TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.7K photos
1.52K videos
215 files
4.15K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
ፎቶ⬆️አትሌት #ፈይሳ_ሌሊሳ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ከፍተ ኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ አትሌቶች እና ታዋቂ ሰዎች አቀባበል አድርገውለታል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሳዛኝ ዜና‼️አንጋፋው የኦሮሚኛ መሰንቆ ተጫዋች ጋሽ ለገሰ አብዲ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጅንካ⬇️

የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን በ60 ሚሊየን ብር ወጪ በጅንካ ከተማ ያስገነባው የከረጢት ፋብሪካ የምርት ስራው #ቆሟል

5 የኦሞ ኩራዝ ስኳር ፕሮጀክቶች በደቡብ ኦሞ ዞን መገንባታቸውን ተከትሎ በጂንካ ከተማ በ18 ነጥብ 2 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የከረጢት ፋብሪካው "ኮርፖሬት ኒው ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት” በተሰኘ ተቋም ግንባታው ተጠናቆ የሙከራ ምርት ማምረት ችሎ ነበር።

ሆኖም ፋብሪካውን የሚያስተዳድረው የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን አምርቶ መሸጥ ለሚችል 3ኛ ወገን ሳያስተላልፍ በመቆየቱና ለሙከራ የቀረበው ግብዓትም በማለቁ አሁን ፋብሪካው ምርት ማቆሙን fbc በስፍራው ባደረገው ቅኝት #አረጋግጧል

የጅንካ ከረጢት ፋብሪካ በሙከራ ወቅት ከ400 ሺህ በላይ ከረጢት ያመረተ ሲሆን፥ ፍብሪካው ለሚመለከተው አካል አለመተላለፉን ተከትሎ የገበያ ትስስር ሊፈጠርለት አልቻለም።

ከዚህ ባሻገርም ፋብሪካው በራሱ በብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የውስጥ ስምምነት መሰረት 130 ሰራተኞችን ቀጥሮ እንዲንቀሳቀስ ሲያደርግ ቢቆይም፤ በተጠቀሱት ምክንያቶች ስራ እንዲያቆም ሲደረግ 89 ሰራተኞች ከስራ እንዲሰናበቱ መደረጉ እና በበረሃ አበል ክፍያ ላይ ችግሮች መኖራቸው ቅሬታ እንዲፈጠር አድርጓል።

የጅንካ ከረጢት ፋብሪካ ዋና ስራ አስኪያጅ ሺህ አለቃ ቀረብህ ህብስቱ እንደተናገሩት፤ ፋብሪካውን ተረክቦ ምርት እያመረተ መሸጥ ለሚችል አካል ለማስተላለፍ እና የሙከራ ምርቶቹንም ለመሸጥ የጨረታ ማስታወቂያ ወጥቶ ክትትል እየተደረገ ነው።

የፋብሪካው የሰው ሃይል አስተዳደር አና ልማት ሃላፊው ሺህ አለቃ ማጆር ተሰማ በበኩላቸው ከስራ ገበታቸው የተሰናበቱ ሰራተኞች ፍብሪካው እስኪተላለፍ ድረስም ቢሆን እንዲመለሱ እና የክፍያ ቅሬታቸውም ውይይት እንዲደረግበት መወሰኑን ገልፀዋል።

የጅንካ ከረጢት ፋብሪካ በሙሉ አቅሙ መስራት ሲጀምር በአመት 30 ሚሊየን ከረጢት የማምረት አቅም ያለው ሲሆን በሙከራ ወቅት በቀን ከ1 መቶ ሺህ በላይ ከረጢት የማምረት ብቃት እንዳለው ተረጋግጧል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ አሴት (ካፒታል) ያስመዘገቡ ባለሀብቶች በደብረ ማርቆስ ኢንዱስትሪ ፓርክ #ሊሰማሩ ነው፡፡ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን #ደብረ_ማርቆስ ቅርንጫፍ ጽ.ቤት ለ12 ባለሀብቶች ቦታ፣ ካርታና የቦታ ፕላን ማዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Audio
ኢንጂነር አይሻ ከVOA ጋር ያደረጉት ቆይታ‼️
ኢንጂነር አይሻ⬆️ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #አብይ_አሕመድ ባዋቀሩት አዲስ የካቢኔ አባላት ውስጥ #የመከላከያ_ሚኒስቴር ሚኒስትር የሆኑት ኢንጂነር አይሻ መሐመድ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ አንደኛና ሁለተኛ የሚባል ዜጋ የለም "ኢትዮጵያ ለሁሉም #እኩል የሆነች አገር ናት" ብለዋል። ይህ ደግሞ ለፖለቲካ ፍጆታ ብቻ መዋል እንደሌለበት ገልፀው፤ "ፖለቲከኛም፣ ጤነኛም ሆነ በሽተኛ መሆን የሚቻለው #አገር ስትኖር ነው" ብለዋል።

በየትኛውም ደረጃ ያለ ማንኛውም የመንግሥት አመራር ላይ ያለ ሰው ገለልተኛ መሆን እንዳለበት የተናገሩት ወ/ሮ አይሻ፤ "ይህን ደግሞ በሚያንፀባርቁት ሐሳብም በድርጊትም ማሳየት ይገባቸዋል።"ብለዋል።

ምንጭ፦ VOA አማርኛው አገልግሎት(ፂዮን ግርማ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አብን በአማራ ክልል 8 ከተሞች ህዝባዊ ውይይት እያካሄደ ነው፡፡
ውይይቱን፡-

1. በሚዳ ወረሞ (ሜንሽን አዳራሽ)
2. በምንጃር ሸንኮራ (አረርቲ)
3. በመካነ ሰላም (ቦረና)
4. በወረኢሉ
5. በመቅደላ (ማሻ ከተማ)
6. በቋሪት (ገበዘማሪያም)
7. በይልማና ዴንሳ (አዴት)
8. በበየዳ (ድልይብዛ) እያካሄደ ነው፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ራያ እና አላማጣ⬇️

"ሰላም ፅግሽ ራያ እና አላማጣ ጠዋት አካባቢ ተኩስ እና ሰላማዊ ሰልፍ እንደነበር አላማጣ ያል ቅርብ የስራ ባልደረባዬ ነግሮኛል አሁን ትንሽ #ተረጋግቶ ህዝቡና ፌደራሉ ተፋጦ ነው ያለው የንግድ ቤቶችም ተዘግተዋል።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update የከፍተኛ አመራሮች ስልጠና⬆️

2ኛው ቀኑን የያዘው የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች #ስልጠና እንደቀጠለ ነው።

በዛሬው ዕለት:-

* ለህዝብ ቅርብ መሆንና በሚረዳው ቋንቅ ማናገር (How to be closer to the people and address them effectively in their setting?)

* ልህቀትን የሚያመጣ የአመራር ክህሎት (Leadership for Excellence)

* ፕሮቶኮል፣ የጊዜ አጠቃቀም እና ተያያዥ ጉዳዮች (Protocol, Etiquette and Time management)

* ውጤታማ የንግግር ክህሎት (Effective Public Speaking) በሚሉ ርዕሶች በአገር ውስጥ እና በውጭ -ባለሙያዎች ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

ስልጠናውና ውይይቱ በዛሬው ዕለት #እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል፡፡

ምንጭ፡- ጠ/ሚ ጽ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል⬆️በቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከአንድ የ33 ዓመት ወጣት በቀዶ ህክምና 122 ሚስማሮች፣ አንድ መርፌ ቁልፍ፣ ሁለት መርፌ፣ ሁለት ስትኪና ሁለት ስባሪ ብርጭቆዎች #መውጣታቸው ተገለፀ።

ለ10 ዓመታት የአዕምሮ ህመምተኛ የነበረ ወጣቱ ለስምንት ዓመታት መድሃኒት እየወሰደ መቆየቱ ተነግሯል።

በኋላም መድሃኒቱን በመቋረጥ ለሁለት ዓመት ፀበል ሲከታተል መቆየቱን  ቤተሰቦቹ አስታውቀዋል።

በቅርቡ ግን የወጣቱ ሆድ በማበጡና በአጋጠመው ህመም  ምክንያት ወደ ሆስፒታሉ አቅንቷል።

በዚህ  ወቅት በዶክተሮች በተደረገ ምርመራ ባልተለመደ ሁኔታ በሆዱ ውስጥ ሚስማሮችን  አግኝተዋል።

2 ሰዓት 30 ደቂቃ በፈጀው የቆዶ ህክምና  122 ሚስማሮች፣ አንድ መርፌ ቁልፍ፣ ሁለት መርፌ፣ ሁለት ስትኪና ሁለት ስባሪ ብርጭቆዎችን አውጥተዋል።

ቆዶ ህክምናውን የመሩት  የሆስፒታሉ የቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ዳዊት ተአረ  እንደገለፁት፥ ቀዶ ህክምናው በተሳካ ሁኔታ ተጠናቆ ወጣቱ በአሁን ወቅት በጥሩ ሁኔታ በማገገሚያ ክፍል ውስጥ ይገኛል።

ምንጭ፦ ፋና
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ራያ አላማጣ⬇️

የራያ አላማጣ የማንነት ጥያቄ #ሊታፈን እንደማይገባ የቆቦ ከተማ ነዋሪዎች ጠየቁ።

የራያ አላማጣ ነዋሪዎች ማንነታችን አማራ በመሆኑ ሊከበርልን ይገባል ሲሉ በተደጋጋሚ እየጠየቁ ይገኛሉ። ይሁን እንጂ እንግልት እና ወከባ እየደረሰባቸው መሆኑን ነው የሚናገሩት። አላማጣ ላይ ከትናንት ምሽት ጀምሮ የፀጥታ ችግር መኖሩንና #ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች መኖራቸውንም ከአካባቢው የዓይን እማኞች ተናግረዋል።

ስለ ጉዳዩ የጠየቅናቸው የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ በአካባቢው ስለሌሉ መረጃ መስጠት እንደማይችሉ ነው የተናገሩት።

የቆቦ ከተማ ነዋሪዎችም ዛሬ በሰላማዊ ሰልፍ ድርጊቱን አውግዘዋል። "ማንነታቸውን ስለጠየቁ መብታቸው ሊታፈን፣ ሊንገላቱ እና ሊዋከቡ አይገባም" ሲሉ ነው የጠየቁት።

ከዚህ በፊት ስለ ጉዳዩ የተጠየቀው የትግራይ ክልል መንግስት "ጥያቄው ከማንነት ጋር አይያያዝም" ማለቱ ይታወሳል።

ነዋሪዎቹ ግን ጥያቄያቸው የማንነት እና የነፃነት መሆኑን ነው የሚያስረዱት። በሰልፉ "ጣናና ላል ይበላን እንታደግ!" የሚሉ መልዕክቶችንም አስተላልፈዋል።

የሰሞኑን የሚኒስትሮች ሹመት አሰጣጥም ተቃውመዋል።

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከሳሪስ አቦ⬆️

"ሰላም ፀግሽ! ዛሬ ሳሪስ አቦ ሚባለው ሠፈር ቀለበት መንገድ የ ትራፊክ መብራቱ ጋር የትራፊክ አደጋ ደርሷል፡፡ በ አደጋው ከ 8 ሚበልጡ ሚኪኖች የተጋጩ ሲሆን ፤ 4ቱ ግን ክፋኛ ተጎድተዋል፡፡ እንደውም አንድ ዶልፊን መኪና የመኪኖቹ ጣሪያ ላይ ወጥቶ አይቻለው፡፡ እዛ አካባቢ የነበሩ ሠዎችን ጠይቄ ፤ በ አደጋው ያለፈ ሂወት እንደሌለ ነግረውኛል፡፡ AK ነኝ ከአዲስ አበባ"

@tsegabwolde @tikvahethiopia