#AddisAbaba
በአዲስ አበባ ከተማ በመንግስት የግል ባለብቶች ቅንጅት የተገነቡ ዳቦ ቤቶች ላይ የሚቀርቡ ዳቦዎች ዝቅተኛ ግራምና ዋጋ ተመን ወጥቶላቸዋል።
በዚህም፦
- በዳቦ ቤቶቹ የሚቀርበው ዝቅተኛ ዳቦ ግራም 70 እንዲሆን፤
- የዳቦ ዋጋውም 6:00 ብር ሆኖ ለህብረተሰቡ መሰራጨት እንዲችል ተወስኗል።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ የንግድ ግብይት ዘርፍ ከባለህብቶቹና ተወካዮቻቸው ጋር ውይይት ካካሄደ በኋላ መሆኑን ገልጿል።
👋 @TikvahethMagazine
በአዲስ አበባ ከተማ በመንግስት የግል ባለብቶች ቅንጅት የተገነቡ ዳቦ ቤቶች ላይ የሚቀርቡ ዳቦዎች ዝቅተኛ ግራምና ዋጋ ተመን ወጥቶላቸዋል።
በዚህም፦
- በዳቦ ቤቶቹ የሚቀርበው ዝቅተኛ ዳቦ ግራም 70 እንዲሆን፤
- የዳቦ ዋጋውም 6:00 ብር ሆኖ ለህብረተሰቡ መሰራጨት እንዲችል ተወስኗል።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ የንግድ ግብይት ዘርፍ ከባለህብቶቹና ተወካዮቻቸው ጋር ውይይት ካካሄደ በኋላ መሆኑን ገልጿል።
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#AddisAbaba
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በማዕከል ደረጃ ያለውን የሰራተኛ ቁጥር በመቀነስ ከፍተኛ የሥራ ጫና ወደ አለባቸው ወረዳ እና ተቋማት #ስርጭት እንዲደረግ ወስኗል።
ውሳኔው የተወሰነው ዛሬ በተካሄደው የካቢኔው የ3ኛ ዓመት 5ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ሲሆን ውሳኔው ከተማዋ ከምታመነጨው ገቢ እና ለህብረተሰብ ከሚሰጠው አገልግሎት አንፃር የማይመጣጠን በመሆኑ የተወሰነ እንደሆነ ነው የተገለጸው።
ይህንንም ውሳኔ ተቋማት ሙያዊ እና ተፈላጊ ችሎታን ታሳቢ አድርገው እንዲያስተገብሩ እንዲደረግ ትዕዛዝ ተላልፏል።
በተጨማሪም አሁን በውስጥ አቅም የሚሰሩ ሥራዎችን ለ3ተኛ ወገን በማስተላለፍ (Outsource) መስራትን የሚያስችል ውሳኔም ተላልፏል።
ለሦስተኛ ወገን የሚተላለፉት ሥራዎች ጥሩ እና ተፈላጊውን ውጤት ያመጣሉ ተብለው በጥናት የተለዩ አገልግሎቶች እንደሆኑ ነው የተጠቆመው።
👋 @TikvahethMagazine
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በማዕከል ደረጃ ያለውን የሰራተኛ ቁጥር በመቀነስ ከፍተኛ የሥራ ጫና ወደ አለባቸው ወረዳ እና ተቋማት #ስርጭት እንዲደረግ ወስኗል።
ውሳኔው የተወሰነው ዛሬ በተካሄደው የካቢኔው የ3ኛ ዓመት 5ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ሲሆን ውሳኔው ከተማዋ ከምታመነጨው ገቢ እና ለህብረተሰብ ከሚሰጠው አገልግሎት አንፃር የማይመጣጠን በመሆኑ የተወሰነ እንደሆነ ነው የተገለጸው።
ይህንንም ውሳኔ ተቋማት ሙያዊ እና ተፈላጊ ችሎታን ታሳቢ አድርገው እንዲያስተገብሩ እንዲደረግ ትዕዛዝ ተላልፏል።
በተጨማሪም አሁን በውስጥ አቅም የሚሰሩ ሥራዎችን ለ3ተኛ ወገን በማስተላለፍ (Outsource) መስራትን የሚያስችል ውሳኔም ተላልፏል።
ለሦስተኛ ወገን የሚተላለፉት ሥራዎች ጥሩ እና ተፈላጊውን ውጤት ያመጣሉ ተብለው በጥናት የተለዩ አገልግሎቶች እንደሆኑ ነው የተጠቆመው።
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#AddisAbaba
ከልደታ ቆርቆሮ ሰፈርና ከዓድዋ ድል መታሰቢያ ዙሪያ ለልማት ለሚነሱ ነዋሪዎች የሚሰጡ ከ300 በላይ የሚሆኑ የመኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል።
ከንቲባ አዳነች ዛሬ ማለዳ ልደታ ቤተክርስታያን አካባቢ ለልማት ተነሺዎች የሚተላለፍ ሁለት ባለ 9 ወለል የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ ከሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ጋር በመሆን የመሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ግንባታውን በይፋ ማስጀመራቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልፀዋል።
ቀድም ተብሎ ከተጀመሩት ጋር ከ300 በላይ የሚሆኑ የመኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ መሆኑን የገለፀት ከንቲባዋ እነዚህ በመገንባት ላይ ያሉ ቤቶች ከልደታ ቆርቆሮ ሰፈርና ከዓድዋ ድል መታሰቢያ ዙሪያ ለልማት ለሚነሱ ነዋሪዎች የሚሰጡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
@TikvahethMagazine
ከልደታ ቆርቆሮ ሰፈርና ከዓድዋ ድል መታሰቢያ ዙሪያ ለልማት ለሚነሱ ነዋሪዎች የሚሰጡ ከ300 በላይ የሚሆኑ የመኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል።
ከንቲባ አዳነች ዛሬ ማለዳ ልደታ ቤተክርስታያን አካባቢ ለልማት ተነሺዎች የሚተላለፍ ሁለት ባለ 9 ወለል የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ ከሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ጋር በመሆን የመሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ግንባታውን በይፋ ማስጀመራቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልፀዋል።
ቀድም ተብሎ ከተጀመሩት ጋር ከ300 በላይ የሚሆኑ የመኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ መሆኑን የገለፀት ከንቲባዋ እነዚህ በመገንባት ላይ ያሉ ቤቶች ከልደታ ቆርቆሮ ሰፈርና ከዓድዋ ድል መታሰቢያ ዙሪያ ለልማት ለሚነሱ ነዋሪዎች የሚሰጡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
@TikvahethMagazine
#AddisAbaba
የ20ሚሊዮን ብር የዋጋ ግምት ያለው በህገወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ የተለያዩ መድሃኒቶች በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
ፖሊስ መድሃኒት የማከፋፈል ሆነ የመሸጥ ፍቃድ የለውም ያለው ተጠርጣሪ የህገ-ወጥ መድሃኒቱን አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ዱባይ ተራ ህንፃ የታችኛው ክፍል ደብቆት ነበር ብሏል።
ግለሰቡ፥ የካቲት 10 ቀን 2016 ዓ/ም መድሀኒቱን ወደ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ቦታው ታደሰ ብሩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጀርባ ወዳለው የግል መኖሪያ ቤት በመውሰድ በዚያ አከማችቶ መያዙን ፖሊስ አስታውቋል።
@TikvahethMagazine
የ20ሚሊዮን ብር የዋጋ ግምት ያለው በህገወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ የተለያዩ መድሃኒቶች በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
ፖሊስ መድሃኒት የማከፋፈል ሆነ የመሸጥ ፍቃድ የለውም ያለው ተጠርጣሪ የህገ-ወጥ መድሃኒቱን አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ዱባይ ተራ ህንፃ የታችኛው ክፍል ደብቆት ነበር ብሏል።
ግለሰቡ፥ የካቲት 10 ቀን 2016 ዓ/ም መድሀኒቱን ወደ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ቦታው ታደሰ ብሩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጀርባ ወዳለው የግል መኖሪያ ቤት በመውሰድ በዚያ አከማችቶ መያዙን ፖሊስ አስታውቋል።
@TikvahethMagazine
#AddisAbaba
በቅዱስ ጳውሎስ ሚሊኒየም ሆስፒታል እና በሬቲና ፋርማሲዩቲካልስ በጋራ የሚተገበር አዲስ የዲያግኖስቲክ ማእከል ግንባታ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ ስምምነት ተፈርሟል።
ስምምነቱ፥ በተለይም በሆስፒታሉ የሚሰጠው የላብራቶሪ አገልግሎት መቆራረጥን የሚያስቀር መሆኑም የተገለጸ ሲሆን፤ የአገልግሎት ክፍያውም ቢሆን ከግል ተቋማት ጋር ሲነጻጸር በግማሽ ያህል ቅናሽ እንደሚኖረው በመድረኩ ተገልጿል፡፡
ላብራቶሪው አገልግሎት መስጠት ሲጀምር አሁን ላይ በሆስፒታሉ ከሚሰጡት የላብራቶሪ አገልግሎቶች በተጨማሪ ሌሎች አዳዲስ አገልግሎቶችንም መስጠት የሚያችል በመሆኑ በቀጥታ የሆስፒታሉን ተገልጋዮች ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሏል፡፡
@TikvahethMagazine
በቅዱስ ጳውሎስ ሚሊኒየም ሆስፒታል እና በሬቲና ፋርማሲዩቲካልስ በጋራ የሚተገበር አዲስ የዲያግኖስቲክ ማእከል ግንባታ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ ስምምነት ተፈርሟል።
ስምምነቱ፥ በተለይም በሆስፒታሉ የሚሰጠው የላብራቶሪ አገልግሎት መቆራረጥን የሚያስቀር መሆኑም የተገለጸ ሲሆን፤ የአገልግሎት ክፍያውም ቢሆን ከግል ተቋማት ጋር ሲነጻጸር በግማሽ ያህል ቅናሽ እንደሚኖረው በመድረኩ ተገልጿል፡፡
ላብራቶሪው አገልግሎት መስጠት ሲጀምር አሁን ላይ በሆስፒታሉ ከሚሰጡት የላብራቶሪ አገልግሎቶች በተጨማሪ ሌሎች አዳዲስ አገልግሎቶችንም መስጠት የሚያችል በመሆኑ በቀጥታ የሆስፒታሉን ተገልጋዮች ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሏል፡፡
@TikvahethMagazine
#AddisAbaba
በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ቡልቡላና አካባቢው ያሉ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የሚያደርግ የ14 ኪሎ ሜትር የመካከለኛ መስመር ዝርጋታ ከኮየ-አቦ እስከ ቦሌ ቡልቡላ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል።
172 ሚሊየን ብር ወጪ የሚፈጅው ፕሮጀክቱ፤
ጥር 1 ቀን 2016 ዓ.ም ተጀምሮ አሁን ላይ 14 ኪ.ሜ የሚሸፍን 320 የኮንክሪት ምሰሶ ተከላ ስራ ተከናውኗል። ቀድም ሲል በአካባቢው ተደጋጋሚ የኃይል መቆራረጥ የነበረ ሲሆን፤ የተጀመረው ሥራ ሲጠናቀቅ በቦሌ ቡልቡላና አካባቢው የነበረውን ችግር በከፍተኛ ደረጃ መቅረፍ የሚያስችል ይሆናል ብሏል ተቋሙ።
@TikvahethMagazine
በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ቡልቡላና አካባቢው ያሉ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የሚያደርግ የ14 ኪሎ ሜትር የመካከለኛ መስመር ዝርጋታ ከኮየ-አቦ እስከ ቦሌ ቡልቡላ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል።
172 ሚሊየን ብር ወጪ የሚፈጅው ፕሮጀክቱ፤
ጥር 1 ቀን 2016 ዓ.ም ተጀምሮ አሁን ላይ 14 ኪ.ሜ የሚሸፍን 320 የኮንክሪት ምሰሶ ተከላ ስራ ተከናውኗል። ቀድም ሲል በአካባቢው ተደጋጋሚ የኃይል መቆራረጥ የነበረ ሲሆን፤ የተጀመረው ሥራ ሲጠናቀቅ በቦሌ ቡልቡላና አካባቢው የነበረውን ችግር በከፍተኛ ደረጃ መቅረፍ የሚያስችል ይሆናል ብሏል ተቋሙ።
@TikvahethMagazine
#AddisAbaba
የአንበሳ እና ሸገር ከተማ አውቶቡሶች የመገልገያ ትኬት ከነገ ጀምሮ የሚቀየር መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት አስታወቀ።
ትኬቶችን የመቀየር ስራ የመዲናዋ የትራንስፖርት ቢሮ በኪሎ ሜትር ባወጣው የትራንስፖርት ታሪፍ መሰረት ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑን አስታውቋል። በመሆኑም አውቶቡሶቹ ከዚህ ቀደም ሲጠቀሙበት የነበረው ትኬት በባለ 5፣ 10፣ 15፣ 20 እና ባለ 25 ብር ይቀይራል ብሏል፡፡
በዚህም መሰረት የካቲት 19 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በሁለቱም ድርጅቶች የተቀየረው አዲስ ቲኬት ሙሉ በሙሉ ሥራ የሚጀምር ሲሆን በአዲስ መልክ ስራ ላይ የሚውለው ትኬት ከነባሩ የተለየ ቀለም፣ ወጥ የሆነ ዋጋ፣ ምስጢራዊ መለያ ያለው መሆኑን የዘገበው ኢዜአ ነው።
@TikvahethMagazine
የአንበሳ እና ሸገር ከተማ አውቶቡሶች የመገልገያ ትኬት ከነገ ጀምሮ የሚቀየር መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት አስታወቀ።
ትኬቶችን የመቀየር ስራ የመዲናዋ የትራንስፖርት ቢሮ በኪሎ ሜትር ባወጣው የትራንስፖርት ታሪፍ መሰረት ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑን አስታውቋል። በመሆኑም አውቶቡሶቹ ከዚህ ቀደም ሲጠቀሙበት የነበረው ትኬት በባለ 5፣ 10፣ 15፣ 20 እና ባለ 25 ብር ይቀይራል ብሏል፡፡
በዚህም መሰረት የካቲት 19 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በሁለቱም ድርጅቶች የተቀየረው አዲስ ቲኬት ሙሉ በሙሉ ሥራ የሚጀምር ሲሆን በአዲስ መልክ ስራ ላይ የሚውለው ትኬት ከነባሩ የተለየ ቀለም፣ ወጥ የሆነ ዋጋ፣ ምስጢራዊ መለያ ያለው መሆኑን የዘገበው ኢዜአ ነው።
@TikvahethMagazine
#AddisAbaba
በአዲስ አበባ የተማሪዎችን አጠቃላይ መረጃ የሚይዝና ጥራት አመላካች አሃዶችን የሚተነትን ኢ ስኩል ሶፍትዌር በትምህርት ቤቶች ተግባራዊ ሊሆን ነው።
ሥርዓቱ በሁሉም አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተግባራዊ እንደሚሆን ሲጠቆም በትምህርት ቤቶች ከመረጃ አያያዝና ትንተና ጋር የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለመሙላት እንዲሁም ለተማሪዎች ዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት ለማቅረብ እድል ይፈጥራል ተብሏል።
ሥርዓቱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ግብዓቶች ሙሉ በሙሉ በሁሉም ትምህርት ቤቶች መሟላታቸውን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ ገልፀዋል ሲል የዘገበው ኢዜአ ነው።
@TikvahethMagazine
በአዲስ አበባ የተማሪዎችን አጠቃላይ መረጃ የሚይዝና ጥራት አመላካች አሃዶችን የሚተነትን ኢ ስኩል ሶፍትዌር በትምህርት ቤቶች ተግባራዊ ሊሆን ነው።
ሥርዓቱ በሁሉም አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተግባራዊ እንደሚሆን ሲጠቆም በትምህርት ቤቶች ከመረጃ አያያዝና ትንተና ጋር የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለመሙላት እንዲሁም ለተማሪዎች ዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት ለማቅረብ እድል ይፈጥራል ተብሏል።
ሥርዓቱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ግብዓቶች ሙሉ በሙሉ በሁሉም ትምህርት ቤቶች መሟላታቸውን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ ገልፀዋል ሲል የዘገበው ኢዜአ ነው።
@TikvahethMagazine
#AddisAbaba
በአዲስ አበባ በ2016 በጀት ዓመት በአዲስ አበባ እና አከባቢው 523 የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች አጋጥመዋል።
በዚህ ጊዜ ውስጥ፦
- 351 የእሳት አደጋ፤ 172 ሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች አጋጥመዋል፡፡
- በእሳት አደጋ ሳቢያ የ2 ሰዎች ህይወት አልፏል።
- የአደጋ ጊዜ ሠራተኞችን ጨምሮ በ90 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል፡፡
- በእሳትና በሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች ምክንያት የ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር የንብረት ውድመት አጋጥሟል፡፡
- በአደጋ ጊዜ ሠራተኞች ርብርብ ከ37 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ከውድመት ማዳን ተችሏል፡፡
Source : ENA
#TikvahEthiopia
@tikvahethmagazine
በአዲስ አበባ በ2016 በጀት ዓመት በአዲስ አበባ እና አከባቢው 523 የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች አጋጥመዋል።
በዚህ ጊዜ ውስጥ፦
- 351 የእሳት አደጋ፤ 172 ሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች አጋጥመዋል፡፡
- በእሳት አደጋ ሳቢያ የ2 ሰዎች ህይወት አልፏል።
- የአደጋ ጊዜ ሠራተኞችን ጨምሮ በ90 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል፡፡
- በእሳትና በሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች ምክንያት የ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር የንብረት ውድመት አጋጥሟል፡፡
- በአደጋ ጊዜ ሠራተኞች ርብርብ ከ37 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ከውድመት ማዳን ተችሏል፡፡
Source : ENA
#TikvahEthiopia
@tikvahethmagazine
#AddisAbaba
የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ በከተማ አስተዳደሩ የተገነቡትን የኮልፌና የለሚኩራ የገበያ ማዕከላትን ለ3ተኛ ወገን ማስተላለፉን (Outsource) አስታውቋል።
የገቢያ ማዕከላቱን እንዲያስተዳድሩ ለሁለት የግል ድርጅቶች የተሰጠ ሲሆን 'ሀብ ቢዝነስ ግሩፕ' የአስተዳደሩን ስራ 'ኢትዮ ጥበቃ' ደግም የጽዳትና የጥበቃ ስራውን እንዲሰሩ የተመረጡ ድርጅቶች ናቸው ተብሏል።
ድርጅቶቹ ከሐምሌ 1 ቀን 2016ዓ.ም ጀምሮ ወደስራ መግባታቸውም ተገልጿል። የግብይት ስርዓቱ በየሳምንቱ ንግድ ቢሮ በሚያወጣው ተመን የሚካሄድ መሆኑም የተገለጸ ሲሆን አጠቃላይ ሂደቱን ቢሮው እንደሚቆጣጠርም ተገልጿል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በውስጥ አቅም የሚሰሩ ሥራዎችን ለ3ተኛ ወገን በማስተላለፍ (Outsource) መስራትን የሚያስችል ውሳኔ በዚህ ዓመት ሕዳር ወር ላይ ማስተላለፉ ይታወሳል።
@tikvahethmagazine
የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ በከተማ አስተዳደሩ የተገነቡትን የኮልፌና የለሚኩራ የገበያ ማዕከላትን ለ3ተኛ ወገን ማስተላለፉን (Outsource) አስታውቋል።
የገቢያ ማዕከላቱን እንዲያስተዳድሩ ለሁለት የግል ድርጅቶች የተሰጠ ሲሆን 'ሀብ ቢዝነስ ግሩፕ' የአስተዳደሩን ስራ 'ኢትዮ ጥበቃ' ደግም የጽዳትና የጥበቃ ስራውን እንዲሰሩ የተመረጡ ድርጅቶች ናቸው ተብሏል።
ድርጅቶቹ ከሐምሌ 1 ቀን 2016ዓ.ም ጀምሮ ወደስራ መግባታቸውም ተገልጿል። የግብይት ስርዓቱ በየሳምንቱ ንግድ ቢሮ በሚያወጣው ተመን የሚካሄድ መሆኑም የተገለጸ ሲሆን አጠቃላይ ሂደቱን ቢሮው እንደሚቆጣጠርም ተገልጿል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በውስጥ አቅም የሚሰሩ ሥራዎችን ለ3ተኛ ወገን በማስተላለፍ (Outsource) መስራትን የሚያስችል ውሳኔ በዚህ ዓመት ሕዳር ወር ላይ ማስተላለፉ ይታወሳል።
@tikvahethmagazine