#ደብረብርሃን
በደብረ ብርሃን የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ለማስጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው ተብሏል።
የደብረ ብርሃን ከተማ ትራንስፖርት ልማት ጽ/ቤት ፤ በትራንስፖርት ዘርፍ እየተፈጠረ ያለውን ጫና ለመቅረፍ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ለማስጀመር ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን አሳውቋል።
ጽ/ቤቱ በመንግስት ሠራተኛው ላይ የተፈጠረውን የኑሮ ውድነት ጫና ለማቃለል ሠራተኛው ለጊዜው #በነጻ_የትራንስፖረት_አገልግሎት እንዲጠቀም ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጿል።
የከተማ አውቶብስ አገልግሎት መጀመር በከተማ ታክሲ አገልግሎት ሰጪዎች ላይ የሚፈጥረው ጫና የለም ተብሏል።
የከተማ አውቶብስ አገልግሎት እንዲጀመር ትራንስፖረት ጽህፈት ቤት ያቀረበውን ዕቅድ የደብረብርሃን ከተማ ከንቲባ ኮሚቴ እና ገንዘብ መምሪያው ተቀብለው ወደ ስራ እንዲገባ መፍቀዳቸው መገለፁን ከከተማው ኮሚኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
@tikvahethiopia
በደብረ ብርሃን የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ለማስጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው ተብሏል።
የደብረ ብርሃን ከተማ ትራንስፖርት ልማት ጽ/ቤት ፤ በትራንስፖርት ዘርፍ እየተፈጠረ ያለውን ጫና ለመቅረፍ የከተማ አውቶብስ አገልግሎት ለማስጀመር ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን አሳውቋል።
ጽ/ቤቱ በመንግስት ሠራተኛው ላይ የተፈጠረውን የኑሮ ውድነት ጫና ለማቃለል ሠራተኛው ለጊዜው #በነጻ_የትራንስፖረት_አገልግሎት እንዲጠቀም ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጿል።
የከተማ አውቶብስ አገልግሎት መጀመር በከተማ ታክሲ አገልግሎት ሰጪዎች ላይ የሚፈጥረው ጫና የለም ተብሏል።
የከተማ አውቶብስ አገልግሎት እንዲጀመር ትራንስፖረት ጽህፈት ቤት ያቀረበውን ዕቅድ የደብረብርሃን ከተማ ከንቲባ ኮሚቴ እና ገንዘብ መምሪያው ተቀብለው ወደ ስራ እንዲገባ መፍቀዳቸው መገለፁን ከከተማው ኮሚኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
@tikvahethiopia
#ግሪንላይፍ_ስፔሻሊቲ_ዴንታል_ክሊኒክ
🦷 የወለቁ ጥርሶችን ያለምንም እንከን በኢምፕላንት እንተክላለን ፡፡
🪥በእጅግ ዘመናዊ የብሬስ ህክምና ውስብስብ የሆኑትን ጥርሶችን እናስተካክላለን።
🔬በዓለምአቀፉ ታዋቂ ከሆኑ ላብራቶሪ ጋር በመተባበር በዝርኮኒያ ቋሚ ጥርሶችን እንተክላለን ፡፡
👦 ቋሚ የልጆች ጥርስ (በpit & fissure sealant) ማከም
አድራሻ ፦
https://www.facebook.com/GreenLife-speciality-Dental-Clinic-1866888506724080/
http://www.greenlifeethiopia.com
http://yangx.top/Greenlifedentalclini
🦷 የወለቁ ጥርሶችን ያለምንም እንከን በኢምፕላንት እንተክላለን ፡፡
🪥በእጅግ ዘመናዊ የብሬስ ህክምና ውስብስብ የሆኑትን ጥርሶችን እናስተካክላለን።
🔬በዓለምአቀፉ ታዋቂ ከሆኑ ላብራቶሪ ጋር በመተባበር በዝርኮኒያ ቋሚ ጥርሶችን እንተክላለን ፡፡
👦 ቋሚ የልጆች ጥርስ (በpit & fissure sealant) ማከም
አድራሻ ፦
https://www.facebook.com/GreenLife-speciality-Dental-Clinic-1866888506724080/
http://www.greenlifeethiopia.com
http://yangx.top/Greenlifedentalclini
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ፍርድ ቤት በዋስ ከእስር እንዲፈቱ የወሰነላቸው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ጋዜጠኛ መዓዛ መሀመድ እና ጋዜጠኛ ሰለሞን ሹምዬ ከእስር አልተለቀቁም። ዛሬ ግንቦት 30 ቀን 2014 ዓ.ም የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት፣ 3ቱ ጋዜጠኖች በ10 ሺ ብር ዋስ እንዲለቀቁ መወሰኑ ይታወሳል። ነገር ግን መርማሪ ፖሊስ ይግባኝ ለማለት ለ8 ሰዓት ቀጥሮ ነበር ሆኖም ችሎቱን የሚመሩት…
#ችሎት
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ መዓዛ መሐመድ እና ሰለሞን ሹምዬ ላይ የቀረበውን ይግባኝ መርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠት ለነገ ሐሙስ ሰኔ 2/2014 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በዛሬው ችሎት፤ ለ3ቱ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በስር ፍርድ ቤት የተፈቀደው ዋስትና ውድቅ እንዲደረግ እና 14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።
የቀረበውን ይግባኝ መርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠት ለነገ ሐሙስ ሰኔ 2/2014 ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ መዓዛ መሐመድ እና ሰለሞን ሹምዬ ላይ የቀረበውን ይግባኝ መርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠት ለነገ ሐሙስ ሰኔ 2/2014 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በዛሬው ችሎት፤ ለ3ቱ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በስር ፍርድ ቤት የተፈቀደው ዋስትና ውድቅ እንዲደረግ እና 14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።
የቀረበውን ይግባኝ መርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠት ለነገ ሐሙስ ሰኔ 2/2014 ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት
ኢትዮ ቴሌኮም በመደበኛው ኤሌክትሪክ ሀይል (Commercial Power) መቋረጥ ምክንያት ፦
- በጅማ፣ መቱ እና አከባቢው፣
- በደቡብ (በሆሳዕና፣አርባ ምንጭ፣ሶዶ እና ሳውላ)፣
- በምዕራብ ወሎ አከባቢ፣
- በነቀምት እና አካባቢው፣
- አሶሳና አከባቢው፣
- በደቡብ ጎንደር እንዲሁም በአዲስ አበባ (በኮተቤ፣ጉርድሾላ፣ጣፎ፣ ቅሊንጦ እና ቱሉዲምቱ) በመጠባበቂያ ሀይል አገልግሎቱን ለማስቀጠል እየሞከረ መሆኑን አሳውቋል።
በዚህም በተወሰኑት አካባቢዎች በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የአገልግሎት መቋረጥ ሊያጋጥም እንደሚችል ገልጿል።
ድርጅቱ ችግሩን ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ በመሆኑን ገልጾ ደንበኞቹ በትዕግስት እንዲጠባበቁ ጠይቋል።
@tikvahethiopia
ኢትዮ ቴሌኮም በመደበኛው ኤሌክትሪክ ሀይል (Commercial Power) መቋረጥ ምክንያት ፦
- በጅማ፣ መቱ እና አከባቢው፣
- በደቡብ (በሆሳዕና፣አርባ ምንጭ፣ሶዶ እና ሳውላ)፣
- በምዕራብ ወሎ አከባቢ፣
- በነቀምት እና አካባቢው፣
- አሶሳና አከባቢው፣
- በደቡብ ጎንደር እንዲሁም በአዲስ አበባ (በኮተቤ፣ጉርድሾላ፣ጣፎ፣ ቅሊንጦ እና ቱሉዲምቱ) በመጠባበቂያ ሀይል አገልግሎቱን ለማስቀጠል እየሞከረ መሆኑን አሳውቋል።
በዚህም በተወሰኑት አካባቢዎች በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የአገልግሎት መቋረጥ ሊያጋጥም እንደሚችል ገልጿል።
ድርጅቱ ችግሩን ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ በመሆኑን ገልጾ ደንበኞቹ በትዕግስት እንዲጠባበቁ ጠይቋል።
@tikvahethiopia
#ጥቆማ
አዋሽ ባንክ አንድ ሚሊዮን ብር ሽልማት የሚያስገኝ የሥራ ፈጠራ ውድድር ይፋ ማድረጉ ይታወቃል።
የሥራ እድል ፈጠራን የሚያበረታታውና "ታታሪዎቹ" የተሰኘው ውድድሩ፤ አንድ ሺህ ተወዳዳሪዎችን እንደሚያሳትፍ ይጠበቃል።
አዳዲስ እና ችግር ፈቺ የሆኑ የሥራ ሀሳቦች ያላችሁ አመልካቾች በውድድሩ መሳተፍ ትችላላችሁ።
የማመልከቻ ቅጹ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት አማራጭ ሊንኮች ይገኛሉ፦
ለአማርኛ 👉
https://formfaca.de/sm/ibm6Nojej
ለአፋን ኦሮሞ👉
https://formfaca.de/sm/WZwSVKhOY
ለእንግሊዝኛ 👉
https://formfaca.de/sm/WFbP8sJNG
በተጨማሪም በየትኛውም የአዋሽ ባንክ ቅርንጫፍ በመቅረብና የተዘጋጀውን ፎርም በመሙላት ማመልከት ይቻላል ተብሏል።
የማመልከቻ ጊዜ 👉
ከግንቦት 24 እስከ ሰኔ 15/2014 ዓ.ም
@tikvahuniversity @tikvahethiopia
አዋሽ ባንክ አንድ ሚሊዮን ብር ሽልማት የሚያስገኝ የሥራ ፈጠራ ውድድር ይፋ ማድረጉ ይታወቃል።
የሥራ እድል ፈጠራን የሚያበረታታውና "ታታሪዎቹ" የተሰኘው ውድድሩ፤ አንድ ሺህ ተወዳዳሪዎችን እንደሚያሳትፍ ይጠበቃል።
አዳዲስ እና ችግር ፈቺ የሆኑ የሥራ ሀሳቦች ያላችሁ አመልካቾች በውድድሩ መሳተፍ ትችላላችሁ።
የማመልከቻ ቅጹ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት አማራጭ ሊንኮች ይገኛሉ፦
ለአማርኛ 👉
https://formfaca.de/sm/ibm6Nojej
ለአፋን ኦሮሞ👉
https://formfaca.de/sm/WZwSVKhOY
ለእንግሊዝኛ 👉
https://formfaca.de/sm/WFbP8sJNG
በተጨማሪም በየትኛውም የአዋሽ ባንክ ቅርንጫፍ በመቅረብና የተዘጋጀውን ፎርም በመሙላት ማመልከት ይቻላል ተብሏል።
የማመልከቻ ጊዜ 👉
ከግንቦት 24 እስከ ሰኔ 15/2014 ዓ.ም
@tikvahuniversity @tikvahethiopia
#WorldBank
የምሥራቅ አፍሪካ አገራት በአስርት ዓመታት ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት እንደተጋረጠባቸው የዓለም ባንክ ከሰሞኑ አስታውቋል።
የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት እንዲሁም የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ጫና ተደማምሮ አንዳንድ አገራት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ድቀት እያጋጠማቸው መሆኑን ባንኩ ገልጿል።
ከዚህም ጋር ተያይዞ ዓመታዊ ትንበያውን ቀንሷል።
ባንኩ በተለይም የምሥራቅ አፍሪካ አገራት እና አንዳንድ የአውሮፓ ክፍሎች ተጎጂ ሆነዋል ብሏል።
ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት እና ዝቅተኛ የምጣኔ ሀብረት ዕድገት ጥምረት ከ1970ዎቹ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊመለስ እንደሚችልም ጠቁሟል።
አገራቱ በምግብ እና በነዳጅ ዋጋ መጨመር ምክንያት ቀውስ እያጋጠማቸው መሆኑም ተገልጿል።
የዓለም ባንክ ኃላፊ ዴቪድ ማልፓስስ ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት ቆይታ የቀውሱን ሌላ ጎን ማየት ከባድ ነው ብለዋል።
አንዳንድ በማደግ ላይ ያሉ አገራት መንግሥታት እቃዎችን መግዛት አለመቻላቸውን እንዲሁም የብድር ዕዳ ውስጥ እየተዘፈቁ ነው ብለዋል ።
የባንኩ አዲስ የዓለም አቀፍ እድገት ትንበያ ከዜሮ በታች 2.9 በመቶ ሲሆን፣ ይህም በ80 ዓመታት ውስጥ ከፍተኛው መቀነስ የታየበት መሆኑን ቢቢሲ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
የምሥራቅ አፍሪካ አገራት በአስርት ዓመታት ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት እንደተጋረጠባቸው የዓለም ባንክ ከሰሞኑ አስታውቋል።
የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት እንዲሁም የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ጫና ተደማምሮ አንዳንድ አገራት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ድቀት እያጋጠማቸው መሆኑን ባንኩ ገልጿል።
ከዚህም ጋር ተያይዞ ዓመታዊ ትንበያውን ቀንሷል።
ባንኩ በተለይም የምሥራቅ አፍሪካ አገራት እና አንዳንድ የአውሮፓ ክፍሎች ተጎጂ ሆነዋል ብሏል።
ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት እና ዝቅተኛ የምጣኔ ሀብረት ዕድገት ጥምረት ከ1970ዎቹ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊመለስ እንደሚችልም ጠቁሟል።
አገራቱ በምግብ እና በነዳጅ ዋጋ መጨመር ምክንያት ቀውስ እያጋጠማቸው መሆኑም ተገልጿል።
የዓለም ባንክ ኃላፊ ዴቪድ ማልፓስስ ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት ቆይታ የቀውሱን ሌላ ጎን ማየት ከባድ ነው ብለዋል።
አንዳንድ በማደግ ላይ ያሉ አገራት መንግሥታት እቃዎችን መግዛት አለመቻላቸውን እንዲሁም የብድር ዕዳ ውስጥ እየተዘፈቁ ነው ብለዋል ።
የባንኩ አዲስ የዓለም አቀፍ እድገት ትንበያ ከዜሮ በታች 2.9 በመቶ ሲሆን፣ ይህም በ80 ዓመታት ውስጥ ከፍተኛው መቀነስ የታየበት መሆኑን ቢቢሲ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
#Hulugram
ተጨማሪ 10% ስጦታ ያግኙ! ከሚወዷቸው ለአፍታም ቢሆን እንዳይቆራረጡ፤ የአየር ሰዓት በሁሉግራም ይግዙ!
አሁን ሁሉግራምን ተጠቅመው ካርድ መግዛት ይችላሉ። እንዲሁም ቻት እያደረጉት ላሉት ወዳጆ በቀላሉ ካርድ ማጋራት ይችላሉ።
አዲሱን ሁሉግራም ዛሬውኑ በማውረድ ተጠቃሚ ይሁኑ። ሁሉም በሁሉግራም ይቻላል!
Download Hulugram SuperApp 👇
https://play.google.com/store/apps/details?id=plus.ride.huluchat
ተጨማሪ 10% ስጦታ ያግኙ! ከሚወዷቸው ለአፍታም ቢሆን እንዳይቆራረጡ፤ የአየር ሰዓት በሁሉግራም ይግዙ!
አሁን ሁሉግራምን ተጠቅመው ካርድ መግዛት ይችላሉ። እንዲሁም ቻት እያደረጉት ላሉት ወዳጆ በቀላሉ ካርድ ማጋራት ይችላሉ።
አዲሱን ሁሉግራም ዛሬውኑ በማውረድ ተጠቃሚ ይሁኑ። ሁሉም በሁሉግራም ይቻላል!
Download Hulugram SuperApp 👇
https://play.google.com/store/apps/details?id=plus.ride.huluchat
#የሹመት_መረጃዎች ፦
1. አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው መሾማቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ አሳውቋል። በአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ ቋሚ መልክተኛ የነበሩት አምባሳደር ተስፋዬ እንግሊዝን ጨምሮ በተለያዩ ሀገራት የኢትዮጵያ አምባሳደር በመሆን ሀገራቸውን ያገለገሉ ነባር ዲፕሎማት ናቸው።
2. የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 6ዙር፣ 1ኛ ዓመት፣ 12ኛ መደበኛ ጉባዔው በጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የቀረቡለትን የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር እና ምክትል ዋና ኦዲተር ሹመቶችን በሙሉ ድምፅ አጽድቋል። በዚሁ መሰረት ወ/ሮ መሠረት ዳምጤ ጫንያለው የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር፤ አቶ አበራ ታደሰ ኢቲቻ ደግሞ የመ/ ቤቱ ምክትል ዋና ኦዲተር ሆነው ተሾመዋል።
@tikvahethiopia
1. አምባሳደር ተስፋዬ ይልማ የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው መሾማቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ አሳውቋል። በአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ ቋሚ መልክተኛ የነበሩት አምባሳደር ተስፋዬ እንግሊዝን ጨምሮ በተለያዩ ሀገራት የኢትዮጵያ አምባሳደር በመሆን ሀገራቸውን ያገለገሉ ነባር ዲፕሎማት ናቸው።
2. የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 6ዙር፣ 1ኛ ዓመት፣ 12ኛ መደበኛ ጉባዔው በጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የቀረቡለትን የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር እና ምክትል ዋና ኦዲተር ሹመቶችን በሙሉ ድምፅ አጽድቋል። በዚሁ መሰረት ወ/ሮ መሠረት ዳምጤ ጫንያለው የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር፤ አቶ አበራ ታደሰ ኢቲቻ ደግሞ የመ/ ቤቱ ምክትል ዋና ኦዲተር ሆነው ተሾመዋል።
@tikvahethiopia
#ETHIOPIA
በሃገራችን የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የቁርዓን እና የአዛን ውድድር የፊታችን እሁድ ይካሄዳል !
በመጪው እሁድ ሰኔ 5/2014 በአዲስ አበባ ስቲዲዮም ለሚካሄደው ዓለም አቀፍ የቁርዓን እና የአዛን ውድድር በርካታ እንግዶች እየገቡ ይገኛሉ።
ሀገራችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚያስጠራው ይህ ውድድር ከ56 በላይ ሀገራት የሚወዳደሩበት ሲሆን ለውድድሩ ከፍተኛ ዝግጅት ሲካሄድ ቆይቷል ።
ውድድሩን በዘይድ እብን ሳቢት የቁርአን ማህበር አዘጋጅነትና በአገሪቱ ከሚገኙ የተለያዩ የመንግስት ተቋማት እንዲሁም ታላላቅ ድርጅቶች ጋር በመተባበር የሚካሄድ ነው።
ውድድሩ በሦሥት ዘርፎች የሚካሄድ ሲሆን በአዛን በቁርአን ሒፍዝና በ30ጁዝዕ የድምጽ ውድድር ይካሔዳል።
እስካሁን ድረስ ባለው መረጃም ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተወዳዳሪዎች ዳኞች እንዲሁም ታዳሚዎች እንደገቡና እየገቡ መሆኑን ተገልጿል።
በዚህ ታላቅ ፕሮግራም ላይ ሁላችንም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ስታድየም በመገኘት የሃገራችንን ስም ከፍ አድርገን ለአለም ልናስተዋውቅ ይገባል።
ለበለጠ መረጃ
በዚህ ይደውሉ
0911755245
0911723051
#ኡስታዝ_አቡበከር_አህመድ
@tikvahethiopia
በሃገራችን የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የቁርዓን እና የአዛን ውድድር የፊታችን እሁድ ይካሄዳል !
በመጪው እሁድ ሰኔ 5/2014 በአዲስ አበባ ስቲዲዮም ለሚካሄደው ዓለም አቀፍ የቁርዓን እና የአዛን ውድድር በርካታ እንግዶች እየገቡ ይገኛሉ።
ሀገራችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚያስጠራው ይህ ውድድር ከ56 በላይ ሀገራት የሚወዳደሩበት ሲሆን ለውድድሩ ከፍተኛ ዝግጅት ሲካሄድ ቆይቷል ።
ውድድሩን በዘይድ እብን ሳቢት የቁርአን ማህበር አዘጋጅነትና በአገሪቱ ከሚገኙ የተለያዩ የመንግስት ተቋማት እንዲሁም ታላላቅ ድርጅቶች ጋር በመተባበር የሚካሄድ ነው።
ውድድሩ በሦሥት ዘርፎች የሚካሄድ ሲሆን በአዛን በቁርአን ሒፍዝና በ30ጁዝዕ የድምጽ ውድድር ይካሔዳል።
እስካሁን ድረስ ባለው መረጃም ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተወዳዳሪዎች ዳኞች እንዲሁም ታዳሚዎች እንደገቡና እየገቡ መሆኑን ተገልጿል።
በዚህ ታላቅ ፕሮግራም ላይ ሁላችንም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ስታድየም በመገኘት የሃገራችንን ስም ከፍ አድርገን ለአለም ልናስተዋውቅ ይገባል።
ለበለጠ መረጃ
በዚህ ይደውሉ
0911755245
0911723051
#ኡስታዝ_አቡበከር_አህመድ
@tikvahethiopia
#ወላጆች_ለልጆች_ጥንቃቄ_እንዲያደርጉ_አሳስቧቸው !
ትናንትና በአዲስ አበባ ከተማ በጣለው ዝናብ አንድ ተማሪ በጎርፍ እንደተወሰደ ተሰምቷል።
የአዲስ አባባ እሳትና ድንገተኛ አደጋ የኮሙኒኬሽን ተማሪው በጉለሌ ክፍለ ከተማ በሚገኘው ላዛሪስት የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ትምህርት ቤት ተማሪ መሆኑን አመልክቷል።
ተማሪው በጎርፍ የተወሰደው ትላንት 9 ሠዓት አካባቢ በጣለው ዝናብ መሆኑን የገለፀው ኮሚኒኬሽኑ በጎርፉ የተወሰደው ተማሪ በትምህርት መውጫ ሠዓት ላይ ከትንሽ ወንድሙ ጋር ወደ ቤት እየሄዱ እንደነበርም አስረድቷል።
እስከዛሬ ጠዋት የእሳትና ድንገተኛ አደጋ ሠራተኞቹ ከኅብረተስቡ ጋር በመሆን ተማሪውን የመፈለጉን ሥራ ቀጥለዋል ተብሏል፡፡
ወላጆች በክረምቱ ልጆቻቸውን ወደ ት/ቤት ሲልኩ ሆነ ሲቀበሉ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉላቸው የእሳትና ድንገተኛ አደጋ ማሳሰቡን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
ትናንትና በአዲስ አበባ ከተማ በጣለው ዝናብ አንድ ተማሪ በጎርፍ እንደተወሰደ ተሰምቷል።
የአዲስ አባባ እሳትና ድንገተኛ አደጋ የኮሙኒኬሽን ተማሪው በጉለሌ ክፍለ ከተማ በሚገኘው ላዛሪስት የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ትምህርት ቤት ተማሪ መሆኑን አመልክቷል።
ተማሪው በጎርፍ የተወሰደው ትላንት 9 ሠዓት አካባቢ በጣለው ዝናብ መሆኑን የገለፀው ኮሚኒኬሽኑ በጎርፉ የተወሰደው ተማሪ በትምህርት መውጫ ሠዓት ላይ ከትንሽ ወንድሙ ጋር ወደ ቤት እየሄዱ እንደነበርም አስረድቷል።
እስከዛሬ ጠዋት የእሳትና ድንገተኛ አደጋ ሠራተኞቹ ከኅብረተስቡ ጋር በመሆን ተማሪውን የመፈለጉን ሥራ ቀጥለዋል ተብሏል፡፡
ወላጆች በክረምቱ ልጆቻቸውን ወደ ት/ቤት ሲልኩ ሆነ ሲቀበሉ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉላቸው የእሳትና ድንገተኛ አደጋ ማሳሰቡን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia