TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#update የመከላከያ ሚኒስትር ክብርት ኢንጂነር #አይሻ_መሃመድ በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ አዲስ ከተሾሙት የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ አምባሳደር መሀመድ #ሳሊም_አልራሺዲ ጋር በፅ/ቤታቸው ተነጋግረዋል፡፡ አምባሳደር መሃመድ በዚሁ ወቅት የሁለቱን አገሮች ግንኙነቶች በማሳደግ በኩል ጠንክረው እንደሚሰሩ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል፡፡ በተለይም በአቅም ግንባታ ዘርፍ ተቋሙን ለማገዝ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸውም ተናግረዋል፡፡ ክብርት ሚኒስትሯም ሁለቱ አገራት ያላቸው የረጅም ጊዜ ግንኑኙት ዘመናትን የተሻገረ መሆኑን ገልፀው አምባሳደር መሀመድ በኢትዮጵያ ውጤታማ የቆይታ ጊዜያት እንዲኖራቸው ተመኝተዋል፡፡

Via Defense Minister Office, Ethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia