#ባቲ
ወደ ባቲ ከተማ የተሽከርካሪዎች መግቢያ እና መውጫ የሰዓት እላፊ ገደብ ተግባራዊ እየተደረገ ነው።
ይህ የሰዓት እላፊ ገደብ ከጥቅምት 17 ጀምሮ ነው ተግባራዊ የሆነው።
የባቲ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ም/ ቤት ለአጠቃላይ ተሽከርካሪዎች ወደ ባቲ ከተማ አስ/ር መግቢያና መውጫ ያስቀመጠው የሰአት እላፊ ገደብ ከ12፡00 ጀምሮ ሲሆን ከዚህ ሰዓት በኃላ ወደ ባቲ ከተማ መግባትም ሆነ መውጣት አይቻልም (ይህ ባለሶስት እግር ተሽከርካሪ /ባጃጅ/ ጨምሮ ነው) ።
ውስጥ ለውጥ ተሽከርካሪ ማንቀሳቀስም በጥብቅ የተከለከለ ነው።
ተግባራዊ እየሆነ ያለው የሰዓት እላፊ ገደብ የፀጥታ አካላት የሚጠቀሙባቸው ተሽከርካሪዎችን አይጨምርም።
ገደቡን በሚጥስ አካል ላይ ጠበቅ ያለ እርምጃ የሚወሰድ ሲሆን ሁሉም አካል ለሰላሙ ሲል ይህንን የሰዓት እላፊ ገደብ እንዲያከብር መልዕክት ተላልፏል።
@tikvahethiopia
ወደ ባቲ ከተማ የተሽከርካሪዎች መግቢያ እና መውጫ የሰዓት እላፊ ገደብ ተግባራዊ እየተደረገ ነው።
ይህ የሰዓት እላፊ ገደብ ከጥቅምት 17 ጀምሮ ነው ተግባራዊ የሆነው።
የባቲ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ም/ ቤት ለአጠቃላይ ተሽከርካሪዎች ወደ ባቲ ከተማ አስ/ር መግቢያና መውጫ ያስቀመጠው የሰአት እላፊ ገደብ ከ12፡00 ጀምሮ ሲሆን ከዚህ ሰዓት በኃላ ወደ ባቲ ከተማ መግባትም ሆነ መውጣት አይቻልም (ይህ ባለሶስት እግር ተሽከርካሪ /ባጃጅ/ ጨምሮ ነው) ።
ውስጥ ለውጥ ተሽከርካሪ ማንቀሳቀስም በጥብቅ የተከለከለ ነው።
ተግባራዊ እየሆነ ያለው የሰዓት እላፊ ገደብ የፀጥታ አካላት የሚጠቀሙባቸው ተሽከርካሪዎችን አይጨምርም።
ገደቡን በሚጥስ አካል ላይ ጠበቅ ያለ እርምጃ የሚወሰድ ሲሆን ሁሉም አካል ለሰላሙ ሲል ይህንን የሰዓት እላፊ ገደብ እንዲያከብር መልዕክት ተላልፏል።
@tikvahethiopia