TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
61.7K photos
1.56K videos
216 files
4.28K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#update እንግሊዝ ማንኛዉም #የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖች በግዛቷ እንዳይበሩ መከልከሏን አስታወቀች፡፡ ዉሳኔዉን ተከትሎ አየር ላይ የነበሩ 2 የቱርክ አየር መንገድ ንብረት የሆኑ ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደርጓል፡፡ አውሮፕላኖቹ ከኢስንታቡል አውሮፕላን ማረፊያ ተነስተው ወደ በርሚንግሃምና ጋትዊክ ሲበሩ ነበር፡፡ ወደ በርሚንገሃም ሲበር የነበረው የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ከአራት ሰዓታት በረራ ዉስጥ 3 ሰዓቱን በመብረር ምዕራብ ጀርመን ፍራንክፈርት ደርሶ እንደነበር ነው የተገለፀው። ወደ የጋትዊክ ሲበር የነበረው ደግሞ ጉዞውን ከግማሽ በላይ ሸፍኖ ቼክ ሪፐብሊክ ከደረሰ በኋላ ነው እንዲመለስ የተደረገው፡፡ ምንም እንኳን የእንግሊዝ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን እቀባዉን የጣለው ሁለቱ የቱርክ የቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላኖች በረራ ከጀመሩ በኋላ ቢሆንም ህጉን ወዲያው ተግባራዊ በማድረግ አውሮፕላኖቹ ወደ ተነሱበት እንዲመለሱ አድርጓል፡፡ የቱርክ አየር መንገድ ለተጓዦች ሌሎች የበረራ አማራጮችን በማቅረብ ችግሩን እንደሚፈታ ይጠበቃል፡፡

ምንጭ፡- ኢንዲፔንደንት
@tsegabwolde @tikvahethiopia