TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የተቋረጠው #የባጃጅ_ትራንስፖርት አገልግሎትን አስመልከቶ ዛሬ መጋቢት 8/2015 ዓ.ም መግለጫ ይሰጣል ተብሏል።

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ዛሬ ከሰዓት 9 ሰዓት የካቲት 30 ቀን 2015 ዓ.ም የተቋረጠውን የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ መግለጫ እንደሚሰጥ " አሻም ቴሌቪዥን " ዘግቧል።

የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት መቋረጡን ተከትሎ አሽከርካሪዎች የዕለቱ ጉርሳቸውን ማጣታቸውን፣ ተጠቃሚዎችም ለከፍተኛ እንግልት መዳረጋቸውን እየገለፁ እንደሚገኙ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን /ኢሰመኮ ትላንት ባወጣው መግለጫ የባጃጅ ትራንስፖርት እገዳው እንዲነሳ መጠየቁ ይታወሳል፡፡

Credit : #AshamTV

@tikvahethiopia