#update ከሶማሌ ላንድ ተነስተው በቶጎጫሌ ወደ ጅግጅጋ ሲያመሩ የነበሩ ኮድ-04046፣ ኮድ-05759 ሁለት ቅጥቅጥ አይሱዙዎች እና ኮድ-39416 የጭነት ተሸከርካሪ ግምታዊ ዋጋቸዉ 550ሺ ብር በላይ የሚያወጡ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ፤ ምግብ ነክ፣ ጨርቃ ጨርቅ እና ሌሎች እቃዎችን ጭነዉ በህገወጥ መንገድ ወደ ጅግጅጋ ለመግባት ሲሞክሩ በፌደራልና በክልል ፖሊሶች እንዲሁም በጉምሩክ ሰራተኞች ክትትል ታህሳስ 23/2011 ዓ.ም ከቀኑ 11፡30 እስከ ምሽት 2 ሰዓት ባለዉ ጊዜ በቁጥጥር ስር መዋላቸዉን በጉምሩክ ኮሚሽን የጅግጅጋ ቅ/ጽ/ቤት አስታዉቋል፡፡ የቅ/ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ #ደመላሽ_ተሾመ አያይዘዉ እንደገለጹትም በድርጊቱ ተሳታፊ የነበረዉ ግለሰብ #በቁጥጥር ስር ዉሎ አስፈላጊዉ ምርመራ እየተደረገበት ሲሆን ሌሎች ተጠርጣሪዎችንም በቁጥጥር ስር ለማዋል ክትትሉ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዉ በቀጣይም ህብረተሰቡ ይሄን መሰል ድርጊቶች በንቃት በመከታተል ለሚመለከታቸው አካላት ጥቆማ እንዲያደርግ ጥሪያቸውን አቅርበዋል ሲል የገቢዎች ሚኒስቴር ገልጿል፡፡
Via~EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via~EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia