#AddisAbaba
ምንነቱ ያልታወቀ #ስራስር እና #ሰጋቱራ ከጤፍ ዱቄት ጋር ቀላቅለው ሲያከፋፍሉ የነበሩ ተጠርጣሪዎች ተያዙ።
ከጤፍ ዱቄት ጋር የተለያዩ ባዕድ ነገሮችንና የእንጨት ፍቅፋቂ (ሰጋቱራ) በመቀላቀል ለህብረተሰቡ ሊያከፋፍሉ የነበሩ ግለሰቦችን በህብረተሰቡ ትብብር በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።
ህገ-ወጥ ተግባሩ ሲፈፀም የነበረው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 በተለምዶ አጠራሩ ቆሼ ድልድይ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በአንድ መጋዘን ውስጥ ነው።
በመጋዘኑ ውስጥ 47 ኩንታል ምንነቱ ያልታወቀ ስራስር፤ የእንጨት ፍቅፋቂ (ሰጋ ቱራ) እና 167 ኩንታል የጤፍ ዱቄት ተከማችቶ የተገኘ ሲሆን ባዕድ ነገሩን ከዱቄቱ ጋር የሚደባልቅ መጋዘኑ ውስጥ እንዳይወጣ የተቆለፈበት ሠራተኛ በፍተሻ መገኘቱን ፖሊስ አስታውቋል።
ከአካባቢው ማህበረሰብ በደረሰው ጥቆማ መሰረት የጅማ በር አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ በህግ አግባብ ባደረገው ድንገተኛ ፍተሻ በስራ ላይ የነበረውን ተጠርጣሪ እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ስር አውሎ ባደረግው ተጨማሪ ምርመራ የንብረቱን ባለቤትን አፈላልጎ በመያዝ ተገቢው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።
Via @tikvahethmagazine
ምንነቱ ያልታወቀ #ስራስር እና #ሰጋቱራ ከጤፍ ዱቄት ጋር ቀላቅለው ሲያከፋፍሉ የነበሩ ተጠርጣሪዎች ተያዙ።
ከጤፍ ዱቄት ጋር የተለያዩ ባዕድ ነገሮችንና የእንጨት ፍቅፋቂ (ሰጋቱራ) በመቀላቀል ለህብረተሰቡ ሊያከፋፍሉ የነበሩ ግለሰቦችን በህብረተሰቡ ትብብር በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።
ህገ-ወጥ ተግባሩ ሲፈፀም የነበረው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 በተለምዶ አጠራሩ ቆሼ ድልድይ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በአንድ መጋዘን ውስጥ ነው።
በመጋዘኑ ውስጥ 47 ኩንታል ምንነቱ ያልታወቀ ስራስር፤ የእንጨት ፍቅፋቂ (ሰጋ ቱራ) እና 167 ኩንታል የጤፍ ዱቄት ተከማችቶ የተገኘ ሲሆን ባዕድ ነገሩን ከዱቄቱ ጋር የሚደባልቅ መጋዘኑ ውስጥ እንዳይወጣ የተቆለፈበት ሠራተኛ በፍተሻ መገኘቱን ፖሊስ አስታውቋል።
ከአካባቢው ማህበረሰብ በደረሰው ጥቆማ መሰረት የጅማ በር አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ በህግ አግባብ ባደረገው ድንገተኛ ፍተሻ በስራ ላይ የነበረውን ተጠርጣሪ እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ስር አውሎ ባደረግው ተጨማሪ ምርመራ የንብረቱን ባለቤትን አፈላልጎ በመያዝ ተገቢው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።
Via @tikvahethmagazine