ለቢዝነሶ ወይም ለግሎ ዌብሳይት ይፈልጋሉ?
እኛ ዛየን ዌብ (Zion Web) እንሰኛለን። ደረጃውን የጠበቀ ዌብሳይት ዲዛይን አድርገን በአጭር ጊዜ ውስጥ በተመጣጣኝ ዋጋ እናስረክባለን።
አሁኑኑ ደዉለዉ 📞0922501644 or @muzika23
1. ከአንድ አመት ዌብ ሆስቲንግ
2. እስከፈለጉት ድረስ የድርጅቶ ኢሜል አድሬስ ለእርሶ እና ለሰራተኞቾች
አሁኑኑ ደዉለዉ የድርጅቶን ዌብሳይት ያስጀምሩ 📞 0922501644 or @muzika23
🏢 SarBet Beside Effoi Pizza
📥 https://yangx.top/zionwebs
እኛ ዛየን ዌብ (Zion Web) እንሰኛለን። ደረጃውን የጠበቀ ዌብሳይት ዲዛይን አድርገን በአጭር ጊዜ ውስጥ በተመጣጣኝ ዋጋ እናስረክባለን።
አሁኑኑ ደዉለዉ 📞0922501644 or @muzika23
1. ከአንድ አመት ዌብ ሆስቲንግ
2. እስከፈለጉት ድረስ የድርጅቶ ኢሜል አድሬስ ለእርሶ እና ለሰራተኞቾች
አሁኑኑ ደዉለዉ የድርጅቶን ዌብሳይት ያስጀምሩ 📞 0922501644 or @muzika23
🏢 SarBet Beside Effoi Pizza
📥 https://yangx.top/zionwebs
#NewsUpdate
ትላንት ምሽቱን የሂዝቦላ ታጣቂ ኃይል በእስራኤል ላይ ተኩስ ከፍቶ አድሯል። የምሽቱ የሮኬት ጥቃቶች ኢንዱስትሪ እና ወታደራዊ ቦታዎች ላይ ያነጣጠረ ነው ሲል የእስራኤል ጦር ገልጿል።
መነሻቸውን ከሊባኖስ አድርገው ወደ ሰሜናዊ እስራኤል ክፍል የተተኮሱት ሮኬቶች መካከል 105 ሮኬቶችን ማክሸፉንም ጨምሮ ገልጿል። ይህም ሆኖ ግን በተወሰኑ ቤቶች ላይ ጉዳት ደርሷል ተብሏል።
ሄዝቦላህ በበኩሉ ባለፈው ሳምንት ለደረሰው የፔጀር እና የዎኪ ቶኪ ጥቃት አጸፋ በደርዘን የሚቆጠሩ ሮኬቶችን ወደ እስራኤል መተኮሱን ተናግሯል።
እስራኤል በሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል የሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶች እስከ ሰኞ ምሽት ድረስ እንዲዘጉ ትዕዛዝ አስተላልፋለች። በቡድን መሰባሰብንም ገድባለች።
@tikvahethmagazine
ትላንት ምሽቱን የሂዝቦላ ታጣቂ ኃይል በእስራኤል ላይ ተኩስ ከፍቶ አድሯል። የምሽቱ የሮኬት ጥቃቶች ኢንዱስትሪ እና ወታደራዊ ቦታዎች ላይ ያነጣጠረ ነው ሲል የእስራኤል ጦር ገልጿል።
መነሻቸውን ከሊባኖስ አድርገው ወደ ሰሜናዊ እስራኤል ክፍል የተተኮሱት ሮኬቶች መካከል 105 ሮኬቶችን ማክሸፉንም ጨምሮ ገልጿል። ይህም ሆኖ ግን በተወሰኑ ቤቶች ላይ ጉዳት ደርሷል ተብሏል።
ሄዝቦላህ በበኩሉ ባለፈው ሳምንት ለደረሰው የፔጀር እና የዎኪ ቶኪ ጥቃት አጸፋ በደርዘን የሚቆጠሩ ሮኬቶችን ወደ እስራኤል መተኮሱን ተናግሯል።
እስራኤል በሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል የሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶች እስከ ሰኞ ምሽት ድረስ እንዲዘጉ ትዕዛዝ አስተላልፋለች። በቡድን መሰባሰብንም ገድባለች።
@tikvahethmagazine
#Telegram ❤ 🇺🇦
ዩክሬን የቴሌግራም የመልእክት መላላኪያ መድረክን ለመንግስት እና ወታደራዊ ሰራተኞች እንዲሁም ለመከላከያ ሴክተር እና ወሳኝ የመሠረተ ልማት ሰራተኞች በተሰጡ ኦፊሴላዊ መሳሪያዎች ላይ አገልግሎት ላይ እንዳይውል አግዳለች።
እገዳው የግል የሞባይል ስልኮችን አያካትትም ተብሏል።
እግዱ የወጣው በ2022 በዩክሬን ላይ ሙሉ ወረራ በጀመረችው ሩሲያ የሚፈጠረውን ስጋት “ለመቀነስ” ነው ሲል የሀገሪቱ ኃያል የብሄራዊ ደህንነት እና መከላከያ ምክር ቤት ተናግሯል።
የደህንነት ምክር ቤቱ "ጠላት ቴሌግራምን ለሳይበር ጥቃት፣ለተንኮል አዘል ሶፍትዌሮች ስርጭት፣ለሚሳኤል ጥቃት ቦታ ጥቆማ በንቃት ይጠቀማል" ሲል ለእገዳው ምክንያቱን አስቀምጧል።
ቴሌግራም የዩክሬን እና የሩሲያ የመንግስት እና የጦር ባለስልጣናት በስፋት የሚጠቀሙት የመረጃ መለዋወጫ መተግበሪያ ነው።
እገዳው ተግባራዊ እንዲሆን በዩክሬን ከፍተኛ የመረጃ ደኅንነት ባለሥልጣናት፣ ወታደራዊ እና የህግ አውጭዎች ባደረጉት ስብሰባ ከስምምነት ላይ መደረሱን ምክር ቤቱ በሰጠው መግለጫ ተናግሯል።
የወታደራዊ መረጃ ሃላፊው ኪሪሎ ቡዳኖቭ እንደገለጹት የተሰረዙ መልእክቶችን እና የተጠቃሚዎችን ግላዊ የመልእክት ልውውጦችን የሩስያ ሃይሎች ማግኘት መቻላቸውን የሚያሳዩ ተአማኒ ማስረጃዎች አሉ ብሏል።
"የመናገር ነፃነትን ሁሌም እደግፋለሁ ነገር ግን የቴሌግራም ጉዳይ የመናገር ነፃነት ጉዳይ አይደለም፣ የብሄራዊ ደህንነት ጉዳይ ነው" ሲል ቡዳኖቭ ተናግሯል።
ቴሌግራም መጠቀም የስራቸው አካል የሆኑ ባለስልጣናት ከእገዳው ነፃ ይሆናሉ ተብሏል።
ቴሌግራም ለቢቢሲ በሰጠው መግለጫ "ሩሲያን ጨምሮ ለየትኛውም ሀገር ምንም አይነት የመልዕክት መረጃ አላቀረበም" ብሏል።
አክሎም አንድ ጊዜ የተሰረዙ መልእክቶች ከተሰረዙ በኋላ ዳግም የሚታዩበት በቴክኒክ ደረጃ ምንም አይነት መንገድ የለም ሲልም ገልጿል።
@tikvahethmagazine
ዩክሬን የቴሌግራም የመልእክት መላላኪያ መድረክን ለመንግስት እና ወታደራዊ ሰራተኞች እንዲሁም ለመከላከያ ሴክተር እና ወሳኝ የመሠረተ ልማት ሰራተኞች በተሰጡ ኦፊሴላዊ መሳሪያዎች ላይ አገልግሎት ላይ እንዳይውል አግዳለች።
እገዳው የግል የሞባይል ስልኮችን አያካትትም ተብሏል።
እግዱ የወጣው በ2022 በዩክሬን ላይ ሙሉ ወረራ በጀመረችው ሩሲያ የሚፈጠረውን ስጋት “ለመቀነስ” ነው ሲል የሀገሪቱ ኃያል የብሄራዊ ደህንነት እና መከላከያ ምክር ቤት ተናግሯል።
የደህንነት ምክር ቤቱ "ጠላት ቴሌግራምን ለሳይበር ጥቃት፣ለተንኮል አዘል ሶፍትዌሮች ስርጭት፣ለሚሳኤል ጥቃት ቦታ ጥቆማ በንቃት ይጠቀማል" ሲል ለእገዳው ምክንያቱን አስቀምጧል።
ቴሌግራም የዩክሬን እና የሩሲያ የመንግስት እና የጦር ባለስልጣናት በስፋት የሚጠቀሙት የመረጃ መለዋወጫ መተግበሪያ ነው።
እገዳው ተግባራዊ እንዲሆን በዩክሬን ከፍተኛ የመረጃ ደኅንነት ባለሥልጣናት፣ ወታደራዊ እና የህግ አውጭዎች ባደረጉት ስብሰባ ከስምምነት ላይ መደረሱን ምክር ቤቱ በሰጠው መግለጫ ተናግሯል።
የወታደራዊ መረጃ ሃላፊው ኪሪሎ ቡዳኖቭ እንደገለጹት የተሰረዙ መልእክቶችን እና የተጠቃሚዎችን ግላዊ የመልእክት ልውውጦችን የሩስያ ሃይሎች ማግኘት መቻላቸውን የሚያሳዩ ተአማኒ ማስረጃዎች አሉ ብሏል።
"የመናገር ነፃነትን ሁሌም እደግፋለሁ ነገር ግን የቴሌግራም ጉዳይ የመናገር ነፃነት ጉዳይ አይደለም፣ የብሄራዊ ደህንነት ጉዳይ ነው" ሲል ቡዳኖቭ ተናግሯል።
ቴሌግራም መጠቀም የስራቸው አካል የሆኑ ባለስልጣናት ከእገዳው ነፃ ይሆናሉ ተብሏል።
ቴሌግራም ለቢቢሲ በሰጠው መግለጫ "ሩሲያን ጨምሮ ለየትኛውም ሀገር ምንም አይነት የመልዕክት መረጃ አላቀረበም" ብሏል።
አክሎም አንድ ጊዜ የተሰረዙ መልእክቶች ከተሰረዙ በኋላ ዳግም የሚታዩበት በቴክኒክ ደረጃ ምንም አይነት መንገድ የለም ሲልም ገልጿል።
@tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የዘመን መለወጫ በዓላት በ #ኢትዮጵያ 🇪🇹
🎆 ጊፋታ (የዎላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ)
🎆 ማሽቃሮ (የካፊቾ የዘመን መለወጫ በዓል)
🎆 ያሆዴ (የሀዲያ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል)
🎆 መሳላ (የከምባታ ብሄር ዘመን መለወጫ በዓል)
🎆 የጎፋ ''ጋዜ'' ማስቃላ እና የኦይዳ ''#ዮኦ'' ማስቃላ በዓል
🎆 ሄቦ (የየም ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ በዓል)
🎆 ዮ__ማስቃላ (የጋሞ ብሔር ዘመን መለወጫ)
🎆 ጋሪ ዎሮ (በቦሮ-ሺናሻ ብሄረሰብ ዘመን መለወጫ በዓል)
እንኳን አደረሳችሁ!
#TikvahEthiopia
@tikvahethmagazine
እንኳን አደረሳችሁ!
#TikvahEthiopia
@tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከታላቁ የህዳሴ ግድብ ኃይል በሚያገኝበት ሁኔታ ላይ የዳሰሳ ጥናት ተጀመረ።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአሶሳ ከተማ እንዲሁም በክልሉ የሚታየውን ሰፊ የኃይል አቅርቦት ችግር ለመፍታት ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኃይል በሚገኝበት ዙሪያ የዳሰሳ ጥናት መጀመሩ ተገልጿል።
ከህዳሴ ግድብ እስከ አሶሳ ድረስ ያለውን 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ መስመር ለመዘርጋት የዳሰሳ ጥናቱ መጀመሩን የተቋሙ ኃላፊ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አረጋግጠዋል።
ይህ ፕሮጀክት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚታየውን የኤሌክትሪክ አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ በረጅም ጊዜ የተቀመጠ አማራጭ ነው ተብሏል።
የዳሰሳ ጥናቱ ምን ያህል ገንዘብ እንደሚፈጅ እንዲሁም የአዋጭነት ጥናት ጭምር ሲሆን አራት ወራትን ይፈጃል ተብሏል።
ተግባራዊነቱ ተረጋግጦ ወደ ግንባታ ከተገባም ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ ሦስት አመት ወይም ከዚያ በላይ ሊወስድ እንደሚችል ሪፖርተር ዘግቧል።
@tikvahethmagazine
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአሶሳ ከተማ እንዲሁም በክልሉ የሚታየውን ሰፊ የኃይል አቅርቦት ችግር ለመፍታት ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኃይል በሚገኝበት ዙሪያ የዳሰሳ ጥናት መጀመሩ ተገልጿል።
ከህዳሴ ግድብ እስከ አሶሳ ድረስ ያለውን 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ መስመር ለመዘርጋት የዳሰሳ ጥናቱ መጀመሩን የተቋሙ ኃላፊ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አረጋግጠዋል።
ይህ ፕሮጀክት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚታየውን የኤሌክትሪክ አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ በረጅም ጊዜ የተቀመጠ አማራጭ ነው ተብሏል።
የዳሰሳ ጥናቱ ምን ያህል ገንዘብ እንደሚፈጅ እንዲሁም የአዋጭነት ጥናት ጭምር ሲሆን አራት ወራትን ይፈጃል ተብሏል።
ተግባራዊነቱ ተረጋግጦ ወደ ግንባታ ከተገባም ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ ሦስት አመት ወይም ከዚያ በላይ ሊወስድ እንደሚችል ሪፖርተር ዘግቧል።
@tikvahethmagazine
#Update
° እስራኤል በዛሬው እለት ሂዝቦላ ይንቀሳቀስባቸዋል ባለቻቸው ከ800 በላይ ቦታዎች ላይ ጥቃት ከፍታለች።
° የሊባኖስ የጤና ሚኒስቴር በጥቃቱ ቢያንስ 270 ሰዎች መሞታቸውን ሲግልጽ፤ 21 ህጻናት ናቸው ብሏል።
እስራኤል በዛሬው እለት "የሂዝቦላ ታጣቂዎች የሚንቀሳቀሱባቸው ቦታዎች ናቸው" ባለቻቸው ከ8 መቶ በላይ በሚቆጠሩ ኢላማዎች ላይ የአየር ጥቃት ከፍታለች።
ጥቃቱ የጋዛ ግጭት ከጀመረ በኋላ ከፍተኛው ነው ሲባል በቀጠናው ውጥረት ነግሷል።
ከሟቾቹ መካከል ምን ያህሉ ሲቪሎች ወይም የሂዝቦላህ ታጣቂዎች እንደሆኑ ግልፅ ባይሆንም እስራኤል ጥቃቶቹ ያነጣጠሩት ሂዝቦላ በሚንቀሳቀስባቸው አካባቢዎች እንደሆኑ ገልጻለች።
እስራኤል የጥቃት ትኩረቷን ወደ ሰሜናዊ ድንበር አዙራለች የተባለ ሲሆን በኢራን ይደገፋል የተባለው የሂዝቦላ ጦር ሃማስን በመደገፍ ወደ እስራኤል ሮኬቶችን እያስወነጨፈ ነው ተብሏል።
የእስራኤል የመከላከያ ሚኒስትር ዮአቭ ጋላንት ባሰራጩት የቪዲዮ መልእክት "የሰሜን አካባቢ ነዋሪዎችን በሰላም ወደ ቤታቸው በመመለስ ሂደት ውስጥ ግባችን ላይ እስክንደርስ ድረስ ጥቃቶቹ ይቀጥላሉ" ሲሉ ተናግረዋል።
በጥቃቱ ቢያንስ 270 ሰዎች መሞታቸው ሲገልፅ ከ1,024ሰዎች በላይ መቁሰላቸውን የሊባኖስ የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
ከተጎጂዎቹ መካከል ሴቶች እና ህጻናትን እንደሚገኙነት የሊባኖስ የሀገር ውስጥ ሚዲያዎች ዘግበዋል። የሊባኖስ ነዋሪዎች ሂዝቦላህ የጦር መሳሪያውን ከሚያከማችባቸው ቦታዎች ለቀው እንዲወጡ እስራኤል ማሳሰቢያ ሰጥታለች ተብሏል።
የሂዝቦላ ጦር ለጥቃቱ ሰጠሁት ባለው አፀፋዊ ምላሸ በእስራኤል ወታደራዊ ካምፖች ላይ ሮኬቶችን ማስወንጨፉን ገልጿል።
እስራኤል ይህን መሰል ጥቃት ስትፈጽም ከ2006 በኋላ ይኽ የመጀመሪያው ነው ተብሏል።
@tikvahethmagazine
° እስራኤል በዛሬው እለት ሂዝቦላ ይንቀሳቀስባቸዋል ባለቻቸው ከ800 በላይ ቦታዎች ላይ ጥቃት ከፍታለች።
° የሊባኖስ የጤና ሚኒስቴር በጥቃቱ ቢያንስ 270 ሰዎች መሞታቸውን ሲግልጽ፤ 21 ህጻናት ናቸው ብሏል።
እስራኤል በዛሬው እለት "የሂዝቦላ ታጣቂዎች የሚንቀሳቀሱባቸው ቦታዎች ናቸው" ባለቻቸው ከ8 መቶ በላይ በሚቆጠሩ ኢላማዎች ላይ የአየር ጥቃት ከፍታለች።
ጥቃቱ የጋዛ ግጭት ከጀመረ በኋላ ከፍተኛው ነው ሲባል በቀጠናው ውጥረት ነግሷል።
ከሟቾቹ መካከል ምን ያህሉ ሲቪሎች ወይም የሂዝቦላህ ታጣቂዎች እንደሆኑ ግልፅ ባይሆንም እስራኤል ጥቃቶቹ ያነጣጠሩት ሂዝቦላ በሚንቀሳቀስባቸው አካባቢዎች እንደሆኑ ገልጻለች።
እስራኤል የጥቃት ትኩረቷን ወደ ሰሜናዊ ድንበር አዙራለች የተባለ ሲሆን በኢራን ይደገፋል የተባለው የሂዝቦላ ጦር ሃማስን በመደገፍ ወደ እስራኤል ሮኬቶችን እያስወነጨፈ ነው ተብሏል።
የእስራኤል የመከላከያ ሚኒስትር ዮአቭ ጋላንት ባሰራጩት የቪዲዮ መልእክት "የሰሜን አካባቢ ነዋሪዎችን በሰላም ወደ ቤታቸው በመመለስ ሂደት ውስጥ ግባችን ላይ እስክንደርስ ድረስ ጥቃቶቹ ይቀጥላሉ" ሲሉ ተናግረዋል።
በጥቃቱ ቢያንስ 270 ሰዎች መሞታቸው ሲገልፅ ከ1,024ሰዎች በላይ መቁሰላቸውን የሊባኖስ የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
ከተጎጂዎቹ መካከል ሴቶች እና ህጻናትን እንደሚገኙነት የሊባኖስ የሀገር ውስጥ ሚዲያዎች ዘግበዋል። የሊባኖስ ነዋሪዎች ሂዝቦላህ የጦር መሳሪያውን ከሚያከማችባቸው ቦታዎች ለቀው እንዲወጡ እስራኤል ማሳሰቢያ ሰጥታለች ተብሏል።
የሂዝቦላ ጦር ለጥቃቱ ሰጠሁት ባለው አፀፋዊ ምላሸ በእስራኤል ወታደራዊ ካምፖች ላይ ሮኬቶችን ማስወንጨፉን ገልጿል።
እስራኤል ይህን መሰል ጥቃት ስትፈጽም ከ2006 በኋላ ይኽ የመጀመሪያው ነው ተብሏል።
@tikvahethmagazine
#ሊባኖስ
በሊባኖስ እና በቀጠናው ያለው ወቅታዊ የፀጥታ
ውጥረት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ በመምጣቱ
በሊባኖስ፤ የቤይሩት የኢትዮጵያ ቆንስላ ጄኔራል ፅ/ቤት የጥንቃቄ መልዕከት አስተላልፏል።
ፅ/ቤቱ "በተለይም በደቡባዊ ሊባኖስ እንዲሁም በቤይሩት አንዳንድ አካባቢዎች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች ተጠናከረው ቀጥለዋል" ብሏል።
ቆንስላ ጄኔራል ፅ/ቤቱ የሁኔታውን አሳሳቢነት ተረድቶ፣ የዜጎቻችን ደህንነት ለማስጠበቅ ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመሆን እየተከታተለ እንደሚገኝም አሳውቋል።
ስለሆነም የሚከተሉትን የጥንቃቄ እርምጃዎች ዜጎች እንድትወስዱ ሲል አሳስቧል።
1. በአብዛኛው የጥቃት ዒላማ ሊሆኑ ይቻላሉ ተብለው ከሚታሰቡ ቦታዎች እራስን ማራቅ፣
2. ከሊባኖስ መንግስት የሚሰጡ መመሪያዎችን እና አቅጣጫዎችን መተግበር ወይም ማከበር፤
3. አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ የበለጠ እየከፋ የሚሄድ ከሆነ በቀጣይ የምንወስዳቸውን እርምጃዎችን ይፋ ስለምናደግ ከቆንስላ ጄኔራል ጽ/ቤቱ የፌስ-ቡክ ፔጅ የሚለቀቁ መረጃዎችን በየጊዜው መከታተል፣
4. ማንኛውንም የከፋ ሁኔታ በሚገጥማችሁ ወቅት በቆንስላው ቀጥታ የስልክ መስመር +9615467166 እና በWhatsapp ቁጥር ማሳወቅ ጠቃሚ ይሆናል።
@tikvahethmagazine
በሊባኖስ እና በቀጠናው ያለው ወቅታዊ የፀጥታ
ውጥረት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ በመምጣቱ
በሊባኖስ፤ የቤይሩት የኢትዮጵያ ቆንስላ ጄኔራል ፅ/ቤት የጥንቃቄ መልዕከት አስተላልፏል።
ፅ/ቤቱ "በተለይም በደቡባዊ ሊባኖስ እንዲሁም በቤይሩት አንዳንድ አካባቢዎች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች ተጠናከረው ቀጥለዋል" ብሏል።
ቆንስላ ጄኔራል ፅ/ቤቱ የሁኔታውን አሳሳቢነት ተረድቶ፣ የዜጎቻችን ደህንነት ለማስጠበቅ ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመሆን እየተከታተለ እንደሚገኝም አሳውቋል።
ስለሆነም የሚከተሉትን የጥንቃቄ እርምጃዎች ዜጎች እንድትወስዱ ሲል አሳስቧል።
1. በአብዛኛው የጥቃት ዒላማ ሊሆኑ ይቻላሉ ተብለው ከሚታሰቡ ቦታዎች እራስን ማራቅ፣
2. ከሊባኖስ መንግስት የሚሰጡ መመሪያዎችን እና አቅጣጫዎችን መተግበር ወይም ማከበር፤
3. አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ የበለጠ እየከፋ የሚሄድ ከሆነ በቀጣይ የምንወስዳቸውን እርምጃዎችን ይፋ ስለምናደግ ከቆንስላ ጄኔራል ጽ/ቤቱ የፌስ-ቡክ ፔጅ የሚለቀቁ መረጃዎችን በየጊዜው መከታተል፣
4. ማንኛውንም የከፋ ሁኔታ በሚገጥማችሁ ወቅት በቆንስላው ቀጥታ የስልክ መስመር +9615467166 እና በWhatsapp ቁጥር ማሳወቅ ጠቃሚ ይሆናል።
@tikvahethmagazine
በደመራ እና በኢሬቻ በዓላት ለሚያስተባብሩ 310ሺህ ወጣቶች ስምሪት ተሰጠ።
የመስቀል ደመራ እና የኢሬቻ በዓላት በሰላም እንዲከበር ለሚያስተባብሩ 310 ሺህ ለሚሆኑ የከተማው ወጣቶች የስራ ስምሪት ተሰጥቷል።
ስምሪቱን የሰጡት፥ የአዲስ አበባ ከተማ ሰላም ፀጥታ ቢሮ፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ እና የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽን በጋራ በመሆን ነው።
ወጣቶቹ፥ ከፀጥታ አካላት ጋር ተቀናጅተው በተሰጣቸው ስምሪት መሰረት እንዲሰሩና በበዓላቱ እንዳይያዙ የተከለከሉ ነገሮችን እና በኮሪደር ልማት የተሰሩ የልማት ስራዎችን እንዲቆጣጠሩ ማሳሰቢያ ተሰጥቷቸዋል።
መረጃው የአ/አ ከተማ አስተዳደር ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።
@tikvahethmagazine
የመስቀል ደመራ እና የኢሬቻ በዓላት በሰላም እንዲከበር ለሚያስተባብሩ 310 ሺህ ለሚሆኑ የከተማው ወጣቶች የስራ ስምሪት ተሰጥቷል።
ስምሪቱን የሰጡት፥ የአዲስ አበባ ከተማ ሰላም ፀጥታ ቢሮ፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ እና የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽን በጋራ በመሆን ነው።
ወጣቶቹ፥ ከፀጥታ አካላት ጋር ተቀናጅተው በተሰጣቸው ስምሪት መሰረት እንዲሰሩና በበዓላቱ እንዳይያዙ የተከለከሉ ነገሮችን እና በኮሪደር ልማት የተሰሩ የልማት ስራዎችን እንዲቆጣጠሩ ማሳሰቢያ ተሰጥቷቸዋል።
መረጃው የአ/አ ከተማ አስተዳደር ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።
@tikvahethmagazine
TIKVAH-MAGAZINE
በሱዳን በተቀሰቀሰ የኮሌራ ወረርሽኝ 348 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ። የሱዳን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በሃገሪቱ ከነሐሴ 12 ጀምሮ በተቀሰቀሰ የኮሌራ ወረርሽኝ ከ 11,000 በላይ ሰዎች መያዛቸውን እና በዘጠኝ ግዛቶች 348 ሰዎች በወረርሽኙ ሳቢያ መሞታቸውን መናገሩን ሱዳን ትሪብዩን ዘግቧል። በሃገሪቱ ካለው የጸጥታ ችግር በተጨማሪ ከባድ ዝናብ እና የጎርፍ አደጋዎች ለወረርሽኙ መስፋፋት ምክንያት መሆናቸው…
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#Canada 🇨🇦
የካናዳ መንግስት የትምህርት እና የስራ ፈቃድን ለመገደብ ያወጣው ፖሊሲ ከሁለት ቀናት በኋላ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል
የካናዳ መንግስት የትምህርት ፈቃዶችን ቁጥር መገደብን ጨምሮ አንዳንድ የኢሚግሬሽን ፖሊሲዎቹን አዘምኗል።
ይህም በሺዎች በሚቆጠሩ የውጭ ተማሪዎችን ያስቆጣ ሲሆን በመላው ካናዳ ከአገር ልንባረር እንችላለን በሚል ስጋት ተቃውሞአቸውን ሲያሰሙ ቆይተዋል።
በፖሊሲው ለውጥ መሰረት መንግስት የቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ የሚሰጣቸው እጩዎች ቁጥር በ25 በመቶ እንዲቀንስ የሚያደርግ ሲሆን የትምህርት ፈቃዶችንም ይገድባል።
ለፖሊሲው መሻሻል ሀገሪቱ ባለፉት ጥቂት አመታት ፈጣን የህዝብ ቁጥር መጨመር ማስመዝገቧ ምክንያት መሆኑን ተነግሯል።
አንዳንድ የተማሪዎች ተሟጋች ቡድን ተወካዮች የውጭ ሀገር ተመራቂዎች የስራ ፈቃዳቸው በ2024 መጨረሻ ሲያልቅ ከአገር የመባረር ስጋት እንዳለባቸው አስጠንቅቀዋል።
ካናዳ ከትምህርት ፈቃዶች በተጨማሪ ጊዜያዊ የውጭ ሀገር የስራ ፈቃዶችን በ65,000 ለመቀነስ አቅዳለች።
እ.ኤ.አ. በ 2023 የካናዳ መንግስት 183,820 ለሚሆኑ የውጭ ዜጎች ጊዜያዊ የስራ ፈቃድ ሰጥቶ ነበር።
ይህም በ 2019 ከነበረው የስራ ፈቃድ ቁጥር በ 88 በመቶ ጭማሪ ነበረው።
በሌላ በኩል፣ በካናዳ ያለው የስራ አጥነት መጠን ባለፉት ሁለት ወራት በ 6.4 በመቶ የጨመረ ሲሆን 1.4 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች ስራ አጥ መሆናቸው ተነግሯል።
ከመስከረም 16 ጀምሮ በሥራ ላይ የሚውለው አዲሱ ፖሊሲ ይህንን ችግር ለመቅረፍ ያለመ ነው ተብሏል።
@tikvahethmagazine
የካናዳ መንግስት የትምህርት እና የስራ ፈቃድን ለመገደብ ያወጣው ፖሊሲ ከሁለት ቀናት በኋላ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል
የካናዳ መንግስት የትምህርት ፈቃዶችን ቁጥር መገደብን ጨምሮ አንዳንድ የኢሚግሬሽን ፖሊሲዎቹን አዘምኗል።
ይህም በሺዎች በሚቆጠሩ የውጭ ተማሪዎችን ያስቆጣ ሲሆን በመላው ካናዳ ከአገር ልንባረር እንችላለን በሚል ስጋት ተቃውሞአቸውን ሲያሰሙ ቆይተዋል።
በፖሊሲው ለውጥ መሰረት መንግስት የቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ የሚሰጣቸው እጩዎች ቁጥር በ25 በመቶ እንዲቀንስ የሚያደርግ ሲሆን የትምህርት ፈቃዶችንም ይገድባል።
ለፖሊሲው መሻሻል ሀገሪቱ ባለፉት ጥቂት አመታት ፈጣን የህዝብ ቁጥር መጨመር ማስመዝገቧ ምክንያት መሆኑን ተነግሯል።
አንዳንድ የተማሪዎች ተሟጋች ቡድን ተወካዮች የውጭ ሀገር ተመራቂዎች የስራ ፈቃዳቸው በ2024 መጨረሻ ሲያልቅ ከአገር የመባረር ስጋት እንዳለባቸው አስጠንቅቀዋል።
ካናዳ ከትምህርት ፈቃዶች በተጨማሪ ጊዜያዊ የውጭ ሀገር የስራ ፈቃዶችን በ65,000 ለመቀነስ አቅዳለች።
እ.ኤ.አ. በ 2023 የካናዳ መንግስት 183,820 ለሚሆኑ የውጭ ዜጎች ጊዜያዊ የስራ ፈቃድ ሰጥቶ ነበር።
ይህም በ 2019 ከነበረው የስራ ፈቃድ ቁጥር በ 88 በመቶ ጭማሪ ነበረው።
በሌላ በኩል፣ በካናዳ ያለው የስራ አጥነት መጠን ባለፉት ሁለት ወራት በ 6.4 በመቶ የጨመረ ሲሆን 1.4 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች ስራ አጥ መሆናቸው ተነግሯል።
ከመስከረም 16 ጀምሮ በሥራ ላይ የሚውለው አዲሱ ፖሊሲ ይህንን ችግር ለመቅረፍ ያለመ ነው ተብሏል።
@tikvahethmagazine
TIKVAH-MAGAZINE
#Mpox_Update የዝንጀሮ ፈንጣጣ (Mpox) የዓለም የህብረተሰብ የጤና ሥጋት ተብሎ ከተበየነ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአፍሪካ ውጪ በስዊድን በበሽታው የተያዘ ሰው መገኘቱ ሪፖርት ተደርጓል። የሀገሪቱ የህብረተሰብ ጤና ኤጀንሲ እንዳስታወቀው የተያዘው ግለሰብ በሽታው ሪፖርት በተደረገበት የአፍረካ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያለው ሲሆን አሁን ላይ በስቶክሆልም የማገገሚያ ሥፍራ ክትትል እየተደረገለት ነው ተብሏል።…
በህንድ የመጀመሪያ የኤምፖክስ (Mpox) ታማሚ መገኘቱ ሪፖርት ተደረገ።
ህንድ በአዲሱ የኤምፖክስ ዝርያ የተያዘ ታማሚ በሀገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ መመዝገቡን ይፋ አድርጋለች።
በህንድ የተመዘገበወሰ #ክላድ 1 ለ (Clade_1 B) ተብሎ የሚጠራው አዲሱ ተለዋጭ እና ተላላፊ ዝርያ በአፍሪካ ውስጥ ካለው የMpox ወረርሽኝ ጋር ተመሳስይ ባህርይ ያለው እንደሆነ ሮይተርስ ዘግቧል።
በበሽታ የተያዘው ግለሰብ ወንድ ሲሆን እድሜው 38 አመቱ ነው። የደቡብ ኬራላ ግዛት ነዋሪ እና በቅርቡ ከዱባይ የተመለሰ እንደሆነ ተገልጿል።
የዓለም ጤና ድርጅት በነሀሴ ወር የMpox ወረርሽኝን በአፍሪካ ድንገተኛ የጤና አደጋ መሆኑን ካወጀ በኋላ ከአፍሪካ ውጪ ወደ ስዊድን፣ ታይላንድ እና ፓኪስታን መሰራጨቱ ተነግሯል።
@tikvahethmagazine
ህንድ በአዲሱ የኤምፖክስ ዝርያ የተያዘ ታማሚ በሀገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ መመዝገቡን ይፋ አድርጋለች።
በህንድ የተመዘገበወሰ #ክላድ 1 ለ (Clade_1 B) ተብሎ የሚጠራው አዲሱ ተለዋጭ እና ተላላፊ ዝርያ በአፍሪካ ውስጥ ካለው የMpox ወረርሽኝ ጋር ተመሳስይ ባህርይ ያለው እንደሆነ ሮይተርስ ዘግቧል።
በበሽታ የተያዘው ግለሰብ ወንድ ሲሆን እድሜው 38 አመቱ ነው። የደቡብ ኬራላ ግዛት ነዋሪ እና በቅርቡ ከዱባይ የተመለሰ እንደሆነ ተገልጿል።
የዓለም ጤና ድርጅት በነሀሴ ወር የMpox ወረርሽኝን በአፍሪካ ድንገተኛ የጤና አደጋ መሆኑን ካወጀ በኋላ ከአፍሪካ ውጪ ወደ ስዊድን፣ ታይላንድ እና ፓኪስታን መሰራጨቱ ተነግሯል።
@tikvahethmagazine