TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#AddisAbaba

ታህሳስ 7 ቀን 2016 ዓ/ም ምሽት አዲስ አበባ ቦሌ ኤድና ሞል አካባቢ አንድ ሰው በጥይት ተመቶ ተገድሏል።

ድርጊቱ የተፈፀመው ቦሌ ከኤድናሞል ወረድ ብሎ በሚገኝ አንድ የመዝናኛ ስፍራ አካባቢ ነው።

ምሽት አራት ሰዓት ገደማ ሟች #አባተ_አበበ በአንድ #መሳሪያ_በታጠቀ ግለሰብ በጥይት ተመቶ መገደሉ ታውቋል።

አባተ አበበ ተወልዶ ባደገበት ፣ በሚኖርበት  አካባቢ እንዲሁም ደግሞ በስራ ህይወቱ በመልካም ስነምግባሩና በተግባቢነቱ በርካቶች እንደሚያውቁት ለመረዳት ችለናል።

ስርዓተ ቀብሩ ዛሬ ይፈፀማል።

ገዳይ እንዳልተያዘ ለመረዳት ተችሏል።

የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ በሰጠው ቃል፤ ከዚህ ወንጀል ጋር በተያያዘ ምርመራ ላይ መሆኑን ገልጾ ሲጠናቀቅ በሚዲያ ለህዝቡ ይፋ ይደረጋል ብሏል።

@tikvahethiopia