TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
የጋዜጠኞች ግድያ ... #በ2021

የጎርጎሮሳውያኑ 2021 ተጠናቆ ከትላንት ጀምሮ አዲሱ ዓመት 2022 ገብቷል።

በተሰናበተው 2021 በመላው ዓለም 45 ጋዜጠኞች ተገድለዋል።

የዓለም አቀፍ ጋዜጠኞች ፌዴሬሽን እንዳስታወቀው በ2021 የተመዘገበው የጋዜጠኞች ግድያ ከየትኛውም አመት ከተመዘገበው ዝቅተኛ ቁጥር አንዱ ነው ብሏል።

በአንድ ሀገር ከፍተኛ የተመዘገበው አፍጋኒስታን ውስጥ ሲሆን 9 ጋዜጠኞች ተገድለዋል እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ ግድያ የተመዘገበባቸው በሜክሲኮ 8 ፣ በህንድ 4 ፣ በፓኪስታን 3 እንደሆነ ተገልጿል።

አፍጋኒስታንን የሚያጠቃልለው ኤዥያ-ፓሲፊክ አካባቢ 20 ግድያዎች የተመዘገቡበትና ከፍተኛው ሲሆን አሜሪካ 10 ፣ አፍሪካ 8 ፣ አውሮፓ 6 እና መካከለኛው ምስራቅ እና አረብ ሀገራት 1 ተመዝግቧል።

በኢራን በደረሰ “አሰቃቂ አደጋ” የ2 ጋዜጠኞች ሞትም ጠቅሷል።

@tikvahethiopia