አምባሳደር መለስ አለም...
ዛሬ #በናይሮቢ መድኃኒያለም ቤተ ክርስትያን ባለፈው ሳምንት ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ በመብረር ላይ ሳለ #ቢሾፍቱ አቅራቢያ በተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ቦንግ 737 ሕይወታቸውን ላጡ መንገደኞች የመታሰቢያ ፀሎት ስነ ስርዓት ላይ አምባሳደር #መለስ_አለም ተገኝተው ንግግር አድርገዋል። በፀሎት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ሰፋ ያለ ንግግር ያደረጉት አምባሳደር #መለስ የአውሮፕላኑ አደጋ በደረሰበት ዕለት ወደ ናይሮቢ እንደመጡና #በተከሰከሰው አውሮፕላን #ሊሳፈሩ እንደነበርም ተናግረዋል።
Via BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዛሬ #በናይሮቢ መድኃኒያለም ቤተ ክርስትያን ባለፈው ሳምንት ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ በመብረር ላይ ሳለ #ቢሾፍቱ አቅራቢያ በተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ቦንግ 737 ሕይወታቸውን ላጡ መንገደኞች የመታሰቢያ ፀሎት ስነ ስርዓት ላይ አምባሳደር #መለስ_አለም ተገኝተው ንግግር አድርገዋል። በፀሎት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ሰፋ ያለ ንግግር ያደረጉት አምባሳደር #መለስ የአውሮፕላኑ አደጋ በደረሰበት ዕለት ወደ ናይሮቢ እንደመጡና #በተከሰከሰው አውሮፕላን #ሊሳፈሩ እንደነበርም ተናግረዋል።
Via BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
AAU-EiABC🔝የረዳት አብራሪ አህመድ ኑር መሐመድ የመታሰቢያ ስነ ስርዓት #በAAU እየተካሄደ ይገኛል።
ፎቶ፦ George A(TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ፦ George A(TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰበር ዜና‼️
የተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመረጃ ሳጥን (black box) #ሙሉ_መረጃው ሊያስገኝ በሚችል ደረጃ ላይ መሆኑን ምርመራውን ያከናወነው የፈረንሳዩ ቢ.ኢ.ኤ የአውሮፕላን አደጋ ምርመራ ኤጀንሲ ማስታወቁን የትራንስፖርት ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት መረጃዎቹን #መረከቡን የትራንስፖርት ሚኒስትር ዳግማዊት ሞገስ ለኢቢሲ ተናግረዋል፡፡
ዝርዝር #ትንተናው በቅርቡ በአንድ ወር ውስጥ ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግም ተገልጿል፡፡ ከመረጃ ሳጥኑ የሚገኙ መረጃዎች በቅርቡ ለ157 ሰዎች ህይወት ማጣት ምክንያት ለሆነው የቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን መከስከስ ምክንያት ፍንጭ እንደሚጠቁም የሮይተርስ ዘገባ ያስረዳል፡፡
Via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመረጃ ሳጥን (black box) #ሙሉ_መረጃው ሊያስገኝ በሚችል ደረጃ ላይ መሆኑን ምርመራውን ያከናወነው የፈረንሳዩ ቢ.ኢ.ኤ የአውሮፕላን አደጋ ምርመራ ኤጀንሲ ማስታወቁን የትራንስፖርት ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት መረጃዎቹን #መረከቡን የትራንስፖርት ሚኒስትር ዳግማዊት ሞገስ ለኢቢሲ ተናግረዋል፡፡
ዝርዝር #ትንተናው በቅርቡ በአንድ ወር ውስጥ ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግም ተገልጿል፡፡ ከመረጃ ሳጥኑ የሚገኙ መረጃዎች በቅርቡ ለ157 ሰዎች ህይወት ማጣት ምክንያት ለሆነው የቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን መከስከስ ምክንያት ፍንጭ እንደሚጠቁም የሮይተርስ ዘገባ ያስረዳል፡፡
Via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ የሚውል የሁለት ቢሊዮን ብር ፈንድ አፀደቀ፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ ዛሬ ባደረገው ስብሰባ ለወጣቶች ተዘዋዋሪ የብድር ፈንድ ለመመደብ የቀረበ ረቂቅ ሰነድ ላይ ተወያይቶ አፅድቋል፡፡ በዚህም መሠረት ዝርዝር ዕቅዶችን በማዘጋጀት እና በአፋጣኝ ከወጣቱ ጋር ሰፊ የምክክር መድረኮችን በማዘጋጀት የጋራ መግባባት ላይ ከተደረሰ በኃላ ወጣቶቹ በተለያየ ዘርፍ ወደ ስራ እንዲገቡ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡ በከተማዋ ከ700ሺ በላይ ስራ አጥ ወጣት እንዳሉ መረጃዎች የሚያመለክቱ ሲሆን ይህ የሁለት ቢሊዮን ብር ተዘዋዋሪ የብድር ፈንድ ይህንን የስራ አጥ ቁጥር ለመቀነስ እና የከተማዋን ኢኮኖሚ በማነቃቃቱ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅዖ እንደሚኖረውም ይጠበቃል፡፡
Via @MayorOfficeAA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via @MayorOfficeAA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሳዛኝ ዜና‼️
#ለልቅሶ_የወጡ_እናቶች በመኪና አዳጋ ህይወታቸዉ አለፈ፡፡ በምስረቅ ጎጃም ዞን #ማቻክል_ወረዳ ከደጋ ሰኝን ታዳጊ ከተማ ወደ አማኑኤል ከተማ ህዝብ ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ኮድ 3 አማ 05430 የሆነ አይሱዝ ቅጥቅጥ የህዝብ ማመለለሻ መኪና ከተፈቀደለት የጭነት ልክ በላይ ጭኖ ስለነበር አማኑኤል ዙርያ ቀበሌ ጎጃም ዱር አካባቢ በመገልበጡ ለልቅሶ የወጡ የሁለት እናቶች ህይወት ወዲያዉኑ ሲያልፍ በበርካታ ተሳፋሪዎች ላይ ቀላልና ከባድ አካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡
Via Machakel Woreda Government Communication Affairs
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ለልቅሶ_የወጡ_እናቶች በመኪና አዳጋ ህይወታቸዉ አለፈ፡፡ በምስረቅ ጎጃም ዞን #ማቻክል_ወረዳ ከደጋ ሰኝን ታዳጊ ከተማ ወደ አማኑኤል ከተማ ህዝብ ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ኮድ 3 አማ 05430 የሆነ አይሱዝ ቅጥቅጥ የህዝብ ማመለለሻ መኪና ከተፈቀደለት የጭነት ልክ በላይ ጭኖ ስለነበር አማኑኤል ዙርያ ቀበሌ ጎጃም ዱር አካባቢ በመገልበጡ ለልቅሶ የወጡ የሁለት እናቶች ህይወት ወዲያዉኑ ሲያልፍ በበርካታ ተሳፋሪዎች ላይ ቀላልና ከባድ አካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡
Via Machakel Woreda Government Communication Affairs
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"በቅርቡ አደጋ የደረሰበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር 302 ከመረጃ ሳጥን (FDR & CVR) ሙሉ መረጃው #በተሳካ ሁኔታ መገልበጥ ተችሏል። በስፍራው የሚገኙ ባለሞያዎቻችንና አሜሪካዉያን ኤክስፐርቶች የመረጃውን #ትክክለኝነት አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ መንግስት መረጃዎቹን የተረከበ ሲሆን እስካሁን በነበረው ሂደት የአደጋው መንስኤ #ከኢንዶንዢያው በረራ 610 ጋር የሚመሳሰል ሆኖ ተገኝቷል። በቀጣይ በሚደረግ ዝርዝር ትንተና መሰረት በአንድ ወር ውስጥ ለህዝብ ይፋ ይሆናል፡፡ በእስካሁኑ ሂደት የፈረንሳይ መንግስት ላደረገው ትብብር ማመስገን አንወዳልን።" -- Dagmawit Moges
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለወገን ደራሽ ወገን ነው🔝
በዛሬው ዕለት #በወላይታ_ሶዶ_ከተማ በተካሄደው የወላይታ ዲቻ እና የሽረ ስሁል ጨዋታ ለጌዴኦ ተፈናቃዮች የእርዳታ ማሰባሰቢያ ስራዎች ሲካሄዱ ውለዋል። እቅስሴውን ያስተባበሩት የወላይታ ወጣቶች(የለጋ) ከየወላይታ ዲቻ ስፖርት ክለብ የደጋፊዎች ማህበር ጋር በመሆን ነው። መረጃውን ያደረሰን የወላይታ ዲቻ ስፖርት ክለብ የደጋፊዎች ማህበር ፕሬዘዳንት አንዱአለም እንደነገረን በዛሬው ውሎ ከ50ሺ ብር በላይ ተሰብስቧል። 9,111 ብር ወጣቶቹ በመንገድ ላይ ሆነው ከከተማው ህዝብ የሰበሰቡት ሲሆን፤ 41,025 ብር ደግሞ በስታዲየሙ ከተገኘው ደጋፊ የተሰበሰበ እንደሆነ አዱአለም ነግሮናል። ስራው ቀጣይነት እንደሚኖረውም ጨምሮ ነግሮናል። ከገንዘብ በተጨማሪም በቁሳቁስ የከተማው ነዋሪ ለጌዴኦ ተፈናቃዮች ድጋፍ ማድረጉን በከተማው የሚኖሩ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ገልፀዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በዛሬው ዕለት #በወላይታ_ሶዶ_ከተማ በተካሄደው የወላይታ ዲቻ እና የሽረ ስሁል ጨዋታ ለጌዴኦ ተፈናቃዮች የእርዳታ ማሰባሰቢያ ስራዎች ሲካሄዱ ውለዋል። እቅስሴውን ያስተባበሩት የወላይታ ወጣቶች(የለጋ) ከየወላይታ ዲቻ ስፖርት ክለብ የደጋፊዎች ማህበር ጋር በመሆን ነው። መረጃውን ያደረሰን የወላይታ ዲቻ ስፖርት ክለብ የደጋፊዎች ማህበር ፕሬዘዳንት አንዱአለም እንደነገረን በዛሬው ውሎ ከ50ሺ ብር በላይ ተሰብስቧል። 9,111 ብር ወጣቶቹ በመንገድ ላይ ሆነው ከከተማው ህዝብ የሰበሰቡት ሲሆን፤ 41,025 ብር ደግሞ በስታዲየሙ ከተገኘው ደጋፊ የተሰበሰበ እንደሆነ አዱአለም ነግሮናል። ስራው ቀጣይነት እንደሚኖረውም ጨምሮ ነግሮናል። ከገንዘብ በተጨማሪም በቁሳቁስ የከተማው ነዋሪ ለጌዴኦ ተፈናቃዮች ድጋፍ ማድረጉን በከተማው የሚኖሩ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ገልፀዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia