TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
ሀዋሳ ለምትገኙ...

COLORS FOR UNITY #በሀይሌ_ሪዞርት ነገ!

መግቢያ፦

•vip 100 ብር
•መደበኛ 50 ብር

ዋና አዘጋጇን ፍፁም(ሮዳስ) በ +251934985001 ደውለው ያግኙ!!
#update ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ ዛሬ ከሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ #ሙስጠፋ_ኡመርና የኢትዮጲያ ሶማሌ ክልል ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ #አህምድ_ሽዴ ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል። ዉይይቱም የተኮረው በሶማሌ ክልል ልማትና ጸጥታ ጉዳዮች ላይ ሲሄን ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድም የክልሉን ልማት የበለጠ #በማጠናከር ረገድ አቅጣጫ ሰጥተዋል።

#PMOffice
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአገር መከላከያ ሰራዊት‼️

የአገር መከላከያ ሰራዊት አባላት የመለያ ደንብ ልብስ የቀለምና የዲዛይን ለውጥ ሊደረግበት መሆኑን የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ሜጀር ጀኔራል #አብዱራህማን_እስማኤል ገለጹ።

የመከላከያ ሰራዊቱን የመለያ ደንብ ልብስ በመልበስ በሰራዊቱ ስም #ወንጀል የሚፈፅሙ አካላትን #ለመቆጣጠር ያስችላልም ተብሏል።

የመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ሜጀር ጀነራል አብዱራህማን እስማኤል ለኢዜአ እንዳሉት፤ የመከላከያ ሰራዊቱን የመለያ ደንብ ልብስ ጥራትና ደረጃውን በጠበቀ የቀለምና ዲዛይን ለውጥ ሊደረግበት ነው።

ፋውንዴሽኑ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 179/2002 በተሰጠው ስልጣን መሰረት ለሰራዊቱ አልባሳትና ሌሎች ወታደራዊ ግብዓቶችን በማምረት ወይም ገዝቶ ያቀርባል ብለዋል።

የመከላከያ ሰራዊት አባላት የሚወዱት፣ በጥራት፣ በቀለምና በዲዛይን የተሻለ የመለያ ልብስ እንዲሆን ከተለያዩ አገሮች ተመክሮ መወሰዱን ገልጸዋል።

የመከላከያ ጥናትና ምርምር ማዕከል ሃላፊ ብርጋዴር ጀኔራል #ተሾመ_ገመቹ በበኩላቸው የመከላከያ ሰራዊቱን አልባሳት መልበስ የሚችለው የሰራዊቱ አባል ብቻ ቢሆንም ተገቢ ቁጥጥር ባለመደረጉ የማይመለከታቸው ግለሰቦች ለብሰውት ተስተውሏል።

አዳዲስ አልባሳት በሚቀርቡበት ወቅት አሮጌዎቹ በአግባቡ ሳይወገዱ በመቅረታቸው ልብሱ በማይመለከታቸው አካላት እጅ ገብቶ የሰራዊቱን ስምና ክብር የሚያጎድፉ የተለያዩ ወንጀሎች እየተፈጸሙበት መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም በቀጣይ በሰራዊቱ አልባሳት ላይ የሚደረገው የቀለም ለውጥ እንዲሁም አዲስ አልባሳት ሲሰጥ ችግሩን ለመፍታት የሚያስቸሉ እርምጃዎች እንደሚወሰዱ ነው ያመለከቱት።

የመከላከያ ሰራዊቱን የመለያ ደንብ ልብስ በመልበስ ወንጀል የሚፈጽሙ አካላት ካሉ በወንጀል እንደሚጠየቁ ተናግረዋል።

ኅብረተሰቡም የመከላከያ ሰራዊቱን የመለያ ደንብ ልብስ መልበስ የሚችለው ሰራዊቱ ብቻ መሆኑን ተረድቶ የማይገባውን ልብስ ባለመልበስ ወንጀል እንዳይፈጸም ሊተባበር እንደሚገባ አሳስበዋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ድሬደዋ‼️

በድሬዳዋ የተከሰተውን የጸጥታ መደፍረስ ለመቆጣጠር የመከላከያ ሰራዊት የጸጥታ ማስከበር ኃላፊነቱን ሙሉ በሙሉ እንዲረከብ መደረጉን የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ። በሰሞኑ ሁከት የተጠረጠሩ 200 ሰዎች #በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ገልጿል።

የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ የመከላከያ ሰራዊት ወደ ድሬዳዋ እንዲገባ የተደረገው ባለፉት ቀናት በከተማይቱ የነበረው ሁኔታ ከአስተዳደሩ እና ከፌደራል ፖሊስ አቅም በላይ ስለነበር ነው።

የመከላከያ ሰራዊት ከተማይቱን ለመቆጣጠር የሚያስችሉትን ኮማንድ ፖስቶች በተለያዩ አካባቢዎች ማቋቁሙንም ጽህፈት ቤቱ ይፋ አድርጓል።

የጀርመን ራድዮ የድሬዳዋ ዘጋቢ #መሳይ_ተክሉ እንደገለጸው የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከትላንት ምሽት ጀምሮ በከተማይቱ ተሰማርተዋል። በመኪና ላይ ሆነው ከሚዘዋወሩት በተጨማሪ በየአካባቢው በተጠንቀቅ ቆመው የሚታዩ እንዳሉ ዘጋቢው ተናግሯል። የሰራዊቱ አባላት ለአደጋ ይጋለጣሉ ለተባሉ የመንግስት ተቋማት እና ድርጅቶችም #ጥበቃ እያደረጉ ነው ብሏል።

በከተማይቱ ያለው ዘጋቢያችን የመንግስት ወታደሮቹ ህገወጥ እንቅስቃሴዎች በሚያደርጉ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወስዱ በድምጽ ማጉያ ሲያስጠንቅቁ ተመልክቷል። በድሬዳዋ ሰሞኑን ሲደረጉ የነበሩ የህዝቡን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴዎች ከሚያውኩ ድርጊቶች እንዲታቀቡም ተቃዋሚዎችን ሲያስቡም ታዝቧል።

በድሬዳዋ ላለፉት ሶስት ቀናት ተቃውሟቸውን ለማሰማት አደባባይ የወጡ ነዋሪዎች ጎማዎች በማቃጠል እና ድንጋይ በመደርደር መንገዶችን ዘግተው ነበር። በዛሬው ዕለት በከተማይቱ እንቅስቃሴዎች እንደሚታዩ የገለጸው ዘጋቢያችን መንገዶች መከፈታቸውን እና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ወደ ስራ መመለሳቸውን ተናግሯል።

በድሬዳዋ ከሰሞኑ በተከሰተው ሁከት ምክንያት በሰው እና በንብረት ላይ ስለደረሰው ጉዳት የተጠየቁት የከተማይቱ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት እና ፖሊስ “የተደራጀ መረጃ የለም” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ምንጭ:- DW AMHARIC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ‼️

ጥር 17 አፄ #ቴዎድሮስ_ግቢ በ6 የተማሪ መኖሪያ ህንፃዎች በተደረገ #ድንገተኛ ፍተሻ፦

•395 ያልታደሰ፣ ሃሰተኛ እና ፎቶ የሌለው መታወቂያ ተይዟል።

•ከተማሪ መኖሪያ ክፍሎች ጩቤ፣ ድንጋይ፣ ብረት እና ዱላ ተገኝቷል።

•አንድ ተማሪ 9 ሲም ካርድ፤ ሌላ አንድ ተማሪ 7 ሲም ካርድ ይዘው ተገኝተዋል።

•8 ተማሪዎች አካውንት ላይ እያንዳንዳቸው ከ30 ሺ ብር እስከ 86 ሺ ብር ተገኝቷል።

•መታወቂያ ያልያዙ 37 ተማሪዎች ተይዘዋል።

•በቀን ጥር 16/2011 ዓ.ም. 3 ተማሪዎች 4 ጀሪካን ዘይት ጫካ ውስጥ ይዘው እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል፤ 3 ተማሪዎች ሴቶች ህንፃ ሲገቡ ተይዘዋል።

🔹ተጠርጣሪዎች ላይ ተገቢው ማጣራት እየተደረገ ይገኛል፤ በቅርቡ #እርምጃ ተወስዶ #ይፋ ይደረጋል ተብሏል።
.
.
ትምህርት የተቋረጠባቸው አፄ ቴዎድሮስ እና አፄ ፋሲል ግቢዎች ከሰኞ ጥር 20 ጀምሮ ተማሪዎች ትምህርት እንዲጀምሩ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል። ትምህርት የማይጀምሩ ተማሪዎች ግቢውን #ለቀው እንዲወጡ #ጥብቅ_ማሳሰቢያ ተላልፏል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"አብራክ" ተገመገመ‼️

ኢትዮጵያን የሚንጣት #የዘር ፖለቲካን የወከሉ ገፀ ባህሪያት የተወከሉበትና የብሔር ፖለቲካና የብሔር ማንነት ጥልቀት፣ የፖለቲካ ከፋፋይነት ተደርሶበታል የተባለው “አብራክ” የተሰኘ መፅሐፍ ትናንት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተገምግሟል፡፡

Via Sheger FM 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትግራይ ክልል ምክር ቤት‼️

የትግራይ ክልል ምክር ቤት በቅርቡ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፀደቀውን የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ #በመቃወም ውሳኔ አስተላለፈ።

ምክር ቤቱ ውሳኔውን ያስተላለፈው በመቐለ ከተማ እያካሄደ ባለው 5ኛ ዓመት 14 መደበኛ ጉባዔው ነው።

ምክር ቤቱ በውሳኔ ሀሳቡ አዋጁ የፌዴራል መንግስት በክልሎች ጉዳይ ጣልቃ በመግባት የክልላዊ አስተዳደር መብትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት ስልጣንን እንዲጋፋ የሚያደርግ ነው ብሏል።

በተጨማሪም በክልሎች፣ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች መካከል #መጠራጠር እንዲፈጠር የሚያደርግ እንደሆነም ነው ምክር ቤቱ በውሳኔ ሀሳቡ የገለፀው።

ለዚህም ኮሚሽኑ የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች በሕገ መንግስት የተሰጣቸውን ስልጣን ተክቶ የወሰንና የማንነት ጉዳዮችን ለመመልከት መቋቋሙ ስሕተት ነው ሲል በውሳኔ ሀሳቡ አስፍሯል። ምክር ቤቱ በመጨረሻም አዋጁን በመቃወም የተዘጋጀውን የውሳኔ ሀሳብ አፅድቋል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ከትራንስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ እና ከንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/እግዚአብሔር ጋር በመሆን በዛሬው ዕለት በሞጆ ደረቅ ወደብ ተገኝተው 13 አዳዲስ የዕቃ መጫኛና ማውረጃ ( ሪች ስታከር) ማሽኖችን መርቀው ስራ አስጀምረዋል፡፡

Via EPA
@tsegabwolde @tilvahethiopia
ፎቶሾፕ🔝

"አዶቤ ፎቶሾፕ የተመሰረተው #በወንድማማቾቹ #ቶማስ_ኖል እና #ጆን_ኖል እኤአ በ1988 ዓ.ም ነበር። ከዛ ግዜ ጀምሮ ኢትዮጵያውያንን እንዳወዛገበ ይገኛል!"

©ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት(AP)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ስካይ ላይት ሆቴል ነገ ይመረቃል!!

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ60 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ወጪ ያስገነባው #የስካይ_ላይት_ሆቴል በነገው ዕለት ተመርቆ ወደ ሥራ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እኤአ በ2025 በዓለምአቀፍ ደረጃ እጅግ ተወዳዳሪ አየር መንገድ ለማድረግ የሚያደርገውን ጥረት ለማሳካት መሰል የሆቴል ግንባታዎች ሚናቸው ከፍተኛ መሆኑን በአየር መንገዱ የመሠረተ ልማት ክፍል ኃላፊ አቶ አብርሃም ተስፋዬ ለዋልታ ተናግረዋል፡፡

ስካይ ላይት ሆቴል ለሶስት አመታት ያህል የግንባታው ሥራ ሲከናወን የቆየ ሲሆን ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት መሥጠት ሲጀምር የባለ 5 ኮከብ ደረጃን ያገኛል ተብሎ ይጠበቃል። ሆቴሉ በመላው ዓለም የሚገኙ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ትራንዚተሮችን ከማስተናገድ ረገድ ትልቁን ድርሻ እንደሚወጣ ተገልጿል፡፡

ሆቴሉ በአጠቃላይ 373 የማረፊያ ክፍሎች፣ አራት ደረጃቸውን የጠበቁ ሪስቶራንቶች፣ የመዋኛ ገንዳ፣ የአዳራሽ አገልግሎትና ሌሎችም ዘርፈ-ብዙ የሆቴል አገልግሎቶችን በሟሟላት ሀገሪቱ በትኩረት እየሠራች የሚትገኘውን የቱሪዝም ኢንዱስትሪን ይበልጥ እንደሚያግዝም ታምኖበታል፡፡ በነገው ዕለት ተመርቆ ወደ ሥራ የሚገባው ስካይ ላይት ሆቴል የቱሪዝም ኮንፌረንሱን በማገዝም የጎላ አስተዋፅዖ አለው ተብሏል፡፡

ምንጭ፦ ዋልታ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከአዲስ አበባ...

"ጠ/ሚ ዶክተር #አብይ_አህመድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያስገነባውን ሆቴል #ይመርቃሉ፤ እንዲሁም የኢንተርናሽናል ኤርፖርት ተርሚናል ማስፋፊያ ግንባታን ተዘዋውረው ይጎበኛሉ።"

©S(TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሶሪያ ስደተኞች~ሃዋሳ‼️

በአሁኑ ወቅት #በሀዋሳ_ከተማ በልመና ስራ ተሰማርተው የሚገኙ ጥቂት የሶሪያ ዜጎች መኖራቸውን የኢሚግሬሽን የዜግነትና ወሳኝ ኩነቶች ኤጀንሲ አስታውቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ድሬዳዋ አንፃራዊ ሰላም ሰፍኗል‼️

ሰሞኑን #በድሬደዋ_ከተማ የነበረውን ያለመረጋጋት ተከትሎ የመከላከያ ሰራዊት ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት በወሰደው የማረጋጋት ስራ በከተማዋ አንፃራዊ #ሰላም መታየቱን የምስራቅ እዝ አስታወቀ፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia