በእነብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞ የክስ መዝገብ ላይ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ!
በእነብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞ የክስ መዝገብ ላይ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ። መዝገቡን በሚገባ በመመርመር ትክክለኛ ውሳኔ ለመስጠት ተጨማሪ መረጃ ስለሚያስፈልግ በማለት የባሕር ዳር ከተማና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለነሃሴ 21/ 2011 ዓ.ም ጠዋት 3:00 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። የተጠርጣሪዎች #ጠበቆች ከምርመራ ሂደቱ ጋር በቀጥታ ተያያዥነት የሌላቸው የባንክ ደብተርና አልባሳት እንዲመለሱላቸዉ ለፍርድ ቤቱ ጥያቄ አቅርበዋል።
የምርመራ ቡድኑም አልባሳትም ሆነ የባንክ ደብተር ለተጠርጣሪዎች ቢመለስላቸው እንደማይቃወም ገልጿል፤ ነገር ግን አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ሂሳብ ደብተር ላይ ያለው ገንዘብ እንዳይንቀሳቀስ ማድረግ ይቻላል ብሏል። ፍርድ ቤቱም ተጠርጣሪዎቹና ቤተሰቦቻቸው ሌላ ምንም አይነት የገቢ ምንጭ ከሌላቸው የባንክ ደብተሩ እንዲሁም አልባሳቱም በህግ አግባብ ሊሰጣቸው ይገባል በሚል ወስኗል።
Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በእነብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞ የክስ መዝገብ ላይ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ። መዝገቡን በሚገባ በመመርመር ትክክለኛ ውሳኔ ለመስጠት ተጨማሪ መረጃ ስለሚያስፈልግ በማለት የባሕር ዳር ከተማና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለነሃሴ 21/ 2011 ዓ.ም ጠዋት 3:00 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። የተጠርጣሪዎች #ጠበቆች ከምርመራ ሂደቱ ጋር በቀጥታ ተያያዥነት የሌላቸው የባንክ ደብተርና አልባሳት እንዲመለሱላቸዉ ለፍርድ ቤቱ ጥያቄ አቅርበዋል።
የምርመራ ቡድኑም አልባሳትም ሆነ የባንክ ደብተር ለተጠርጣሪዎች ቢመለስላቸው እንደማይቃወም ገልጿል፤ ነገር ግን አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ሂሳብ ደብተር ላይ ያለው ገንዘብ እንዳይንቀሳቀስ ማድረግ ይቻላል ብሏል። ፍርድ ቤቱም ተጠርጣሪዎቹና ቤተሰቦቻቸው ሌላ ምንም አይነት የገቢ ምንጭ ከሌላቸው የባንክ ደብተሩ እንዲሁም አልባሳቱም በህግ አግባብ ሊሰጣቸው ይገባል በሚል ወስኗል።
Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia