TIKVAH-MAGAZINE
199K subscribers
18.9K photos
292 videos
70 files
2.48K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

#ኢትዮጵያ

ያግኙን +251913134524
加入频道
የናይጄሪያው ''ቤንቶ'' በፈረንጆቹ ቀጣይ ዓመት መጨረሻ በኢትዮጵያ ሥራውን ለመጀመር እያማተረ ነው።

የናይጄሪያው የክፍያ መቆጣጠሪያ እና የሰው ኃይል አስተዳደር ቴክኖሎጂ አቅራቢ የሆነው ''ቤንቶ'' በቀጣዩ ዓመት በአፍሪካ በኬንያ፣ ሩዋንዳና ጋና በሌሎች ስድስት ሀገራት ውስጥ ሥራውን ለማሥፋፋት ማቀዱን ገልጿል።

''ቤንቶ'' በፈረንጆቹ ቀጣይ ዓመት መጨረሻ ሥራዬን እጀምርባቸዋለው ብሎ ዐይኑን ካሳረፈባቸው ሀገራት መካከል #ኢትዮጵያ የምትገኝ ሲሆን ግብፅ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ኡጋንዳ፣ ታንዛኒያና፣ አንጎላም በዝርዝሩ ተካተውበታል ተብሏል።

በ2019 የተመሰረተው ''ቤንቶ'' በአፍሪካ የዘርፉን ገቢያ በመምታት ላይ ይገኛል የተባለ ሲሆን ሥርዓቱ በተለምዶ ደሞዝ ለመክፈል አድካሚ የሆኑ ሂደቶችን የሚያቀል እንዲሁም የሰው ኃብት አስተዳደርን ለመምራት የሚያግዝነው። (TechCrunch)

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
#Ethiopia🇪🇹

ኮንጎ ኪንሻሳ በሚደረገው የፓን አፍሪካ የት/ቤቶች ውድድር ላይ በሁለቱም ፆታዎች #ኢትዮጵያ'ን የሚወክሉት የዲላ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት(በሴቶች) እና አዋሮ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት(በወንዶች) ወደ ስፍራው ተጉዘዋል።

መልካም የውድድር ጊዜ!

Credit :- ሀና ገብረስላሴ /@tikvahethsport

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot