TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#BATI

ከአማራ ክልል በባቲ ወረዳ የተሰባሰቡ 92 ታዳጊ ህጻናትና ወጣቶችን በሕገ ወጥ መንገድ ከአገር ለማስወጣት የሞከሩ ሁለት ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ።

በፌዴራል ፖሊስ የ3ኛ ሻምበል ዋና አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ሞገስ ከበደ እንደገለጹት ግለሰቦቹ የተያዙት በሕገ ወጥ መንገድ ሰዎቹን ጭነው ወደ መካከለኛው ምሥራቅ አገሮች ለማሸጋገር ሲሞክሩ ነው።

በወንጀል የተጠረጠሩት ግለሰቦች ለማምለጥ ሙከራ ቢያደርጉም፤ ኅብረተሰቡ ባደረገው ትብብር ዋና አዘዋዋሪውና ረዳት አሽከርካሪው መያዛቸውን ተናግረዋል።

መንገደኞቹ የተሰባሰቡት ከሰሜንና ደቡብ ወሎ፣ ሰሜን ሸዋ፣ ዋግ ኸምራ ብሄረሰብና ኦሮሞ ብሄረሰብ ዞኖች መሆኑንም አስረድተዋል። ወጣቶቹ  ሲጓጓዙ የነበሩት የጅቡቲ ሰሌዳ  844 ዲ64 የጭነት መኪና እንደነበርም ዋና አዛዡ ገልጸዋል።

Via ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia