TIKVAH-MAGAZINE
199K subscribers
18.9K photos
292 videos
70 files
2.48K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

#ኢትዮጵያ

ያግኙን +251913134524
加入频道
#ነፃ_የትምህርት_ዕድል

LG-KOICA Hope የቴክኒክና ሞያ ኮሌጅ በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በግል ከፍለው መማር ለሚቸገሩና የመግቢያ መስፈርቱን ለሚያሟሉ ተማሪዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች ተማሪዎችን በነጻ ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል።

ኮሌጁ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች በላከው መልዕክት በዚህ ዙር እስከ 150 ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር መዘጋጀቱን ገልጾ የሀገር ዉስጥና የዉጭ ሀገር የሥራ ዕድል አማራጮችም እንዳሉት ጠቅሷል።

ከዚህም በተጨማሪ መስፈርቱን አሟልተው ለሚመረጡ ተማሪዎች በነጻ ማስተማር ብቻ ሳይሆን የምግብ፣ የትራንስፖርት እና ሌሎች ወጪዎችን እንደሚሸፍን ገልጿል።

ለማመልከት የሚያስፈልጉ መስፈርቶች፦

1. መንግስት ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ያስቀመጠዉን የቴክኒክና ሙያ የመግቢያ መስፈርት የሚያሟሉ፤

2. የኮሌጁን መግቢያ ፈተና  ማለፍ የሚችሉ፤

3. ከፍለው ለመማር  የማይችሉ ይኽንን የሚገልጽ ማስረጃ ከሚኖሩበት ቀበሌ ካመጡ ቅድሚያ ያገኛሉ።

የትምህርት መስኮች፦

#Electronics: Electrical Electronics equipment servicing management[ Level III & IV]

#IT : Hardware and network servicing [Level III & IV]

#የማመልከቻ_ጊዜ፡ ከየካቲት 24 - መጋቢት 22 ባሉት 21 ተከታታይ የስራ ቀናት

#አድራሻ: ሰሚት ኮንዶሚኒየም 3ኛ በር ከጠዋቱ 2፡00 - 1፡00 ሰአት

#ስልክ:  011-6-67-75-64 / 011-6-66-18-29

@tikvahethmagazine