አልፏል
እ.ኤ.አ. በ 2024 የተያዙት ሰዎች ቁጥር ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ16 በመቶ ያነሰ ቢሆንም በማቾች በኩል ግን የ 126 በመቶ ጭማሪ አለው።
በመስከረም ወር ብቻ ከ14 ሀገራት 47,234 አዳዲስ የኮሌራ ተማሚዎች ተመዝግበዋል።
@tikvahethmagazine
October 19, 2024
#CholeraUpdate
° በአማራ ክልል ባለፉት 8 ወራት 66 ሰዎች በኮሌራ በሽታ መሞታቸው ተገለጸ።
በአማራ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች ቀደም ብሎ ተከስቶ የነበረው የኮሌራ በሽታ ሥርጭቱ የመቀነስ አዝማማያ ቢያሳይም አሁንም በክልሉ በአንዳንድ አካባቢዎች በቀን እስከ 4 ሰዎች በበሽታው ስለመያዛቸው ሪፖርት እየተደረገ መሆኑ ተነግሯል።
በክልሉ ከመጋቢት 27/2016 ዓም እስከ ጥቅምት 11/2017 ዓም ባለው ጊዜ ውስጥ 4,396 ሰዎች በኮሌራ ተይዘው 66 ሰዎች ለሞት መዳረጋቸውን በአማራ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የበሽታዎች እና የጤና ሁኔታዎች ምላሽ አሰጣጥ ባለሞያ የሆኑት ሲ/ር ሰፊ ደርብ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ስርጭቱ አሁን በመጠኑም ቢሆን መቀነሱን ያነሱት ባለሞያዋ ምዕራብ ጎንደር ላይ ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ፣ሰሜን ወሎ ሃሩ ወረዳ እና ደቡብ ጎንደር ላይ ደራ አካባቢ እስካሁን በበሽታው የተጠቁ ሰዎችን ሪፖርት ማድረግ ቀጥለዋል ብለዋል።
ከዚህ ቀደም ሪፖርት አድርገው የነበሩት ጎንደር ከተማ፣ ማዕከላዊ ጎንደር ዞን፣ ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን፣ ምዕራብ ጎንደር ፣ ደቡብ ጎንደር ፣ሰሜን ጎጃም እና ወልዲያ ከተማ ከፍተኛ ሥርጭት የነበረባቸው ቢሆንም አሁን ስርጭቱን መቀነስ ተችሏል ብለዋል።
በመስከረም ወር ለአስር ቀን በተደረገ የክትባት ዘመቻም በጎንደር ከተማ እና ምዕራብ በለሳ እድሜያቸው ከአንድ ዓመት በላይ ለሆኑ 293,405 ሰዎች ክትባት መከተብ መቻሉን አክለዋል።
በክትባት ዘመቻው ምዕራብ በለሳ 100 በመቶ ጎንደር ከተማ ደግሞ 86 በመቶ መሸፈን ተችሏል ተብሏል።
ሥርጭቱን ከመከላከል አኳያ ተግዳሮት ስለሆነ ጉዳዮች ጥያቄ ያቀረብንላቸው ባለሞያዋ የጸጥታ ችግር አንዱ ተግዳሮት መሆኑን ጠቁመዋል።
"ለኮሌራ አጋላጭ የሆኑ የስጋት ቦታዎች በዝተዋል በተለይም የቀን ሠራተኛ በሚበዛባቸው አካባቢዎች ማለትም ማዕከላዊ ጎንደር፣ ወልቃይት ጠገዴ (ሰቲት ሁመራ) እና ምዕራብ ጎንደር ሰፋፊ የእርሻ ቦታዎች ስላሉ እዛ የሚሄድ የቀን ሰራተኛ በሚሊዮን የሚቆጠር ነው ነገር ግን በዛ በቂ የሆነ ውሃ ንጽህናው የተጠበቀ ምግብ ባለመኖሩ ወረርሽኙ እየተከሰተ ነበር" ብለዋል።
የኮሌራ በሽታ ሪፖርት በሚደረግባቸው አካባቢዎች የክትባት ዘመቻው ለምን አልቀጠለም ስንል ላቀረብንላችው ጥያቄም ባለሞያዋ ሲመልሱም :-
"ክትባቱ እኛ ስለፈለግን የምናገኘው አይደለም ይህንን የሚያቀርብ አለም አቀፍ ተቋም አለ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በድንገተኛ (Emergency) ጠይቆ ነው የሚያመጣው ብዙ ጊዜ ክትባቱ ውድ በመሆኑና በእርዳታም የሚመጣ በመሆኑ እኛ ስለፈለግን ብቻ መከተብ አንችልም" ብለዋል።
ነገር ግን አሁንም ክትባት የሚያስፈልጋቸው አካባቢዎች መኖራቸውን ያነሱት ባለሞያዋ ክትባቱ በመጣ ጊዜ ለመስጠት ዝግጁ ነን ሲሉ አክለዋል።
@tikvahethmagazine
° በአማራ ክልል ባለፉት 8 ወራት 66 ሰዎች በኮሌራ በሽታ መሞታቸው ተገለጸ።
በአማራ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች ቀደም ብሎ ተከስቶ የነበረው የኮሌራ በሽታ ሥርጭቱ የመቀነስ አዝማማያ ቢያሳይም አሁንም በክልሉ በአንዳንድ አካባቢዎች በቀን እስከ 4 ሰዎች በበሽታው ስለመያዛቸው ሪፖርት እየተደረገ መሆኑ ተነግሯል።
በክልሉ ከመጋቢት 27/2016 ዓም እስከ ጥቅምት 11/2017 ዓም ባለው ጊዜ ውስጥ 4,396 ሰዎች በኮሌራ ተይዘው 66 ሰዎች ለሞት መዳረጋቸውን በአማራ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የበሽታዎች እና የጤና ሁኔታዎች ምላሽ አሰጣጥ ባለሞያ የሆኑት ሲ/ር ሰፊ ደርብ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ስርጭቱ አሁን በመጠኑም ቢሆን መቀነሱን ያነሱት ባለሞያዋ ምዕራብ ጎንደር ላይ ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ፣ሰሜን ወሎ ሃሩ ወረዳ እና ደቡብ ጎንደር ላይ ደራ አካባቢ እስካሁን በበሽታው የተጠቁ ሰዎችን ሪፖርት ማድረግ ቀጥለዋል ብለዋል።
ከዚህ ቀደም ሪፖርት አድርገው የነበሩት ጎንደር ከተማ፣ ማዕከላዊ ጎንደር ዞን፣ ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን፣ ምዕራብ ጎንደር ፣ ደቡብ ጎንደር ፣ሰሜን ጎጃም እና ወልዲያ ከተማ ከፍተኛ ሥርጭት የነበረባቸው ቢሆንም አሁን ስርጭቱን መቀነስ ተችሏል ብለዋል።
በመስከረም ወር ለአስር ቀን በተደረገ የክትባት ዘመቻም በጎንደር ከተማ እና ምዕራብ በለሳ እድሜያቸው ከአንድ ዓመት በላይ ለሆኑ 293,405 ሰዎች ክትባት መከተብ መቻሉን አክለዋል።
በክትባት ዘመቻው ምዕራብ በለሳ 100 በመቶ ጎንደር ከተማ ደግሞ 86 በመቶ መሸፈን ተችሏል ተብሏል።
ሥርጭቱን ከመከላከል አኳያ ተግዳሮት ስለሆነ ጉዳዮች ጥያቄ ያቀረብንላቸው ባለሞያዋ የጸጥታ ችግር አንዱ ተግዳሮት መሆኑን ጠቁመዋል።
"ለኮሌራ አጋላጭ የሆኑ የስጋት ቦታዎች በዝተዋል በተለይም የቀን ሠራተኛ በሚበዛባቸው አካባቢዎች ማለትም ማዕከላዊ ጎንደር፣ ወልቃይት ጠገዴ (ሰቲት ሁመራ) እና ምዕራብ ጎንደር ሰፋፊ የእርሻ ቦታዎች ስላሉ እዛ የሚሄድ የቀን ሰራተኛ በሚሊዮን የሚቆጠር ነው ነገር ግን በዛ በቂ የሆነ ውሃ ንጽህናው የተጠበቀ ምግብ ባለመኖሩ ወረርሽኙ እየተከሰተ ነበር" ብለዋል።
የኮሌራ በሽታ ሪፖርት በሚደረግባቸው አካባቢዎች የክትባት ዘመቻው ለምን አልቀጠለም ስንል ላቀረብንላችው ጥያቄም ባለሞያዋ ሲመልሱም :-
"ክትባቱ እኛ ስለፈለግን የምናገኘው አይደለም ይህንን የሚያቀርብ አለም አቀፍ ተቋም አለ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በድንገተኛ (Emergency) ጠይቆ ነው የሚያመጣው ብዙ ጊዜ ክትባቱ ውድ በመሆኑና በእርዳታም የሚመጣ በመሆኑ እኛ ስለፈለግን ብቻ መከተብ አንችልም" ብለዋል።
ነገር ግን አሁንም ክትባት የሚያስፈልጋቸው አካባቢዎች መኖራቸውን ያነሱት ባለሞያዋ ክትባቱ በመጣ ጊዜ ለመስጠት ዝግጁ ነን ሲሉ አክለዋል።
@tikvahethmagazine
October 23, 2024