TIKVAH-ETHIOPIA
የ5 ዓመቷን ህፃን የደፈረው የ17 ዓመት ወጣት 6 ወር ተፈረደበት ይለናል የወምበራ ኮሚኒኬሽን። የ5 ዓመቷን ህፃን አስገድዶ በመድፈር ወንጀል የተከሰሰው የ17 ዓመቱ ወጣት #በ6ወር እስራት መቀጣቱ ተሰምቷል። የ10ኛ ክፍል ተማሪና የ17 ዓመት ወጣት የሆነው ግለሰብ በአስገድዶ ወንጀል ተጠርጥሮ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለው ታህሳስ 26 ቀን 2016 ዓ/ም በመተከል ዞን ወንበራ ወረዳ በደብረ―ዘይት ከተማ…
“ ሕጉ ለምን ተለሳለሰ? ”
የአስገድዶ መድፈር ወንጀል በፈጸሙ አካላት ላይ የሚወሰነው ፍርድ ተመጣጣኝ ባለመሆኑ ወንጀል ፈፃሚዎች ከስህተታቸው ተምረው እንዲታረሙና ድርጊቱ እንዲቆም በማስቻል ፋንታ “ አይዟችሁ በርቱ ” የሚል ይመስላል ፣ ሕጉ ለምን ተለሳለሰ ? የሚሉ ትችት እና ጥያቄዎችን በተለይም ከሰሞኑን በበርካቶች ዘንድ ሲሰነዘር ተስተውለዋል።
በርካቶችን ካስቆጡ የወንጀል ቅጣቶች መካከል አንዱ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ወንበራ ወረዳ ዓርብ ታህሳስ 20 ቀን 2016 ዓ/ም አንድ የ17 ዓመት ተማሪ ፣ ምንም ነፍስ ያላወቀች የ5 ዓመቷን ህፃን አስገድዶ ደፈሩን ተከትሎ የወረዳው ፍ/ቤት መጋቢት 9/ 2016 ዓ/ም በዋለው ችሎት በወንጀል ፈጻሚው ላይ የ6 ወራት እስራት የፍርድ ቅጣት ማስተላለፉ ተጠቃሽ ነው።
እንዲሁም፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ኬሌ 01 ቀበሌ መጋቢት 2015 ዓ/ም የ8ኛ ክፍል ተማሪ ፣ የ13 ዓመት ታዳጊ ፣ የአብራካቸው ክፋይ የሆነች #ልጃቸውን አስገድደው ደፈሩ የተባሉትን የ42 ዓመት አባት ላይ የዞኑ ፍርድ ቤት የ10 ዓመታት የእስራት ቅጣት መወሰኑም ሌላኛው ትችት ያጫረ የፍርድ ውሳኔ መሆኑ አይዘነጋም።
ሌሎች ተያያዥ በርካታ ወንጀሎች መኖራቸው እንደተጠበቀ ሆኖ እንደ አብነት ከላይ በተጠቀሱት የአስገድዶ መድፈር ረገድ በተላለፉ የወንጀል ቅጣት ውሳኔዎች እና የቤንሻንጉል ወንበራውን የአስገድዶ መድፈር ጥቃት ወንጀል የተሰጠውን ቅጣት በተመለከተ ፦
➡️ ምን አይነት ቀልድ ነው ?
➡️ ይሄ ውሳኔ አሁን ቅጣት ነው ?
➡️ እስከ መቼ ነው በሰው ቁስል የሚቀለደው ? በሚል ብዙኅን ጥያቄዎች አንስተዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን #ልጃቸውን ደፈሩ የተባሉትን አባት የቅርብ ጊዜ የፍርድ ቤት ቤት ቅጣት ውሳኔ በተመለከተ፣ “ 10 ዓመት እስራት ብቻ ?፣ ውሳኔው ድርጊቱ እንዲበረታታ እንዲያደርግ ታስቦ የተሰጠ ነው እንዴ ? ” የሚሉ ጥያቄዎችን አጭሯል ተስተውሏል።
በተያያዘ ከዓመታት በፊት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከአምስት ዓመታት በታች የሆኑ ወንዶችን ሁሉ የደፈሩ ወንጀለኞች ከአምስት ዓመታት በታች በሆኑ የእስራት፣ ከ2,000 ብር ያልበለጡ ቅጣቶች ሲወሰኑባቸው መስተዋሉ በርካቶችን “ ፍትህ የት ናት ? ” ያስባሉ ጉዳዮች ናቸው።
በወቅቱ አስተያዬታቸውን የሰጡ ምሁራንም፣ ወንድ ልጅ ላይ “ እንዲህ አይነት ወንጀል መፈጸም የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ሳይሆን፣ የግብረሰዶም ድርጊት ተፈጸመ ነው መባል ያለበት ” ሲሉ ተስተውለው ነበር።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ከሰሞኑ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ወንበራ ወረዳ የአምስት ዓመቷን ህፃን አስገድዶ ደፈረ በተባለው የ17 ዓመት ወጣት የ6 ወራት የእስራት ቅጣት መወሰኑ፣ በአጠቃላይ በዘርፉ ለሚፈጸሙ ወንጀሎች ለሚሰጠውን “ የተለሳለሰ ቅጣት ” በተመለከተ ሕጉን በድጋሚ ማጤን እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጽያ ገልጿል።
@tikvahethiopia
የአስገድዶ መድፈር ወንጀል በፈጸሙ አካላት ላይ የሚወሰነው ፍርድ ተመጣጣኝ ባለመሆኑ ወንጀል ፈፃሚዎች ከስህተታቸው ተምረው እንዲታረሙና ድርጊቱ እንዲቆም በማስቻል ፋንታ “ አይዟችሁ በርቱ ” የሚል ይመስላል ፣ ሕጉ ለምን ተለሳለሰ ? የሚሉ ትችት እና ጥያቄዎችን በተለይም ከሰሞኑን በበርካቶች ዘንድ ሲሰነዘር ተስተውለዋል።
በርካቶችን ካስቆጡ የወንጀል ቅጣቶች መካከል አንዱ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ወንበራ ወረዳ ዓርብ ታህሳስ 20 ቀን 2016 ዓ/ም አንድ የ17 ዓመት ተማሪ ፣ ምንም ነፍስ ያላወቀች የ5 ዓመቷን ህፃን አስገድዶ ደፈሩን ተከትሎ የወረዳው ፍ/ቤት መጋቢት 9/ 2016 ዓ/ም በዋለው ችሎት በወንጀል ፈጻሚው ላይ የ6 ወራት እስራት የፍርድ ቅጣት ማስተላለፉ ተጠቃሽ ነው።
እንዲሁም፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ኬሌ 01 ቀበሌ መጋቢት 2015 ዓ/ም የ8ኛ ክፍል ተማሪ ፣ የ13 ዓመት ታዳጊ ፣ የአብራካቸው ክፋይ የሆነች #ልጃቸውን አስገድደው ደፈሩ የተባሉትን የ42 ዓመት አባት ላይ የዞኑ ፍርድ ቤት የ10 ዓመታት የእስራት ቅጣት መወሰኑም ሌላኛው ትችት ያጫረ የፍርድ ውሳኔ መሆኑ አይዘነጋም።
ሌሎች ተያያዥ በርካታ ወንጀሎች መኖራቸው እንደተጠበቀ ሆኖ እንደ አብነት ከላይ በተጠቀሱት የአስገድዶ መድፈር ረገድ በተላለፉ የወንጀል ቅጣት ውሳኔዎች እና የቤንሻንጉል ወንበራውን የአስገድዶ መድፈር ጥቃት ወንጀል የተሰጠውን ቅጣት በተመለከተ ፦
➡️ ምን አይነት ቀልድ ነው ?
➡️ ይሄ ውሳኔ አሁን ቅጣት ነው ?
➡️ እስከ መቼ ነው በሰው ቁስል የሚቀለደው ? በሚል ብዙኅን ጥያቄዎች አንስተዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን #ልጃቸውን ደፈሩ የተባሉትን አባት የቅርብ ጊዜ የፍርድ ቤት ቤት ቅጣት ውሳኔ በተመለከተ፣ “ 10 ዓመት እስራት ብቻ ?፣ ውሳኔው ድርጊቱ እንዲበረታታ እንዲያደርግ ታስቦ የተሰጠ ነው እንዴ ? ” የሚሉ ጥያቄዎችን አጭሯል ተስተውሏል።
በተያያዘ ከዓመታት በፊት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከአምስት ዓመታት በታች የሆኑ ወንዶችን ሁሉ የደፈሩ ወንጀለኞች ከአምስት ዓመታት በታች በሆኑ የእስራት፣ ከ2,000 ብር ያልበለጡ ቅጣቶች ሲወሰኑባቸው መስተዋሉ በርካቶችን “ ፍትህ የት ናት ? ” ያስባሉ ጉዳዮች ናቸው።
በወቅቱ አስተያዬታቸውን የሰጡ ምሁራንም፣ ወንድ ልጅ ላይ “ እንዲህ አይነት ወንጀል መፈጸም የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ሳይሆን፣ የግብረሰዶም ድርጊት ተፈጸመ ነው መባል ያለበት ” ሲሉ ተስተውለው ነበር።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ከሰሞኑ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ወንበራ ወረዳ የአምስት ዓመቷን ህፃን አስገድዶ ደፈረ በተባለው የ17 ዓመት ወጣት የ6 ወራት የእስራት ቅጣት መወሰኑ፣ በአጠቃላይ በዘርፉ ለሚፈጸሙ ወንጀሎች ለሚሰጠውን “ የተለሳለሰ ቅጣት ” በተመለከተ ሕጉን በድጋሚ ማጤን እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጽያ ገልጿል።
@tikvahethiopia