TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
EBC & FANA Live!

"መደመር #ለኢትዮጵያ ከተሞች ብልፅግና" የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም #የመክፈቻ ስነ ስርዓትን ከጅግጅጋ በቀጥታ #መከታተል ትችላላችሁ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#JIGJIGA

”ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የተበረከተው ሽልማት #ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተሰጠ ትልቅ ክብር ነው” ሲሉ የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሃመድ ዑመር ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ ሽልማት በማግኘታቸው ”የእንኳን ደስ አልዎ!” ሰልፍ በጅግጅጋ ስታዲዬም ዛሬ ተካሂዷል። ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት “ሰዎች 50 ዓመታት ስልጣን ላይ ቆይተው የማያገኙትን ዓለም አቀፍ ሽልማት ክብር ጠቅላይ ሚኒስትራችን በማግኘታቸው እጅግ ተደስቻለሁ” ብለዋል።

Via ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#Tigray

በመከላከያ የሰራዊት ግንባታ ስራዎች ዋና አስተባባሪ ሌ/ጄነራል ባጫ ደበሌ ዛሬ በቴሌቪዥን ቀርበው ባደረጉት ገለፃ የፌዴራሉ መንግስት በትግራይ ላይ ያወጀውን የተናጠል የተኩስ አቁም እርምጃ ህወሓት እንደአጋጣሚ ተጠቅሞ ትንኮሳ እየፈፀመ ነው ብለዋል።

ሌ/ጄነራል ባጫ ደበሌ ህወሓት የተኩስ አቁሙን እንደአጋጣሚ ተጠቅሞ ለጥበቃ፣ ለሳተላይት አሃዱዎች፣ የክልል የፀጥታ ኃይሎችን ለማጥቃት እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

"ኮረም እና አላማጣ ቀድሞውንም ሰራዊት አልነበረንም ... ነገር ግን በራያ አካባቢ አነስተኛ ኃይል ማስቀመጥ ነበረብን ፤ በተጨማሪ የአካባቢ ኃይሎችን ማስቀመጥ ነበረብን ህወሓት የተኩስ አቁሙን እንደአጋጣሚ ተጠቅሞ እኛ መቋቋም ሳናደርግ እናጠቃለን በሚል ኃይላችንን አጥቆት ለመደምሰስ ሞክሯል" ብለዋል።

የታወጀው የተናጠል ተኩስ አቁም ለሰብዓዊ ድጋፍ እና የትግራይ ገበሬዎች የግብርና ስራቸውን በነፃነት እንዲሰሩ ታሳቢ በማድረግ የታወጀ መኖሩን አስታውሰው "ህወሓት" ግጭትን መፍጠር መሰረታዊ ባህሪው በመሆኑ ውሳኔውን አልተቀበለም ሲሉ ገልፀዋል።

ሌተናል ጄኔራሉ ፤ ወታደራዊ ስራ በወታደሮች የሚሰራ እንጂ #በአክቲቪስቶች የሚሰራ አይደለም ያሉ ሲሆን አሁን የተፈፀመ ላለው ትንኮሳ መከላከያው የት መስፈር እና እንዴት በሙሉ አቅሙ ጥቃት መፈፀም እንዳለበት ውሳኔ ተወስኖ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

"እየተዋጋን ያለነው #ለኢትዮጵያ_ድንበር ነው ፤ የኛ ድንበር #መረብ ነው" ሲሉ የተደመጡት ሌ/ጄነራል ባጫ የመረብ ድንበር ድረስ ኢትዮጵያን ለመበጣጠስ የሚፈልገውን ኃይል የማይቻል መሆኑን ማሳየት ነው ሲሉ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
#ለኢትዮጵያ

የፊታችን ጥር 1 ከቀኑ 9:00 ላይ በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ " ለኢትዮጵያ " በሚል የምልጃና የአምልኮ ጊዜ መዘጋጀቱ ተገለፀ።

ፕሮግራሙ የተዘጋጀው በዘጸአት አፖስቶሊክ ሪፎርሜሽን ቤተክርስቲያን ሲሆን ስለኢትዮጵያ የጸሎት እና አምልኮ ጊዜ እንደሚሆን ቤተክርስትያኗ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቃለች።

በዕለቱ በጦርነቱ ለተጎዱ ወገኖቻችን የገቢ ማሰባሰቢያ እንደሚደረግ ተገልጿል።

ከደህንነት አንፃር ከመንግስት ጋር አስፈላጊው ሁሉ ዝግጅት መጠናቀቁና ምንም አይነት የሚያሰጋ ነገር ባለመኖሩ ከአዲስ አበባ ሆነ ከአዲስ አበባ ውጭ ያሉ እንዲታደሙ ጥሪ ቀርቧል።

ዝግጅቱ የኮቪድ-19 ጥንቃቄ በሚተገበርበት መልኩ እንደሚሆንም ተነግሯል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የባሕር በር ጉዳይ የቅንጦት ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው " - ኢትዮጵያ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ምን አሉ ? " ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት የቅንጦት ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። ከሶማሌላንድ ጋር የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ ከዓላማው ውጪ የሆኑ የተሳሳቱ መረጃዎች ተሰራጭተዋል። የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የቅንጦት ሳይሆን…
#ኢትዮጵያ🇪🇹

" ... ለሶማሊያ በችግር ጊዜ ብዙ ድጋፍ ያላደረጉ #አንዳንድ_ተዋናዮች ራሳቸውን እንደ እውነተኛ ወዳጆቿ አድርገው ለማሳየት እየሞከሩ ነው " - አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ምን አሉ ?

- ኢትዮጵያ ለሶማሊያ #ሰላም እና #ደህንነት ያላትን ቁርጠኝነት በውድ ልጆቿ #ደም እና #ላብ በግልፅ አሳይታለች።

- ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ድንበር ተጋርተው የሚኖሩ ጎረቤቶች ብቻ ሳይሆኑ የጋራ የሆነ ቋንቋ፣ ባህል እና ህዝብ የሚጋሩ ወንድማማች ሀገራት ናቸው።

- ኢትዮጵያ እና ሶማሊያን የሚያስተሳስሩ ጉዳዮች ጠንካራ ናቸው ፤ እጣ ፈንታችን የማይነጣጠል ነው።

- ከሶማሌላንድ ጋር የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ለኢትዮጵያ የንግድ ግንኙነት የሚሆን የባህር አገልግሎት የሚሰጥ የትብብር እና አጋርነት ስምምነት ነው። ስምምነቱ በየትኛውም ሀገር ላይ ሉዓላዊነትን የሚጥስ / የሚገዳደር / በግዳጅ የየትኛውንም ሀገር ሉዓላዊነት የሚረግጥ አይደለም።

- እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ለሶማሊያ በችግር ጊዜ ብዙ ድጋፍ ያላደረጉ አንዳንድ ተዋናዮች ራሳቸውን እንደ እውነተኛ ወዳጆቿ ለማሳየት እየሞከሩ ነው። ለዚህ ደግሞ ያነሳሳቸው ለሶማሊያ ያላቸው ወዳጅነት ሳይሆን #ለኢትዮጵያ_ያላቸው_ጥላቻ / የጠላትነት ስሜት መሆኑ ግልጽ ነው።

- እነዚህ ተዋናዮች አጀንዳቸው የአፍሪካ ቀንድ ሰላም ፣ መረጋጋት እና ደህንነት አይደለም። ሊዘሩ የፈለጉት #አለመግባባት እና #ትርምስን ነው። እየታየ ያለው ነገር ውጥረት የሚያባብስ እንዲሁም ደግሞ አጋጣሚውን ለመጠቀም ለሚፈልጉ የውጭ ተዋናዮች ፍላጎት ብቻ የሚያገለግል ነው።

- ኢትዮጵያ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመስረተ ሁሉን አቀፍ ቀጠናዊ ትስስርን ለመፍጠር ከሁሉም ጎረቤቶቿ ጋር በትብብር መንፈስ ለመስራት እየጣረች ነው።

- ኢትዮጵያ ውጥረትን ከሚፈጥሩና ከሚያባብሱ መግለጫዎች፣ ንግግሮች እና ትርክቶች ይልቅ ቀጣይነት ያለው ውይይት ማድረግ የተሻለ አማራጭ እንደሆነ በጽኑ ታምናለች።

#AmbassadorRedwanHussien #X

@tikvahethiopia
የካራማራ ድል !

የካቲት 26/1970 ዓ/ም የሱማሊያን ዚያድባሬ ጦር ለመመከት በካራማራ ጀግኖች የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች የህይወት መሰዋዕትነት ከፍለው ወራሪውን ጦር ከሀገር ያባረሩበት እና የሀገራቸውን ሰንደቅ ያውለበለቡበት ቀን ነው።

በሶቪየት ህብረት ከፍተኛ የሆነ ድጋፍ የመጣው የዚአድባሪ ጦር የእናት ሀገር ጥሪ እያለ በተሰበሰበው የኢትዮጵያ ጦረኛ "  ካራማራ " ላይ ድባቅ ተመትቶ ወደ መጣበት ተመልሷል።

በጦርነቱ መጀመሪያ ሶቪየት ህብረት ሶማሊያን ስትደግፍ ነበር በኃላ ላይ ወደ ኢትዮጵያ አዘንብላ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ እገዛ አድርጋለች ፤ ከኢትዮጵያ ጋር ጥሩ ግንኙነት የነበራት አሜሪካ ደግሞ ወደ ሶማሊያ ፊቷን አዙራ ነበር።

በጦርነቱ ኩባ፣ ሰሜን ኮሪያ፣ የመን እና ምሥራቅ ጀርመንን ጨምሮ ሌሎች አገራት አጋርነታቸውን ለኢትዮጵያ አሳይተዋል።

ከ16,000 በላይ የኩባ ወታደሮች በውጊያው እንደተሳተፉ መዛግብት ያሳያሉ። ደቡብ የመንም ጦሯን #ለኢትዮጵያ አሰልፋ ነበር።

በተለያየ የፖለቲካ የትግል ሁኔታ፣ በተለያየ ቅራኔ ውስጥ የነበሩ የኢትዮጵያ ሀይሎች ሁሉ ስለ ሀገር አንድ ሆነው የዚያድባሬን ጦር የመከቱበት የካራማራ ጦርነት የኢትዮጵያ አንድነት ዳግም በጉልህ የታየበት ስለመሆኑ ይነገርለታል፡፡

በየአመቱ የካቲት 26 ቀን የሚታሰበው የ " ካራማራ ድል " ዘንድሮም ለ46ኛ ጊዜ እየታሰበ ይገኛል፡፡

@tikvahethiopia