TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
ለወጣቶች እና ተማሪዎች‼️

ውድ የኢትዮጵያ ልጆች የጥፋት ሀይሎች መጠቀሚያ እንዳትሆኑ ተጠንቀቁ። በተለያዩ ምክንያቶች የትምህርት ተቋማት ውስጥ እጃቸውን ሰደው ሀገሪቷን ዳግም ውጥረት ውስጥ ለመክተት የሚሞክሩ ትንንሽ አሳዎች አሉ እነዚህም በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚለዩ እምነታችን ነው።

ተማሪዎች እና ወጣቶች በሰከነ መንገድ ትምህርታችሁን ትከታተሉ ዘንድ መልዕክታችን እናቀርባለን።

አንዲት ድሀ እና የመጨረሻ ድሀ ሀገር ነው ያለችን የዚህችን ሀገር ታሪክ የምንቀይረው በረባው ባልረባው አዲስ ነገር እየፈጠርን አይደለም።

ሀገር ምትቀየረው በስራ እና በትምህርት ብቻ ነው። ዘላለም አመማችንን የአለም ማፈሪያ ሆነን እንዳንኖር ጠንክረን እንስራ።

የማንም የፖለቲካ ደላላ መጠቀሚያ እንዳትሆኑ! እነሱ ችግር ቢፈጠር ነገ #ፈርጥጠው የሚሄዱበትን መንገድ አመቻችተው ነው እናተን የሚቀሰቅሱት ስለሆነም እኚህን የጥፋት ሀይሎች ከመከተለ ተቆጠቡ።

መንግስት ትልልቆቹ አሳዎች እንደያዘው በየመንደሩ ያሉትን ትንንሽ አሳዎች አድኖ የመያዝ ስራ ላይ መበርታት አለበት።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
የድህነት ታሪካችንን በትምህርት እና በስራ እንቀይር!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Audio
ዶክተር ደብረፅዮን🔝

ኢትዮጵያና ኤርትራ የሚያገናኙ የሑመራ - ኡምሓጀርና የራማ -ዓዲዃላ የመንገድ መስመሮች በቅርብ ግዜ #ተከፍተው የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱ ለማጠናከር ውይይት አመራሮች እያካሄድን ነው አሉ የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በትናንትናው ዕለት ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ:በክልሉ ደቡባዊና ምዕራባዊ ዞኖች ስላካሄዱት ጉብኝት ማብራርያ ሰጥተዋል።

#በትግራይና #አማራ ክልሎች ግንኙነት ለማጠናከር የህዝብ ለህዝብና የአመራሮች ግንኙነት መፍጠር ስራ በአዋሳኝ አከባቢዎች እየተፈፀመ ነው ብለዋል።

ምንጭ፦ የአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶክተር መረራ ጉዲና!!

በኢትዮጵያ የሚፈለገውን ብሄራዊ መግባባት ለማምጣት የታሪክ ሂሳብ ማወራረድ ውስጥ መግባት አያስፈልግም ሲሉ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁሩ ዶክተር #መረራ_ጉዲና ተናገሩ።

”በኢትዮጵያ ብሄራዊ መግባባትና ብሔራዊ እርቅ ለማምጣት ምን መደረግ አለበት?” በሚል ዙሪያ ከተለያዩ የሙያ ዘርፎች የተውጣጡ የኀብረተሰብ ክፍሎች ትናንት ምሽት በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ውይይት አካሂደዋል።

‘ኢምፓውር አፍሪካ’ በተሰኘ ተቋም አዘጋጅነት የተካሄደው ውይይት አዲሲቷን ኢትዮጵያ እንዴት እንፍጠር? መልካም አጋጣሚዎችና ፈተናዎች ምንድን ናቸው? በሚሉ ጉዳዮች ላይ የሀሳብ ልውውጥ ተደርጓል።

ዶክተር መረራ ጉዲና ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት፤ በአገሪቱ ብሄራዊ መግባባትን ለማምጣት በታሪክ የተፈጸሙ ድርጊቶችን ለማወራረድ መሞከር አያስፈልግም።

”ለዘመናት በኢትዮጵያ ሁሉም የሚስማማበት፣ የጋራና ሞዴል ሊሆን የሚችል መሪ አለመኖር ትልቅ ፈተና ሆኖ ቆይቷል” ብለዋል።

አጼ ምኒሊክ በተወሰኑ አካባቢዎች ዘላለማዊ ጀግና ተደረገው ይወሰዳሉ፤ በሌላ አካባቢ ደግሞ ቀኝ ገዥ ተደርገው መታየታቸውን በማሳያነት የጠቀሱት ምሁሩ ብሄራዊ እርቅ ለማምጣት ከዚህ ዓይነት አስተሳሰብ መላቀቅ እንደሚገባ አስረድተዋል።

ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር በኢትዮጵያ የሀሳብ የበላይነት አሸናፊ ሆኖ እንዲወጣ ሁሉም የኀብረተሰብ ክፍል የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግ እንዳለበት ዶክተር መረራ ገልጸዋል።

”በአገሪቱ ታሪክ የነበሩ የሚጋጩ ህልሞችን ይዞ መኳተን የትም አያደርስም” ያሉት ዶክተር መረራ ህልሞቹ በአግባቡ ካልተያዙ ወደለየለት አለመረጋጋት የሚወሰዱ በመሆናቸው ሁሉም የሚጠበቅበትን የቤት ሥራ መስራት እንደሚገባው አመልክተዋል።

ፖለቲከኞች፣ የሐይማኖት መሪዎች፣ አባ ገዳዎችና የአገር ሽማግሌዎች አዲሲቷን ኢትዮጵያን እንዴት እንፍጠር? የሚለውን በጥልቀት ሊሰሩበት ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል።

”መግባባት በሚቻልበት ቋንቋ ምን ያስፈልጋል? የነገዋ ኢትዮጵያ ምን መምሰል አለባት?” በሚሉና መሰል ጉዳዮች ላይ በሰከነ አእምሮ መወያየት እንደሚያስፈልግ ነው ዶክተር መረራ በመነሻ የውይይት ሀሳባቸው አጽንኦት የሰጡት።

”ህዝብ የእኔ መንግሥት ነው” የሚል አስተሳሰብ አለማምጣቱ በአገሪቱ የሚታይ ትልቁ ፈተና መሆኑን የተናገሩት ዶክተር መረራ ”በቀጣይ ህዝቡ የኔ መንግሥት ነው” እንዲል የሚያስችሉ ሥራዎችን መሥራት እንደሚገባም ጠቁመዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ከነበረው የኢትዮጵያ ታሪክ ለምን መማር አልቻልንም? እስከ መቼ ነው በትንንሽ ቁርሾዎች መቃቃሩ የሚቀጥለው? እውነተኛ ለውጥ እንዲመጣ በመሸነጋገል ላይ የተመሠረቱ ሥራዎች መቆም እንዳለባቸው ተናግረዋል።

አቶ ብርሃኑ አሰፋ በሰጡት አስተያየት ”የኔ ብቻ ልክ ነው ከኔ ውጭ ያለው አስተሳሰብ የተሳሳተ ነው” የሚለው አመለካከት ከየት መጣ የሚለውን ከመሰረቱ መለየት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

በተለይ ደግሞ እንደዚህ አይነት ልዩነቶች የሚጎሉት ተማሩ በሚባሉ ሰዎች ላይ ነው ትምህርቱስ ምኑ ላይ ነው? ሲሉም ይጠይቃሉ።

ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ አቶ ታምራት ነገራ ደግሞ ”ጠላትነት ተቋማዊ መዋቅር እንዲይዝ ተደርጓል” የሚል ሀሳብ ያነሱ ሲሆን ይህም ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር ትልቅ ሳንካ ሆኗል ብለዋል።

በውይይት ብቻ ብሔራዊ መግባባት ሊመጣ አይችልም ያሉት አቶ ታምራት በትምህርትና በሐይማኖት ተቋማት በኩል ስለ ብሔራዊ መግባባት በኀብረተሰቡ ዘንድ የማስረጽ ሥራ መሥራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

ሌላዋ የውይይት ተሳታፊ ወይዘሮ መቅደስ አዳነ በበኩላቸው ብሔራዊ መግባባትን አደጋ ላይ የጣለው ዋናው ምክንያት የነበረው የጥላቻ ትርክት እንደሆነም አስረድተዋል።

ዶክተር መረራ በሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብ ብሔራዊ መግባባት በተጨባጭ ለማምጣት የታሪክ ሂሳብ ማወራረድ ውስጥ መግባት እንደማያስፈልግ አመልክተዋል።

በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው የለውጥ እንቅስቃሴ ለብሔራዊ መግባባት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን ያብራሩት ዶክተር መረራ የነገውን ፖለቲካ ለማስተካከል ሁሉም የቤት ሥራውን መሥራት እንዳለበት አስረድተዋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
መከላከያ ሰራዊት🔝ዘመናዊና ብቁ የሆነ ሰራዊት መገንባት የሚያስችለው #የሪፎርም ትግበራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢ/ ሹም ጄኔራል #ሰዓረ_መኮንን አስታወቁ፡፡

ምንጭ~etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፒያሳ🔝ሚድሮክ #ለዓመታት ከልሎ ያስቀመጣቸውን ቦታዎች አጥር በመፍረስ ላይ ይገኛል።

ፎቶ፦GH & DAWIT (TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀሰተኛ ወሬዎችን ተጠንቀቁ‼️

በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ #ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደቱን ለመረበሽ የሚደረጉ ማናቸውንም ዓይነት እንቅስቃሴዎችን በመለየት በጋራ እንደሚከላከሉ የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ አካላት ገለፁ፡፡

ተማሪዎቹም ተጨባጭ ባልሆኑና መሠረተቢስ #ሀሰተኛ ወሬዎች ተታለው ሳይደናገጡ ዋና ትኩረታቸው በትምህርታቸው ላይ ሊሆን እንደሚገባም የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጣሰው ገብሬ አሳስበዋል፡፡

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጣሰው ገብሬ እንደገለፁት የዩኒቨርሲቲውን ሰላማዊ መማር ማስተማር ሂደትን #ለማደናቀፍና ለመረበሽ የሚፈልጉ አንዳንድ ሀይሎች ተማሪዎች ርስበርስ እንዲጋጩ ሆን ተብለው መሠረት የሌላቸው ሀሰተኛ ወሬዎችን በግቢው ውስጥ በመንዛት #ብጥብጥና ግጭት ለመፍጠር የተሞከረው ሙከራ አለመሳካቱን ገልፀው፣ ዩኒቨርሲቲው ያለውን መልካም ስምና ገፅታን በማበላሻትና ተማሪዎች ትምህርታቸውን ተረጋግቶ እንዳይከታተሉ ለማድርግ በውጭም ሆነ በውስጥ በሚሰሩ የጥፋት ሀይሎች ላይ የማጣራት ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው የተደረሰበትንም ውሳኔና እርምጃ በቀጣዩ ዩኒቨርሲቲው እንደሚያሳውቅ ተነግረዋል፡፡

ተማሪዎችም ከእውነት በራቁና በሚናፈሱ ወሬዎች ሳይደናገሩ ትኩረታቸውን ትምህርታቸው ላይ ብቻ እንዲያደርጉ እንዲሁም ወላጆችም ባልተጨበጠና ሀላፊነት በጎደላቸው ግለሰቦች በማህበራዊ ድህረ-ገጽ በሚሰራጩ መሰረት በሌላቸው ወሬዎች ሊረበሹ እንደማይገባ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንት ተማሪ #ሲሳይ_ዮሐንስ እንደተናገረው ተማሪዎች እንዳይረጋጉ ሆን ተብሎ በሀሰት የሚነዙ ወሬዎች መኖራቸውን ጠቅሶ በአሁኑ ግዜ የመማር ማስተማሩ ተግባር ሰላማዊ በሆነ መልኩ እየተካሄደ ነው ሲል ተነግረዋል፡፡

ምንጭ፦ Hadiya zone Communication main process
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለገሀር🔝አዲሱ የለገሃር የተቀናጀ ማህበረሰባዊ ቤቶች ልማት ፕሮጀክት ልዩ የሚያደርገው ምንድነው?

አራት ቁልፍ ነጥቦች፦

1. በአካባቢው ያሉ ነዋሪዎች ቀደም ሲል ከነበረው ልምድ በተለየ መልኩ ወደ ሌላ ቦታ #ሳይፈናቀሉ የልማቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ፤ ድጋፍ በተደረገው 1.8 ቢሊዮን ብር በአካባቢው ከፍተኛ ጥራት ያላቸው መኖሪያ ቤቶች ባለቤቶች ይሆናሉ።

2. በሁለተኛ የልማት ፕሮጄክቱ ከአዲስ አበባ ከተማ ጋር በሽርክና (ጆይንት ቬንቸር) የተገባ ሲሆን፣ አዲስ አበባ 27 በመቶ ድርሻ ትይዛለች።

3. ሦስተኛ፣ ፕሮጄክቱ የለገሃርን ታሪካዊ ገጽታዎች ይዞ፣ አዲስ ከሚሰራዉ ሁለገብ ሰፈር ጋር ጎን ለ ጎን ይቀጥላል።

4. በመጨረሻም ፕሮጀክቱ ስራ ሲጀምር እስከ 25,000 ስራዎችን ይፈጥራል።

ምንጭ፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን በ57 ሚሊዮን ብር ወጪ የሦስት መስኖ ፕሮጀክቶች #ግንባታ መጀመሩን የዞኑ መስኖ ልማት ባለሥልጣን ጽህፈት ቤት አስታውቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update በጋምቤላ ክልል ለታዩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ክፍተቶች በየደረጃው የሚገኙ የጋህአዴን #አመራር አካላት #ችግር መሆኑ ተገለጸ፡፡ ከክልል እስከ ወረዳ የሚገኙ የድርጅቱ የአመራር አካላት በጋምቤላ ከተማ ጥልቅ ግምገማ እያካሄዱ ይገኛሉ።

Via~ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ🔝

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ሕዳር 12 ቀን 2011 ዓ.ም. ከተባበሩት መንግሥታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት #ሊ_ዮንግ ጋር ተገናኝተው ተወያዩ። ውይይታቸው በዋናነት ያተኮረው በኢትዮጵያ ውስጥ የተቀናጀ የግብርና ኢንዲስትሪ ፓርኮችን ለማጠናከር የድርጅቱ ድጋፍ ቀጣይነት ላይ ነው። የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርኮች የግብርና ምርታማነትን በማረጋገጥ፤ እሴትን በመጨመርና የኢትዮጵያዊያንን ኑሮ በማሻሻል የአገሪቱን ኢኮኖሚ መዋቅር ያሸጋግራል ተብሎ ይጠበቃል።

ምንጭ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ #ሙስጠፋ_ዑመር በክልሉ በሚገኙ ከተሞችና ወረዳዎች የመሰረተ ልማትና ማስፋፊያ ፕሮጀክቶች የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠዋል። በጎዴ ከተማ በ300 ሚሊየን ብር ወጪ የሚገነባ የንጹህ መጠጥ ውሃ ማስፋፊያ፣ የጎዴ አጠቃላይ ሆስፒታል ማስፋፊያ እና በሸበሌ ዞን የ2 ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ ስራን የሚያስጀምር የመሰረት ድንጋይ ነው ያስቀመጡት።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia