TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
2021.04.19_MUSE_REPORT.pdf
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#EmmanuelMacron

የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ሩዋንዳ ይገኛሉ።

በ1994 ሩዋንዳ ውስጥ በነበረው አስከፊ የ "ዘር ጭፍጨፋ" ወቅት ፈረንሳይ 'ኃላፊነቷን' መወጣት አለመቻሏን/በጭፍጨፋው የነበራትን ሚና በይፋ እዉቅና ሰጥተዋል።

ፕሬዜዳንቱ እውቅናውን የሰጡት በኪጋሊ የዘር ማጥፋት መታሰቢያ ባደረጉት ንግግር ነው።

በወቅቱ የዘር ማጥፋት አገዛዝን ከመደገፍ አንስቶ ከጭፍጨፋው ጋር በተገናኘ የቅድመ ማስጠንቀቂያ መልዕክቶችን ፈረንሳይ ችላ ብላ ነበር ብለዋል።

ፕሬዜዳትቱ ባደረጉት ንግግር ላይ ግልፅ እና ይፋዊ ይቅርታ አልጠየቁም።

ማክሮን ባሰሙት ንግግር ፥ ፈረንሳይ የዘር ጭፍጨፋው ተባባሪ አይደለችም ያሉ ሲሆን በወቅቱ ሀገሪቱ ለነበራት ኃላፊነት ፈረንሳይን ይቅር ሊሉ የሚችሉት ከአስከፊው ጭፍጨፋ የተረፉት ሩዋንዳውያን ናቸዉ ብለዋል።

የሩዋንዳው ፕሬዜዳንት ፖል ካጋሜ ፤ የማክሮን ቃላቶች ከይቅርታም የበለጠ ዋጋ ያላቸው ነበሩ ሲሉ ገልፀዋል።

ከአንድ ወር በፊት በሩዋንዳ በ100 ቀን ውስጥ ብቻ 800 ሺ ገደማ ቱትሲዎች በተጨፈጨፉበት የ1994ቱ የሩዋንዳ ጭፍጨፋ ፈረንሳይ የተባባሪነት ሚና እንደነበራት የሚያመለክት የምርመራ ሪፖርት ይፋ ሆኖ እንደነበር አይዘነጋም።

@tikvahethiopia