TIKVAH-MAGAZINE
199K subscribers
19.1K photos
299 videos
70 files
2.48K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

#ኢትዮጵያ

ያግኙን +251913134524
加入频道
#SamiTech

አዳዲስ ላፕቶፕች ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech

በአገልግሎት አሰጣጣችንና በዕቃዎቻችን ጥራት ላይ ደንበኞቻችን ምስክሮች ናቸው።
ዛሬም ብዛት እንዲሁም ጥራት ሳንቀንስ እያስተናገድን እንገኛለ!

ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች፣ ለጌመሮች፣ ወ.ዘ.ተ.

አቅምን ካገናዘቡ እስከ ቅንጡ ላፕቶፖች ይህ ቀረ ሳይሉ የሚያገኙበትን ሱቃችንን ይጎብኙ! የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ ባሉበት ሆነው ይዘዙን እናደርሳለን።

የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት 👉 @samcomptech ተጭነው በቴሌግራምው ማየት ይችላሉ።

@sww2844
0928442662
0940141114

https://yangx.top/samcomptech
#cloudbridge. #traininginstitute

ክላውድ በሪጂ ማሰልጠኛ ተቋም ፤ለስልጠና ፍላጊዎች በሙሉ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽ እውቀት አቅም ግንባታ ነፃ ስልጠና ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቆ እናንተን በጉጉት  ይጠብቃል::

ስልጠና ሚሰጥባችው ዘረፎች መካከል፡
1,Web development
2,Interior design

የስልጠና ቦታ
ሲቲ ሞል 6ኛ ፎቅ, መገናኛ ድልድይ,wow burger ያለበት፣Megenagna siti Mall 6th, Addis Ababa, Ethiopia

ለተጨማሪ መረጃ
094-228-0000 092-083-8483
ያሉን ቦታዎች ውስን ናቸው ፈጥነው በአካል መተው ይመዝገቡ።
         ለአንድ ቀን ሚቆይ ነፃ ስልጠና!
              Register online
https://cloudbridgeacademy.com/registration

Telegram :https://yangx.top/cbmtraininginstitute
TIKVAH-MAGAZINE
በኬንያ በተከሰተው ከባድ ጎርፍ በትንሹ 32 ሰዎች ሞተው ከ40 ሺ በላይ ዜጎች መፈናቀላቸው ተነገረ በኬንያ በተከሰተው ከባድ ጎርፍ በትንሹ 32 ሰዎች ህይወታቸውን እንዳጡ እና ከ40 ሺህ የሚበልጡት ደግሞ ዝናቡ ባስከተለው ጎርፍ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ለመፈናቀል መገደዳቸው ተገልጿል። በርዕሰ ከተማዋ መንገዶች በውሃ ተጥለቅልቀው የታዩ ሲሆን በዚህ ከባድ ጎርፍ ምክንያት 15 ሰዎች ቆስለው፣ 1ሺ የሚጠጉ…
#Update: በኬንያ በጣለው ከባድ ዝናብ የሟቾች ቁጥር 70 መድረሱ ተነገረ

በኬንያ በጣለው ከባድ ዝናብ እና የጎርፍ አደጋ ሕይወታቸውን ያጡ የኬንያውያን ዜጎች ቁጥር  70 መድረሱን የኬንያ የመንግሥት ቃል አቀባይ አይዛክ ሙዋራ በትላንትናው እለት በናይሮቢ በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።

የጎርፉ አደጋ ከኬንያ 47 ክልሎች 23ቱን ያጠቃ ሲሆን ሰብአዊ ጉዳቱን እንዳባባሰው ተገልጿል። የሀገሪቱ የሚቲዎሮሎጂ ዲፓርትመንት በሚቀጥሉት 3 ቀናትም በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች መካከለኛ እና ከባድ ዝናብ እንደሚቀጥል ትንበያውን አስቀምጧል።

@TikvahethMagazine
በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊና ቁሳዊ ሀብቶች ላይ ያተኰረ ኢንሳይክሎፔዲያ ሊዘጋጅ ነው

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊና ቁሳዊ ሀብቶች እንዲሁም አስተምህሮዎች ላይ ያተኰረ መዝገበ አእምሮ (ኢንሳይክሎፔዲያ) በማኅበረ ቅዱሳን አማካይነት ሊዘጋጅ መሆኑ ተገልጿል።

የመዝገበ አእምሮ (ኢንሳይክሎፒዲያ) ደረጃውን በጠበቀ መንገድ ለማዘጋጀት እንዲቻል በተለያዩ የሙያ መስኮች የተሰማሩ ምሁራን ዕውቀታቸውንና ልምዳቸውን ማካፈል የሚችሉበት መድረክ በዛሬው እለት በኢሊሌ ኢንተርናሽናል ሆቴል እየተካሄደ ይገኛል።

የሚዘጋጀው መዝገበ አእምሮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ፣ ጥንታዊና ሐዋርያዊ አስተምህሮ ፣ ዶግማ ፣ ቀኖና እና ትውፊት እንዲሁም የጳጳሳትን፣ የሊቃውንትን፣ የትልልቅ ገዳማትንና አድባራትን ታሪክ ወዘተ የሚያካትት ይሆናል ተብሎ እንደሚጠበቅ የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት በዘገባው አመልክቷል።

@TikvahethMagazine
ሳፋሪኮም በ3 ዓመታት ውስጥ የኔትዎርክ ማማዎችን በሦስት እጥፍ ለማሳደግ እቅድ እንዳለው ገለፀ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት 3 አመታት ከ1.5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ኢንቨስት በማድረግ በመላ ሀገሪቱ የኔትወርክ ተደራሽነቱን ለማስፋት የሚያንቀሳቅሳቸውን የቴሌኮም ማማዎች በሶስት እጥፍ ለማሳደግ እቅድ እንዳለው ገለፀ።

ኩባንያው በፀጥታ ችግር ምክንያት በሚፈለገው ልክ ተደራሽቱን ማስፋት እንዳልቻለ ሲገልፅ በአሁኑ ወቅት 2,500 የኔትዎርክ ማማዎችን የሚያንቀሳቅስ ሲሆን 1,000 ያህሉን ከኢትዮ ቴሌኮም የተከራየው መሆኑን የኩባንያው  ዋና ስራ አስፈፃሚ ዊም ቫንሄሌፑቴ ለሪፖርተር ተናግረዋል።

ሳፋሪኮም በአዲስ አበባ እና በሌሎች 26 የከተማ አካባቢዎች ተደራሽ መሆኑን የገለፁት ሀላፊው ነገር ግን ኩባንያው በመላው ሀገሪቱ አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረስ እስከ 7ሺ የኔትዎርክ ማማ የሚያስፈልገው መሆኑን አንስተዋል።

@TikvahethMagazine
ደስ ይበላችሁ!

ካሉበት ሆነው ለሚወዱት ቤተሰቦ/ወዳጆ ለትንሳዔ እንዲሁም ለዳግመ ትንሳዔ በዓላት ሙሉ #ሥጦታ ከሙሉ #ደስታ ጋር ይላኩ!

ድርጅታችን በ #Platinum , #Golden, #Silver አማራጭ #የበግ ሙክትን ጨምሮ በዓል በዓል የሚሉ ሥጦታዎችን ለሚወዱት ሰው #ባለበት #በተመጣጣኝ ዋጋ ይላኩ። እንደ እናንተው ሆነን እናደርሳለን!

ይደውሉ - 0911359234 (WhatsApp NO.) or 0954882764

ሙሉ ፖኬጁን ይመልከቱ 👉 t.me/bluebellgiftstore

😮 #ለቤተሰቦቻችን_ብቻ: ባለፈው ዓመት ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ስጦታ የላኩ እንዲህ ተደስተዋል 👉https://yangx.top/bluebellgiftstore/627
#NaturalDisaster

" በቀጣይ የበልግ ዝናብ ወቅት በሶማሌ ክልል ከ1.2 ሚሊዮን በላይ ሰዎች እንዲሁም በሌሎች ክልሎች በመቶ ሺ የሚገመቱ ሰዎች በጎርፍ ሊጠቁ ይችላሉ " OCHA

በኢትዮጵያ በሶማሌ፣ ደቡብ፣ ኦሮሚያ፣ አፋርን ጨምሮ ሌሎችም ክልሎች እስከ ግንቦት ባለው የበልግ የዝናብ ወቅት ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ሰዎች በጎርፍ ሊጠቁ እና ሊፈናቀሉ እደሚችሉ የመንግስታቱ ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (OCHA) ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል።

በሪፖርቱ መሰረት፦

- በ #ሶማሌክልል፡- በአፍዴር፣ ሊባን፣ ቆራሄ፣ ኤረር፣ ዳዋ፣ ጃራራ፣ ኖጎብ እና ሸበሌ ዞኖች ከ1.2 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በጎርፍ በጎርፍ ሊጠቁ ይችላሉ ተብሎ የተገመተ ሲሆን ወደ 773,000 የሚጠጉ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ ይጠበቃል።

- በ #ደቡብ፦ 145,000 የሚጠጉ ሰዎች በጎርፍ ሊጠቁ የሚችሉ ሲሆኑ 64,000 ሰዎች ቀደም ሲል በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በመካከለኛው ኢትዮጵያ ክልል፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና በሲዳማ ክልሎች ተፈናቅለዋል።

- በ #ኦሮሚያክልል፦ 421,000 የሚገመቱ ሰዎች በጎርፍ ይጠቃሉ ተብሎ የሚገመት ሲሆን በቦረና፣ ጉጂ፣ ምዕራብ ጉጂ፣ ባሌ፣ ምስራቅ ባሌ፣ አርሲ፣ ምዕራብ አርሲ፣ ምስራቅ ሸዋ፣ ምዕራብ ሀረርጌ እና ምስራቅ ሀረርጌ ወደ 104,000 የሚጠጉ ሰዎች ተፈናቅለዋል።

#አፋርክልል፦ 83,000 የሚጠጉ ሰዎች ለጎርፍ አደጋ የመጋለጥ እድላቸው ከፍተኛ ሲሆን 61,000 ሰዎች በተለያዩ ዞኖች ይፈናቀላሉ ተብሎ ይገመታል።

#አማራክልል ፦ ከሰሜን ወሎ፣ ደቡብ ወሎ እና ከኦሮሞ ልዩ ዞን የተፈናቀሉ 3,000 ግለሰቦችን ጨምሮ ወደ 45,000 የሚጠጉ ሰዎች የጎርፍ ተጠቂ ይሆናሉ ተብሎም ተጠቁሟል።

#ትግራይክልል፦ 4,000 የሚገመቱ ሰዎች የጎርፍ ተጠቂ ይሆናሉ ተብሎ የሚገመት ሲሆን 1,000 ሰዎች በደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ አካባቢዎች ሊፈናቀሉ  ይችላሉ።

የኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ከሰብአዊ የእርዳታ ድርጅቶች ጋር በመሆን ከመጋቢት እስከ ግንቦት የጎርፍ አደጋን ለመከላከል በአፋር፣ በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ ሶማሌ እና የደቡብ ክልሎች የጎርፍ አደጋ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን በመለየት የቅድመ ዝግጅት ስራ የሰራ ሲሆን የገንዘብ እጥረት ግን የእርዳታ አቅርቦቱን እየገደበ መሆኑ ተገልጿል።

ፎቶ፦ ፋይል

@TikvahethMagazine
በጎፋ ዞን ቡልቂ ከተማ የ16 አመት ታዳጊ የደፈሩ 2 ግለሰቦችና ታዳጊዋ እንድትደፈር ያደረገች ሴት በፅኑ እስራት ተቀጡ

በጎፋ ዞን በቡልቂ ከተማ አስተዳደር መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በአስገድዶ መድፈር ወንጀል የተከሰሱ 2 ግለሰቦችና ታዳጊዋ እንድትደፈር በማመቻቸት በአባሪነት የተከሰሰች አንዲት ሴት በጽኑ እሥራት መቀጣታቸውን የከተማው ኮሚኒኬሽን አሳውቋል።

1ኛ ተከሣሽ የሆነው አቶ በቃኃኝ ባቤና እና 2ኛ ተከሣሽ አቶ አበራ ሚኖታ የተባሉት ግለሰቦች የ16 ዓመቷን ታዳጊ በመድፈር ክስ ሲቀርብባቸው 3ኛ ተከሣሽ የሆነችው ወ/ሮ ብርቱኳን ከበደ ደግሞ በራሷ ምግብ ቤት በዕቃ አጣቢነት ቀጥራ የምታሠራትን ይህቺን ታዳጊ ሰራተኛ ያለፍቃዷ 1ኛ ተከሣሽ እንዲደፍራት በማመቻቸት መከሰሷ ተገልጿል።

የከተማው ፖሊስ የተፈፀመውን ወንጀል መነሻ በማድረግ ምርመራ አድርጎ ያጠናቀቀውን የምርመራ መዝገብ ለከተማው ዓቃቤ ሕግ አቅርቦ ዐቃቤ ሕግም የምርመራ መዝገቡን ከመረመረ በኋላ ፍርድ ቤቱ 1ኛ እና 2ኛ ተከሣሾች ተበዳይን ያለፍላጎቷ አስገድደው ስለመድፈራቸው እና 3ኛ ተከሣሽም ተበዳይ በ1ኛ ተከሣሽ ያለፍላጎቷ እንድትደፈር ምቹ ሁኔታ መፍጠሯን በማስረጃ አረጋግጧል።

በዚህም የቡልቂ ከተማ አስተዳደር መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የተከሣሾቹን ማቅለያ እና የዐቃቤ ሕግን ማክበጃ ሀሳቦችን ከመረመረ በኋላ

#1ኛ ተከሣሽ አቶ በቃኻኝ ባቤና በ9 ዓመት ጽኑ እሥራት፤
#2ኛ ተከሣሽ አቶ አበራ ምኖታ በ7 ዓመት ከ8 ወር ጽኑ እስራት፤
#3ኛ ተከሣሽ የሆነችው ወ/ሮ ብርቱኳን ከበደ በ6 ዓመት ጽኑ እሥራት እንዲቀጡ ወስኗል።

@TikvahethMagazine
እንኳን አደረሳችሁ!

ካሉበት ሆነው ለሚወዱት ቤተሰቦ/ወዳጆ ለትንሳዔ እንዲሁም ለዳግመ ትንሳዔ በዓላት ሙሉ #ሥጦታ ከሙሉ #ደስታ ጋር ይላኩ!

ድርጅታችን በ #Platinum , #Golden, #Silver አማራጭ #የበግ ሙክትን ጨምሮ በዓል በዓል የሚሉ ሥጦታዎችን ለሚወዱት ሰው #ባለበት #በተመጣጣኝ ዋጋ ይላኩ። እንደ እናንተው ሆነን እናደርሳለን!

ይደውሉ - 0911359234 (WhatsApp NO.) or 0954882764

ሙሉ ፖኬጁን ይመልከቱ 👉 t.me/bluebellgiftstore

😮 #ለቤተሰቦቻችን_ብቻ: ባለፈው ዓመት ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ስጦታ የላኩ እንዲህ ተደስተዋል 👉https://yangx.top/bluebellgiftstore/627
ኢትዮጵያ የፓኪስታን ባንኮች በአዲስ አበባ ቅርንጫፎቻቸውን እንዲከፍቱ ጥሪ አቀረበች

የኢፌዲሪ አምባሳደር ጀማል በከር አብዱላ የፓኪስታን ባንኮች ከንግድ ጋር የተያያዙ ግብይቶችን ለማካሄድ ቅርንጫፎቻቸውን በአዲስ አበባ እንዲከፍቱ መጠየቃቸውን የሀገሪቱ የዜና ምንጭ ዘግቧል።

አምባሳደሩ ጥሪውን ያቀረቡት በፋይሳላባድ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት (FCCI) ጋር በነበራቸው ንግግር ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስትም የንግድ እንቅስቃሴዎችን ለማደላደል እና የሁለትዮሽ ንግድን ለማቀላጠፍ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

የባንክ ቅርንጫፎችን መክፈት ትልቅ ፈተና እንዳለው የተናገሩት አምባሳደሩ ከተሳካ ግን የሁለትዮሽ ንግድን ለማጠናከር እና የፓኪስታን ላኪዎች ሰፊውን የአፍሪካ ገበያ እንዲያገኙ ያስችላቸዋል ብለዋል።

@TikvahethMagazine
የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት የኢትዮጵያውያን ዜጎች ቪዛ አሰጣጥ ላይ ገደብ ማስቀመጡን አሳወቀ

የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት በኅብረቱ አባል ሀገራት ውስጥ ለኢትዮጵያውያን ዜጎች ቪዛ አሰጣጥ ላይ ገደብ ማስቀመጡን ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።

በዚህም የህብረቱ ለአባል ሃገራት ከዚህ በኋላ ኢትዮጵያውያን ቪዛ አመልካቾች ቪዛ ሲፈልጉ

- አስፈላጊ ሰነዶችን እንዲያቀርቡ እና በአውሮፓ ህብረት ህግ የተቀመጠውን መደበኛ መስፈርቶች እንዲያሟሉ እንደሚገደዱ ተጠቁሟል።

- አባል ሀገራት ከአሁን በኋላ ከሁለት ጊዜ በላይ ወደ ህብረቱ አባል ሀገራት ለመግባት የሚያስችለውን ቪዛ ለኢትዮጵያውያን መስጠት እንደማይችሉም ተገልጿል።

- የዲፕሎማቲክ ወይም የሰርቪስ ፓስፖርት የያዙ ኢትዮጵያውያን ቪዛ ሲፈልጉ መደበኛውን የቪዛ ክፍያ ለመክፈል እንደሚገደዱም ተነግሯል።

በተጨማሪም፣ መደበኛው ቪዛ ለማግኘት የሚጠበቀው የ15 ቀን ጊዜ ወደ 45 ቀን ተቀይሯል።

ይህ ውሳኔ የተወሰነው የህብረቱ ምክር ቤት ባደረገው ግምገማ መሰረት ኢትዮጵያ በህገ-ወጥ መንገድ በአውሮፓ ህብረት የሚቆዩ ዜጎቿን በማስመለስ ረገድ የምታደርገው ጥረት በቂ ባለመሆኑ እንደሆነ ተነግሯል።

@TikvahethMagazine
#NaturalDisaster

በቦሌ ክ/ከተማ የጣለዉን ዝናብ ተከትሎ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት አለፈ

በዛሬው ዕለት ንጋት ላይ በቦሌ ክ/ከተማ በወረዳ 11 ወረገኑ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የጣለዉን ዝናብ ተከትሎ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

የክረምት ወር መግባቱን ተከትሎ በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች 32 ሺሕ አባወራዎች ለጎርፍ አደጋ የተጋለጡ መሆናቸው ሲገለፅ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ፣ አቃቂ ቃሊቲ፣ ልደታ፣ ቂርቆስና አራዳ ክፍለ ከተሞች በተደጋጋሚ ጎርፍ የሚያጠቃቸውና በከፍተኛ የጎርፍ አደጋ ተጋላጭ የሆኑ ቦታዎች መሆናቸው በጥናት ተለይተው ታውቀዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ማስተር ፕላናቸዉን ያልተከተሉ የወንዝ ዳርቻ ግንባታዎች ህብረተሰቡን ለጎርፍ አደጋ እንደሚያጋልጡ በጥናት የለየ ሲሆን ተመሳሳይ አደጋዎች እንዳያጋጥሙ ከከተማ አስተዳደሩና ከእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የሚተላለፉ የጥንቃቄ መልእክቶችን ተግባራዊ እንዲያደርግ መልእክቱን አሰተላልፏል፡፡

@TikvahethMagazine
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን በቤሩት አል ሃሪሪ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ምን ገጠመው?

የሊባኖስ አቬዬሽን ባለስልጣን “ቴል አቪቭ” የተሰኘ መለያ ያለበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ቤይሩት ሲደርስ ተቃውሞ ማሰማቱን የሀገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።

የሀገሪቱ ሲቪል አቬዬሽን ባለስልጣን ቤይሩት ያረፈው የኢትዮጵያ አየር መንገድ 787-9 አውሮፕላን ወደ አዲስ አበባ ከመመለሱ በፊት ምልክቱን እንዲሸፍን አድርጓል።

በተጨማሪም፥ አውሮፕላኖች በቤይሩት ከመድረሳቸው በፊት ሊባኖስ "ጠላቴ ናት" ከምትላት እስራኤል ጋር የተያያዘ ምንም አርማ እንደሌለ ማረጋገጥ እንዳለበት አሳስቧል።

ሊባኖስ ከእስራኤል ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ኖሯት የማያውቅ ሲሆን እንደ ጠላት ሀገር የሚተያዩ ናቸው።

ሁለቱ ሀገራት በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በመሀከለኛው ምስራቅ ባለው ግጭትና የሊባኖስ ታጣቂ ቡድን የሆነው 'ሒዝቦላ' ጋር በሚያደርጉት ውጊያ ቀጠናው እና ሁለቱ ሀገራት የተካረረ ውጥረት ውስጥ መግባታቸው ይታወቃል።

አየር መንገዱ አዳዲስ አውሮፕላን ሲያስገባ አውሮፕላኖቹ የመጀመሪያ በረራ ያደረጉበት የመጀመሪያው ከተማ ስም በውጨኛው ክፍል ላይ ይጻፋል። ይህም የአየር መንገዱ ልምድ ነው።

በዚህ መሰረትም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ4 አመት በፊት ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላኑን ወደ መስመር ሲያስገባ ቅድሚያ የበረረበትን የከተማ ስያሜ ' ቴል አቪቭ ' የሚል የሚል ስያሜ ሰጥቶት ነበር።

@TikvahethMagazine
እንኳን አደረሳችሁ!

ካሉበት ሆነው ለሚወዱት ቤተሰቦ/ወዳጆ ለትንሳዔ እንዲሁም ለዳግመ ትንሳዔ በዓላት ሙሉ #ሥጦታ ከሙሉ #ደስታ ጋር ይላኩ!

ድርጅታችን በ #Platinum , #Golden, #Silver አማራጭ #የበግ ሙክትን ጨምሮ በዓል በዓል የሚሉ ሥጦታዎችን ለሚወዱት ሰው #ባለበት #በተመጣጣኝ ዋጋ ይላኩ። እንደ እናንተው ሆነን እናደርሳለን!

ይደውሉ - 0911359234 (WhatsApp NO.) or 0954882764

ሙሉ ፖኬጁን ይመልከቱ 👉 t.me/bluebellgiftstore

😮 #ለቤተሰቦቻችን_ብቻ: ባለፈው ዓመት ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ስጦታ የላኩ እንዲህ ተደስተዋል 👉https://yangx.top/bluebellgiftstore/627
በ2023 አምስት ምርጥ እንግሊዝኛ ተናጋሪ የአፍሪካ ሀገራት የትኞቹ ናቸው?

"ኢዱኬሽን ፈርስት" የተባለ ዓለማቀፍ የትምህርት ተቋም እድሜአቸው ከ 18 - 20 የሆኑ 2.1 ሚሊዮን ወጣቶችን ከ113 ሀገራት የእንጊሊዘኛ ቋንቋ ችሎታቸውን በመገምገም የሀገራትን የእንግሊዘኛ ቋንቋ ተናጋሪ ብቃት ደረጃ አውጥቷል።

ተቋሙ የቋንቋውን ተናጋሪዎች ብቃት በጣም የላቀ፣ ከፍተኛ፣ መካከለኛ፣ ዝቅተኛ እና በጣም ዝቅተኛ በሚሉ አምስት የብቃት ደረጃዎች በመክፈል ነው ሪፖርቱን ይፋ ያደረገው።

በሪፖርቱ መሰረትም ከ1ኛ እስከ 5ኛ የተቀመጡ የአፍሪካ ሀገራት በቅደም ተከተል፦

🇿🇦 ደቡብ አፍሪካ
🇰🇪 ኬንያ
🇳🇬 ናይጄሪያ
🇬🇭 ጋና
🇺🇬 ኡዳንዳ መሆን ችለዋል።

ከአፍሪካ በቋንቋ ተናጋሪነት ብቃት የመጀመሪያ ደረጃ ላይ የተቀመጠችው ደቡብ አፍሪካ  "#በጣም_የላቀ" በተባለው ከፍተኛ የእንግሊዘኛ ብቃት ያላችው ሀገራት ምድብ ውስጥ ተካትታለች።

2ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠችው ኬንያ እንዲሁም 3ኛዋ ናይጄሪያ "#ከፍተኛ" በተባለው እንዲሁም  ዩጋንዳ እና ጋና "#መካከለኛ" በተባለው የቋንቋ ተናጋሪነት ምድብ ተመድበዋል።

ሀገራችን #ኢትዮጵያ🇪🇹 #ዝቅተኛ የእንጊሊዝኛ ቋንቋ ተናጋሪነት ምድብ ውስጥ ከታንዛኒያ፣ ሞሮኮ፣ አልጄሪያ፣ ማዳጋስካር፣ ማላዊ፣ ግብፅ ጋር መመደቧ በሪፖርቱ ተመላክቷል።

ኔዘርላንድስ፣ ሲንጋፖር፣ ኦስትሪያ፣ ዴንማርክ እና ኖርዌይ ከአለም ከ1 እስከ 5 ያለውን የኢንግሊዝኛ ቋንቋ ተናጋሪነት ብቃት ደረጃ መያዝ ችለዋል።

@TikvahethMagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#እንድታውቁት

ነገ ረቡዕ ሚያዚያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም በአለም አቀፍ ደረጃ የሠራተኞች ቀን የሚከበርበት ቢሆንም፤ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከዋናው መስሪያ ቤት እስከ አገልግሎት መስጫ ማዕከሎቹ ድረስ በሚገኙ ሁሉም ቢሮዎች ሁሉንም አገልግሎቶቹን እስከ ቀኑ 11፡00 ድረስ የሚሰጥ መሆኑን አሳውቋል።

@TikvahethMagazine
#CholeraUpdate

በኢትዮጵያ ባለፈው ወር ከአፍሪካ ሀገራት ከፍተኛ የኮሌራ ታማሚዎች ቁጥር እንደተመዘገበ ተነገረ

በአፍሪካ ባለፈው መጋቢት ወር በኮሌራ በሽታ ከተያዙ 14,441 አዲስ የኮሌራ ታማሚዎች መሃከል ከአህጉሪቱ ከፍተኛ ታማሚዎች የተመዘገቡባት ኢትዮጵያ መሆኗን የአለም ጤና ድርጅት ሪፖርት አመልክቷል።

በተጠቀሰው ወር በኢትዮጵያ 4009 ሰዎች በኮሌራ መያዛቸው ተነግሯል። በኮሌራ ከተያዙት ሰዎች ውስጥም 24 ሰዎች መሞታቸው ተጠቁሟል። በኢትዮጵያ ባለፉት 3 ወራት 9,429 ሰዎች በኮሌራ ተይዘው 111 ሰዎች መሞታቸውንም ሪፖርቱ አመልክቷል።

በአፍሪካ ከጃንዋሪ 1 ቀን 2023 እስከ ማርች 31 ቀን 2024 በጠቅላላው በ18 ሀገራት 271,119 ሰዎች በኮሌራ በሽታ ሲያዙ በተጠቀሰው ጊዜ በኢትዮጵያ 39,892 ሰዎች በበሽታው ተይዘው 524 ሰዎች መሞታቸውም ነው የተገለፀው።

@TikvahethMagazine
ከታላቁ ህዳሴ ግድብ በቀን እስከ 250 ኪሎ ግራም የሚደርስ ዓሳ እየተገኘ ነው ተባለ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከዚህ ቀደም ታጥቀው ይንቀሳቀሱ የነበሩና ሌሎች ወጣቶች በ2 ማኅበር ተደራጅተው በጀመሩት የዓሳ ማስገር ስራ ከህዳሴ ግድብ በቀን እስከ 250 ኪሎ ግራም የሚደርስ ዓሳ እየተገኘ መሆኑ ተገለፀ።

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ሐይቅ ግድቡ ውሀ መያዝ ከጀመረ ወዲህ በተለይም ለዓሳ ምርት ምቹ መሆኑ ሲገር በ8 ወራት ውስጥ 1729 ቶን ዓሳ ምርት ከህዳሴ ግድብ መገኘቱን ዶይቼ ቨለ በዘገባው አመልክቷል።

ወጣቶቹ የተደራጁበት ማህበርም 56 የሚደርሱ ወጣቶችን ያቀፈ ሲሆን በግደቡ ዳርቻ በሚሰሩት የዓሳ ማስገር ስራ በቀን ከ2 እስከ 3 ኩንታል ዓሳ እንደሚኝና በአካባቢው የዓሳ ማስገር ስራውን በማህበሰረብ አቀም ለማድረግና ለማሻሻል ዘመናዊ ጅልባዎች ያስፈልጋሉ ተብሏል።

@TikvahethMagazine
እንኳን አደረሳችሁ!

ካሉበት ሆነው ለሚወዱት ቤተሰቦ/ወዳጆ ለትንሳዔ እንዲሁም ለዳግመ ትንሳዔ በዓላት ሙሉ #ሥጦታ ከሙሉ #ደስታ ጋር ይላኩ!

ድርጅታችን በ #Platinum , #Golden, #Silver አማራጭ #የበግ ሙክትን ጨምሮ በዓል በዓል የሚሉ ሥጦታዎችን ለሚወዱት ሰው #ባለበት #በተመጣጣኝ ዋጋ ይላኩ። እንደ እናንተው ሆነን እናደርሳለን!

ይደውሉ - 0911359234 (WhatsApp NO.) or 0954882764

ሙሉ ፖኬጁን ይመልከቱ 👉 t.me/bluebellgiftstore

😮 #ለቤተሰቦቻችን_ብቻ: ባለፈው ዓመት ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ስጦታ የላኩ እንዲህ ተደስተዋል 👉https://yangx.top/bluebellgiftstore/627
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
"የዓለም ባንክ የአፍሪካ ሀገራትን መዋቅራዊ ችግሮች ከመደገፍ ለሴሚናር ገንዘብ ማውጣት ይቀለዋል" የኡጋንዳው ፕሬዝደንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ

የኡጋንዳው ፕሬዝደንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ የዓለም ባንክ ድሃ የአፍሪካ ሀገራት ለዕድገታቸው እንቅፋት የሆኑ የእርሻ፣ ትራንስፖርትና መሰል መዋቅራዊ ችግሮችን እንዲፈቱ ብድር ከመስጠት ይልቅ ለሚዘጋጁት ‘ሴሚናሮች’ ብድር ቅድሚያ ይሰጣል ሲሉ ወቀሳ ሰነዘሩ።

ፕሬዝዳንቱ ይህንን ያሉት በኬኔያ በተካሄደው የአለም አቀፍ ልማት ማህበር የአፍሪካ ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ነው። " አለም ባንክ ሰዎች ተቀምጠው ለሚመገቡት ሴሚናሮች  ብድር ለመስጠት ፈጣን ናቸው። ነው ነገር ግን የመስኖ እና የመሠረተ ልማት ልማትን አይደግፉም " ሲሉ ወቅሰዋል።

ፕሬዝዳንቱ አፍሪካ ዘላቂ ልማት (Sustainable underdevelopment) አያስፈልጋትም አፍሪካ የምትፈልገው ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ለውጥ (Socio-Economic Transformation) ነው ያሉ ሲሆን ዘላቂ ልማትን የሚባለውን ፅንሰ ሀሳብ እድገት የሌለው ሲሉ ገልጸውታል።

"አንድ ሴት በዚህ ዓመት ካረገዘች በሚቀጥሉት ሦስት እና አራት ዓመታት እርጉዝ አትሆንም፥ ይህ ፈጽሞ አይፈጠርም ተፈጥሯዊው እድገት ለወራት ታረግዛለች ልጁ ያድጋል፤ ይወለዳል፤ ይጎለምሳል። የሆነ ምዕራፍ ላይ እርግዝናው (Quantitative) ወደ ልጅነት ይቀየራል (Qualitative) እነዚህን ቃላት በዶክመንታችሁ አስተካክሏቸው።" ሲሉ ገልጸዋል።

ፕሬዚደንት ሙሴቬኒ አክለውም፥ አፍሪቃ የጥሬ ዕቃዎቿን ወደ ውጭ መላክ እንድታቆም የጠየቁ ሲሆን ጥሬ እቃ ላይ እሴት ሳይጨመር መላክ በአፍሪካዊያን ሀብት ሌሎችን ማበልጸግ እንደሆነ የቡና እና የማዕድን ሀብትን በምሳሌ አንስተው አስረድተዋል።

"ኡጋንዳ ሀብታም ሀገር ብትሆንም አብዛኞቹ ዜጎቿ ለዕለት ጉርስ እንጂ ለኪስ የሚሆን ገንዘብ ከሚያገኙበትን ሥርዓት ( Money Economy) ውጪ ናቸው። ይህንን ለመቅረፍ ገንዘብ የሚሰጠኝ የለም ምክንያቱም ሁሉም ገንዘብ ለአቅም ማጎልበቻ (Capacity Building ) ነው። እኛ ግን በራሳችን ፈንድ እየሰራን ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

በአፍሪካ የግሉ ዘርፍ እየተደገፈ ባለመሆኑ እድገት እየተመዘገበ እንዳልሆነ የገለፁት ሙሴቬኒ የግሉ ዘርፍ እንዲበረታታ በቅድሚያ በአነስተኛ ዋጋ ማምረት መቻል ለዚህም ደግሞ  የመንገድ የኤሌክትሪክ ሀይል ያስፈልጋል ሲሉ ጠቅሰው የዓለም ባንክ ለእነዚህ ነገሮች ፈንድ ያደረገበትን ኦዲት ያድርግ ሲሉ ጠቅሰዋል።

(📹 28 MB)

@TikvahethMagazine
ልጆች 13 ዓመት እስኪሞላቸው ድረስ ስማርት ስልኮችን ባይጠቀሙ ሲል በፈረንሳይ የተሰራ ጥናት አመለከተ።

በተለያየ የእድሜ ደረጃ ላይ ያሉ ህፃናት እና ታዳጊዎች ስማርት ስልኮችን በመጠቀም የተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾችን ሲጠቀሙ አለፍ ሊልም በነዚህ የትስስር ገጾች ላይ ተሳትፎ ሲያደርጉ ይስተዋላል።

የስማርት ስልክ አጠቃቀም ጥንቃቄ የሚያስፈልገው እንደሆነ ቢነገርም ሀገራችን ኢትዮጵያ ጨምሮ ስማርት ስልኮች ላይ የሚገኙት የማህበራዊ ትስስር ገጾች ህፃናትና ታዳጊዎችን ለሱስ ከመዳረግ ባለፈ በልጆች ላይ ስነልቦናዊ ጉዳት እያስከተለ ስለመሆኑ ይነገራል።

ጉዳዩን አስመልክቶ በፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ማክሮን ሀሳብ አመንጪነት ታዳጊ ልጆችን ከአደጋ ለመጠበቅ ኒውሮሎጂስት እና የዘርፉ ባለሙያዎች የስልክ ስክሪን አጠቃቀም መመሪያዎችን ለመንግስት እንዲጠቁሙ  በማሰብ 3 ወራትን የፈጀ ጥናት ተሰርቷል።

በጥናቱም ልጆች 13 አመት እስኪሞላቸው ድረስ ስማርት ስልኮችን እንዲጠቀሙ መፈቀድ እንደሌለበትና እንደ #ቲክቶክ#ኢንስታግራም እና #ስናፕቻት የመሳሰሉ ማህበራዊ ሚዲያዎችን እስከ 18 አመት ድረስ መጠቀም እንደሌለባቸው ጥናቱ አመልክቷል።

ጥናቱም ከ3 አመት በታች ያሉ ህጻናት የቴሌቪዥን ስክሪኖች ጨምሮ ለስልኮች ተጋላጭ መሆን እንደሌለባቸው የጠቆመ ሲሆን አንድ ህፃን 11 ዓመት ሳይሞላው ስልክ ሊኖረው እንደማይገባና ይህ ካልሆነ ህፃናት በልጅነታቸው ስሜታቸውን ከመግለፅ እና ነገሮችን ከመረዳት አኳያ ሊያዳብሯቸው የሚገባቸውን ችሎታዎች ሊጎዳ እንደሚችል ተገልጿል።

የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ማክሮን ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በጥር ወር ህፃናትን ላይ ጉዳት እየዳረገ ስለሚገኘው የስማርት ስልክ እንዲሁም የስክሪን አጠቃቀም " እገዳዎች ወይም ገደቦች " ሊኖሩ ይችላሉ ማለታቸውም ነው የተነገረው።

ይህ ጥናት በኢትዮጵያ ካለው የህፃናትና ታዳጊዎች ስማርት ስልክ አጠቀም አንፃር እንዴት ይታያል?

@TikvahethMagazine