TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#ባቲ

ወደ ባቲ ከተማ የተሽከርካሪዎች መግቢያ እና መውጫ የሰዓት እላፊ ገደብ ተግባራዊ እየተደረገ ነው።

ይህ የሰዓት እላፊ ገደብ ከጥቅምት 17 ጀምሮ ነው ተግባራዊ የሆነው።

የባቲ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ም/ ቤት ለአጠቃላይ ተሽከርካሪዎች ወደ ባቲ ከተማ አስ/ር መግቢያና መውጫ ያስቀመጠው የሰአት እላፊ ገደብ ከ12፡00 ጀምሮ ሲሆን ከዚህ ሰዓት በኃላ ወደ ባቲ ከተማ መግባትም ሆነ መውጣት አይቻልም (ይህ ባለሶስት እግር ተሽከርካሪ /ባጃጅ/ ጨምሮ ነው) ።

ውስጥ ለውጥ ተሽከርካሪ ማንቀሳቀስም በጥብቅ የተከለከለ ነው።

ተግባራዊ እየሆነ ያለው የሰዓት እላፊ ገደብ የፀጥታ አካላት የሚጠቀሙባቸው ተሽከርካሪዎችን አይጨምርም።

ገደቡን በሚጥስ አካል ላይ ጠበቅ ያለ እርምጃ የሚወሰድ ሲሆን ሁሉም አካል ለሰላሙ ሲል ይህንን የሰዓት እላፊ ገደብ እንዲያከብር መልዕክት ተላልፏል።

@tikvahethiopia