TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray ከዓመታት በኃላ በትግራይ ያሉ #ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው ለመመለስ ምዝገበ እየተካሄደ ይገኛል። የትግራይ ትምህርት ቢሮ  ለዓመታት በኮቪድ-19 እና በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የቆየውን መደበኛ ትምህርት ለማስጀመር ከሚያዚያ 18 ጀምሮ ምዝገባ እንደሚከናወን እና ሚያዚያ 23 ትምህርት እንደሚጀመር ማሳወቁ የሚዘነጋ አይደለም። ተማሪዎች ያለፋቸውን ጊዜ ለማካካስ በሳምንት 3 የትምህርት…
#ትግራይ

በትግራይ ክልል ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት ተመለሱ።

ላለፉት ዓመታት በትግራይ ክልል አንድም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ በኃላም በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የቆየው ትምህርት ዛሬ ሚያዚያ 23 ቀን 2015 ዓ/ም በተለያዩ ትምህርት ቤቶች ተጀምሯል።

የትግራይ ትምህርት ቢሮ ትምህርት የሚጀመረው ሁሉ ነገር ተሟልቶ ፤ ችግሮች ሁሉ ተፈተው ሳይሆን ትውልድን ለማስቀጠል ሲባል መሆኑን ከዚህ ቀደም አሳውቆ ነበር።

ዛሬ ትምህርት ከተጀመረባቸው ት/ቤቶች መካከል የኤርትራ ጦር ከፍተኛ ጉዳት እንዳደረሰበት የተነገረው " ማይመኸደን የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት እንዲሁም በእንደርታ ወረዳ የሚገኘው ሓሬና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ይጠቀሳሉ።

ምንም እንኳን በርካታ ችግሮች ያሉ ቢሆንም በተማሪዎች ሆነ በወላጆች ዘንድ ትምህርት መጀመሩ ደስታን እና ተስፋን ፈጥሯል።

በትግራይ 85 በመቶ ትምህርት ቤቶች ከባድ ወይም ከፊል ጉዳት ደርሶባቸዋል ፤ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ባለው ነገር ትምህርት ቢጀምሩም አሁንም የተለያዩ ትምህርት ቤቶች ተፈናቃይ ዜጎችን አስጠልለው ይገኛሉ።

ፎቶ ፦ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት

#BringTigrayChildrenBacktoSchool

@tikvahethiopia