#AddisAbaba
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በማዕከል ደረጃ ያለውን የሰራተኛ ቁጥር በመቀነስ ከፍተኛ የሥራ ጫና ወደ አለባቸው ወረዳ እና ተቋማት #ስርጭት እንዲደረግ ወስኗል።
ውሳኔው የተወሰነው ዛሬ በተካሄደው የካቢኔው የ3ኛ ዓመት 5ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ሲሆን ውሳኔው ከተማዋ ከምታመነጨው ገቢ እና ለህብረተሰብ ከሚሰጠው አገልግሎት አንፃር የማይመጣጠን በመሆኑ የተወሰነ እንደሆነ ነው የተገለጸው።
ይህንንም ውሳኔ ተቋማት ሙያዊ እና ተፈላጊ ችሎታን ታሳቢ አድርገው እንዲያስተገብሩ እንዲደረግ ትዕዛዝ ተላልፏል።
በተጨማሪም አሁን በውስጥ አቅም የሚሰሩ ሥራዎችን ለ3ተኛ ወገን በማስተላለፍ (Outsource) መስራትን የሚያስችል ውሳኔም ተላልፏል።
ለሦስተኛ ወገን የሚተላለፉት ሥራዎች ጥሩ እና ተፈላጊውን ውጤት ያመጣሉ ተብለው በጥናት የተለዩ አገልግሎቶች እንደሆኑ ነው የተጠቆመው።
👋 @TikvahethMagazine
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በማዕከል ደረጃ ያለውን የሰራተኛ ቁጥር በመቀነስ ከፍተኛ የሥራ ጫና ወደ አለባቸው ወረዳ እና ተቋማት #ስርጭት እንዲደረግ ወስኗል።
ውሳኔው የተወሰነው ዛሬ በተካሄደው የካቢኔው የ3ኛ ዓመት 5ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ሲሆን ውሳኔው ከተማዋ ከምታመነጨው ገቢ እና ለህብረተሰብ ከሚሰጠው አገልግሎት አንፃር የማይመጣጠን በመሆኑ የተወሰነ እንደሆነ ነው የተገለጸው።
ይህንንም ውሳኔ ተቋማት ሙያዊ እና ተፈላጊ ችሎታን ታሳቢ አድርገው እንዲያስተገብሩ እንዲደረግ ትዕዛዝ ተላልፏል።
በተጨማሪም አሁን በውስጥ አቅም የሚሰሩ ሥራዎችን ለ3ተኛ ወገን በማስተላለፍ (Outsource) መስራትን የሚያስችል ውሳኔም ተላልፏል።
ለሦስተኛ ወገን የሚተላለፉት ሥራዎች ጥሩ እና ተፈላጊውን ውጤት ያመጣሉ ተብለው በጥናት የተለዩ አገልግሎቶች እንደሆኑ ነው የተጠቆመው።
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM