TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray ከዓመታት በኃላ በትግራይ ያሉ #ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው ለመመለስ ምዝገበ እየተካሄደ ይገኛል። የትግራይ ትምህርት ቢሮ ለዓመታት በኮቪድ-19 እና በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የቆየውን መደበኛ ትምህርት ለማስጀመር ከሚያዚያ 18 ጀምሮ ምዝገባ እንደሚከናወን እና ሚያዚያ 23 ትምህርት እንደሚጀመር ማሳወቁ የሚዘነጋ አይደለም። ተማሪዎች ያለፋቸውን ጊዜ ለማካካስ በሳምንት 3 የትምህርት…
#ትግራይ
በትግራይ ክልል ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት ተመለሱ።
ላለፉት ዓመታት በትግራይ ክልል አንድም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ በኃላም በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የቆየው ትምህርት ዛሬ ሚያዚያ 23 ቀን 2015 ዓ/ም በተለያዩ ትምህርት ቤቶች ተጀምሯል።
የትግራይ ትምህርት ቢሮ ትምህርት የሚጀመረው ሁሉ ነገር ተሟልቶ ፤ ችግሮች ሁሉ ተፈተው ሳይሆን ትውልድን ለማስቀጠል ሲባል መሆኑን ከዚህ ቀደም አሳውቆ ነበር።
ዛሬ ትምህርት ከተጀመረባቸው ት/ቤቶች መካከል የኤርትራ ጦር ከፍተኛ ጉዳት እንዳደረሰበት የተነገረው " ማይመኸደን የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት እንዲሁም በእንደርታ ወረዳ የሚገኘው ሓሬና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ይጠቀሳሉ።
ምንም እንኳን በርካታ ችግሮች ያሉ ቢሆንም በተማሪዎች ሆነ በወላጆች ዘንድ ትምህርት መጀመሩ ደስታን እና ተስፋን ፈጥሯል።
በትግራይ 85 በመቶ ትምህርት ቤቶች ከባድ ወይም ከፊል ጉዳት ደርሶባቸዋል ፤ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ባለው ነገር ትምህርት ቢጀምሩም አሁንም የተለያዩ ትምህርት ቤቶች ተፈናቃይ ዜጎችን አስጠልለው ይገኛሉ።
ፎቶ ፦ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት
#BringTigrayChildrenBacktoSchool
@tikvahethiopia
በትግራይ ክልል ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት ተመለሱ።
ላለፉት ዓመታት በትግራይ ክልል አንድም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ በኃላም በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የቆየው ትምህርት ዛሬ ሚያዚያ 23 ቀን 2015 ዓ/ም በተለያዩ ትምህርት ቤቶች ተጀምሯል።
የትግራይ ትምህርት ቢሮ ትምህርት የሚጀመረው ሁሉ ነገር ተሟልቶ ፤ ችግሮች ሁሉ ተፈተው ሳይሆን ትውልድን ለማስቀጠል ሲባል መሆኑን ከዚህ ቀደም አሳውቆ ነበር።
ዛሬ ትምህርት ከተጀመረባቸው ት/ቤቶች መካከል የኤርትራ ጦር ከፍተኛ ጉዳት እንዳደረሰበት የተነገረው " ማይመኸደን የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት እንዲሁም በእንደርታ ወረዳ የሚገኘው ሓሬና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ይጠቀሳሉ።
ምንም እንኳን በርካታ ችግሮች ያሉ ቢሆንም በተማሪዎች ሆነ በወላጆች ዘንድ ትምህርት መጀመሩ ደስታን እና ተስፋን ፈጥሯል።
በትግራይ 85 በመቶ ትምህርት ቤቶች ከባድ ወይም ከፊል ጉዳት ደርሶባቸዋል ፤ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ባለው ነገር ትምህርት ቢጀምሩም አሁንም የተለያዩ ትምህርት ቤቶች ተፈናቃይ ዜጎችን አስጠልለው ይገኛሉ።
ፎቶ ፦ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት
#BringTigrayChildrenBacktoSchool
@tikvahethiopia