#ረመዷን
ታላቁ እና የተቀደሰው የረመዷን ጾም ነገ ቅዳሜ ይጀምራል።
በሳኡዲ አረቢያ የረመዷን ጨረቃ ታይታለች።
ዛሬ የተራዊህ ሶላት የሚጀመር ሲሆን ነገ ቅዳሜ የረመዷን ጾም ይጀምራል።
#Haramain
@tikvahethiopia
ታላቁ እና የተቀደሰው የረመዷን ጾም ነገ ቅዳሜ ይጀምራል።
በሳኡዲ አረቢያ የረመዷን ጨረቃ ታይታለች።
ዛሬ የተራዊህ ሶላት የሚጀመር ሲሆን ነገ ቅዳሜ የረመዷን ጾም ይጀምራል።
#Haramain
@tikvahethiopia
" የግብፅ እና ኢትዮጵያ ጨዋታ የኪሳራ ጨዋታዎች ናቸው። ... ለመሸነፍ ለመሸነፍ ብዙ ወጣት ተጫዋቾች አሉን " - መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ አክስዮን ማህበር በፋይናንስ አሰራር ተቆጣጣሪ ኮሚቴ በተላለፉ ወሳኔዎች ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ በትላንትናው ዕለት ሰጥቶ ነበር።
የሊጉ አክስዮን ማህበር የፋይናንስ አጣሪ ተቆጣጣሪ ኮሚቴ የፋይናንስ ደንቡን በጣሱ ክለቦች እና ተጨዋቾች ላይ የቅጣት ውሳኔ ከቀናት በፊት አስተላልፎ የነበረ ሲሆን በተላለፈው ቅጣትም 4 ክለቦች እና 15 ተጫዋቾች ላይ ባደረገው ምርመራ ክለቦቹ የቅድመ ክፍያ(በሶስተኛ ወገን) ከፍለዋል በማለት 45 ሚልዮን ብር ቀጥቷል።
የአክስዮን ማህበሩ የቦርድ ሰብሳቢ መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ በሰሞነኛ የክለቦች የዝውውር ክፍያ ስርዓት ላይ በተሰጠ መግለጫ የብሔራዊ ቡድኑ ተጫዋቾች እንደሚቀጡ አስረግጠው ተናግረዋል።
ከጋዜጠኞች ይቀጣሉ ወይ ? ተብሎ ለተነሳላቸው ጥያቄ " አዎ ይቀጣሉ " ሲሉ መልሰዋል።
በቀጣይ ከግብፅ ጋር ስለሚደረግ ጨዋታ ሲጠየቁም " እሱን ግጥሚያ ብለህ ትጠራለህ ? ማሟያ ነው " ብለዋል።
መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ አያይዘውም " ካፍ ስላስገደደን ነው የምንሄደው የኪሰራ ጨዋታዎች ናቸው ፣ ለመሸነፍ ለመሸነፍ ብዙ ወጣት ተጫዋቾች አሉን " የሚል ምላሽን ለጋዜጠኞች ሰጥተዋል።
ዋልያዎቹ ከሶስት ሳምንት በኃላ በዓለም ዋንጫ ማጣርያ መርሐ ግብር በሞሮኮ ካሳብላንካ ዛውል አል አረቢ ስታዲየም የግብፅ አቻውን ይገጥማል።
ዋልያዎቹ ለመጨረሻ ጊዜ ከሁለት ዓመት በፊት በሜዳቸው ማድረግ የነበረባቸውን መርሐ ግብር በማላዊ ባደረጉበት ወቅት በሽመልስ በቀለ እና ዳዋ ሆቴሳ ጎሎች 2ለ0 ማሸነፋቸው የሚታወስ ነው።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ አክስዮን ማህበር በፋይናንስ አሰራር ተቆጣጣሪ ኮሚቴ በተላለፉ ወሳኔዎች ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ በትላንትናው ዕለት ሰጥቶ ነበር።
የሊጉ አክስዮን ማህበር የፋይናንስ አጣሪ ተቆጣጣሪ ኮሚቴ የፋይናንስ ደንቡን በጣሱ ክለቦች እና ተጨዋቾች ላይ የቅጣት ውሳኔ ከቀናት በፊት አስተላልፎ የነበረ ሲሆን በተላለፈው ቅጣትም 4 ክለቦች እና 15 ተጫዋቾች ላይ ባደረገው ምርመራ ክለቦቹ የቅድመ ክፍያ(በሶስተኛ ወገን) ከፍለዋል በማለት 45 ሚልዮን ብር ቀጥቷል።
የአክስዮን ማህበሩ የቦርድ ሰብሳቢ መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ በሰሞነኛ የክለቦች የዝውውር ክፍያ ስርዓት ላይ በተሰጠ መግለጫ የብሔራዊ ቡድኑ ተጫዋቾች እንደሚቀጡ አስረግጠው ተናግረዋል።
ከጋዜጠኞች ይቀጣሉ ወይ ? ተብሎ ለተነሳላቸው ጥያቄ " አዎ ይቀጣሉ " ሲሉ መልሰዋል።
በቀጣይ ከግብፅ ጋር ስለሚደረግ ጨዋታ ሲጠየቁም " እሱን ግጥሚያ ብለህ ትጠራለህ ? ማሟያ ነው " ብለዋል።
መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ አያይዘውም " ካፍ ስላስገደደን ነው የምንሄደው የኪሰራ ጨዋታዎች ናቸው ፣ ለመሸነፍ ለመሸነፍ ብዙ ወጣት ተጫዋቾች አሉን " የሚል ምላሽን ለጋዜጠኞች ሰጥተዋል።
ዋልያዎቹ ከሶስት ሳምንት በኃላ በዓለም ዋንጫ ማጣርያ መርሐ ግብር በሞሮኮ ካሳብላንካ ዛውል አል አረቢ ስታዲየም የግብፅ አቻውን ይገጥማል።
ዋልያዎቹ ለመጨረሻ ጊዜ ከሁለት ዓመት በፊት በሜዳቸው ማድረግ የነበረባቸውን መርሐ ግብር በማላዊ ባደረጉበት ወቅት በሽመልስ በቀለ እና ዳዋ ሆቴሳ ጎሎች 2ለ0 ማሸነፋቸው የሚታወስ ነው።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ይህን ተናግሬያለሁ ብዬ ማመን ይከብደኛል፤ ዘሌንስኪን በጣም ደፋር መሪ ነው " - ዶናልድ ትራምፕ አወዛጋቢው የአሜሪካው ፕሬዝዳነት ዶናልድ ትራምፕ ከዚህ ቀደም " አምባገነን " ሲሉ የጠሯቸውን የዩክሬኑን ፕሬዜዳንት ቮሊድሚር ዘለንስኪን " ጀግና መሪ ነው " ሲሉ አሞካሿቸው። ፕሬዝዳት ትራምፕ በዛሬው ዕለት ከዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ጋር ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው። ትራምፕ አስቀድመው በዋይት…
" በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ህይወት ላይ ቁማር እየተጫወትክ ነው " - ትራምፕ
ዛሬ የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮልድሚር ዜሌንስኪ አሜሪካ ሄደው ከፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ተገናኝተዋል።
" ውይይት አደረጉ " ለማለት በሚያስቸግር ሁኔታ ትራምፕ እና ባለስልጣኖቻቸው ዜሌንስኪን ሲገስጹ ፣ ንግግራቸውን ሲያቋርጡ፣ ሲመክሯቸው ታይተዋል።
ትራምፕ ዜሌንስኪን ከሩስያ ጋር የገቡበት ጦርነት የሚያቆምበት ጊዜ አሁን ነው ብለዋቸዋል።
" አሁን አንተ የምትወስንበት አቋም ላይ አይደለህም " ሲሉም ትራምፕ እና ጄዲ ቫንስ ዘለንስኪን ሲገስፁ ነበር።
የገቡበት ጦርነት ያለ ቀድሞው ፕሬዜዳንት ባይደን እና 350 ቢሊዮን ዶላር የአሜሪካ ድጋፍ በሁለት ሳምንታት ውስጥ ያበቃ ነበር ሲሉም ነግረዋቸዋል።
ትራምፕ " በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ህይወት ላይ ቁማር እየተጫወትክ ነው። በሶስተኛው የዓለም ጦርነት ቁማር እየተጫወትክ ነው " ሲሉ ዜሌንስኪን ተናግረዋቸዋል።
" ሀገርህ ችግር ላይ ናት "ም ብለዋቸዋል።
" ደግሞ አመስጋኝ አይደለህም ፤ያ ጥሩ ነገር አይደለም " ሲሉም ገስጸዋቸዋል።
" ወይ ስምምነት ፍጠር ካልሆነ እኛ ከዚህ እንወጣለን። አሁን ምንም የቀረህ የምትመዘው ካርድ የለህም " ሲሉም ተናግረዋቸዋል።
ዘለንስኪ ከትራምፕ ጋር ከነበራቸው የጋለ የቃላት ልውውጥ በኋላ አስቀድመው ዋይት ሃውስን ለቀው ወጥተዋል።
ሁለቱ መሪዎች በጋራ መስጠት የነበረባቸው ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰርዟል።
ትራምፕ ከዘለንስኪ ጋር የጋለ ንግግር ካደረጉ በኋላ በትሩዝ ትስስር ገጻቸው ላይ " ዘለንስኪ ለሰላም ዝግጁ አይደለም። ለሰላም ሲዘጋጅ ተመልሶ መምጣት ይችላል " ብለዋል።
ኢሎን መስክ በX ገጹ ላይ " ዘለንስኪ በአሜሪካ ሕዝብ ፊት እራሱን አዋርዷል " ሲል ፅፏል። #SputnikNews
@tikvahethiopia
ዛሬ የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮልድሚር ዜሌንስኪ አሜሪካ ሄደው ከፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ተገናኝተዋል።
" ውይይት አደረጉ " ለማለት በሚያስቸግር ሁኔታ ትራምፕ እና ባለስልጣኖቻቸው ዜሌንስኪን ሲገስጹ ፣ ንግግራቸውን ሲያቋርጡ፣ ሲመክሯቸው ታይተዋል።
ትራምፕ ዜሌንስኪን ከሩስያ ጋር የገቡበት ጦርነት የሚያቆምበት ጊዜ አሁን ነው ብለዋቸዋል።
" አሁን አንተ የምትወስንበት አቋም ላይ አይደለህም " ሲሉም ትራምፕ እና ጄዲ ቫንስ ዘለንስኪን ሲገስፁ ነበር።
የገቡበት ጦርነት ያለ ቀድሞው ፕሬዜዳንት ባይደን እና 350 ቢሊዮን ዶላር የአሜሪካ ድጋፍ በሁለት ሳምንታት ውስጥ ያበቃ ነበር ሲሉም ነግረዋቸዋል።
ትራምፕ " በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ህይወት ላይ ቁማር እየተጫወትክ ነው። በሶስተኛው የዓለም ጦርነት ቁማር እየተጫወትክ ነው " ሲሉ ዜሌንስኪን ተናግረዋቸዋል።
" ሀገርህ ችግር ላይ ናት "ም ብለዋቸዋል።
" ደግሞ አመስጋኝ አይደለህም ፤ያ ጥሩ ነገር አይደለም " ሲሉም ገስጸዋቸዋል።
" ወይ ስምምነት ፍጠር ካልሆነ እኛ ከዚህ እንወጣለን። አሁን ምንም የቀረህ የምትመዘው ካርድ የለህም " ሲሉም ተናግረዋቸዋል።
ዘለንስኪ ከትራምፕ ጋር ከነበራቸው የጋለ የቃላት ልውውጥ በኋላ አስቀድመው ዋይት ሃውስን ለቀው ወጥተዋል።
ሁለቱ መሪዎች በጋራ መስጠት የነበረባቸው ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰርዟል።
ትራምፕ ከዘለንስኪ ጋር የጋለ ንግግር ካደረጉ በኋላ በትሩዝ ትስስር ገጻቸው ላይ " ዘለንስኪ ለሰላም ዝግጁ አይደለም። ለሰላም ሲዘጋጅ ተመልሶ መምጣት ይችላል " ብለዋል።
ኢሎን መስክ በX ገጹ ላይ " ዘለንስኪ በአሜሪካ ሕዝብ ፊት እራሱን አዋርዷል " ሲል ፅፏል። #SputnikNews
@tikvahethiopia
ሕብረት ባንክ እንኳን ለ1446 ዓ.ሒ የሐጅ ጉዞ በሰላም አደረሳችሁ እያለ፤ የሐጅ ጉዞ ክፍያዎን በአቅራቢያዎ በሚገኙ ቅርንጫፎቻችን በልዩ መስተንግዶ እንዲፈጽሙ በአክብሮት ይጋብዛል፡፡
በዚህ አጋጣሚ የሸሪዓውን መርህ መሰረት ያደረገ ሕብር ሀቅ የተሰኘ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎታችን ተጠቃሚ ይሁኑ፡፡
ሐጀን መብሩር!
ሕብር ሀቅ
ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!
📞 ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://yangx.top/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡
በዚህ አጋጣሚ የሸሪዓውን መርህ መሰረት ያደረገ ሕብር ሀቅ የተሰኘ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎታችን ተጠቃሚ ይሁኑ፡፡
ሐጀን መብሩር!
ሕብር ሀቅ
ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!
📞 ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://yangx.top/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡
#MPESASafaricom
ከUSA ገንዘብ በM-PESA እንቀበል 10% ስጦታ እና 1 ጊ.ባ ኢንተርኔት ተጨማሪ አሁኑኑ እናግኝ! ቪዛ ፣ ማስተርካርድ ወይም አሜክስ ካርድ በመጠቀም በካሽ ጎን በኩል እንላክ።
በምንዛሬ ተመን
1 USD = 137 ብር
ካሽ ጎን ይህንን ሊንክ ተጠቅመን ማውረድ እንችላለን፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=com.bankofabyssinia.cashgo
ገንዘቦን በዳሽን ባንክ እለታዊ ምንዛሬ ያግኙ + 10%ስጦታ ።
#MPESAEthiopia #MPESASafaricom
ከUSA ገንዘብ በM-PESA እንቀበል 10% ስጦታ እና 1 ጊ.ባ ኢንተርኔት ተጨማሪ አሁኑኑ እናግኝ! ቪዛ ፣ ማስተርካርድ ወይም አሜክስ ካርድ በመጠቀም በካሽ ጎን በኩል እንላክ።
በምንዛሬ ተመን
1 USD = 137 ብር
ካሽ ጎን ይህንን ሊንክ ተጠቅመን ማውረድ እንችላለን፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=com.bankofabyssinia.cashgo
ገንዘቦን በዳሽን ባንክ እለታዊ ምንዛሬ ያግኙ + 10%ስጦታ ።
#MPESAEthiopia #MPESASafaricom
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ተማሪ ቢንያም ኢሳያስ የሕክምና ትምህርቱን እንዲቀጥል ተወስኗል። የተማሪ ቢንያም ኢሳያስን ትምህርት በተመለከተ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዛሬ መግለጫ አውጥቷል። በመግለጫው ፤ የተማሪ ቢንያም ኢሳያስን ትምህርት በተመለከተ ለተማሪው የትምህርት ሂደት ይረዳሉ ያሏቸውን አማራጮች መቅረቡን አስታውሷል። ሆኖም ተማሪ ቢንያም ብቸኛ ፍላጎቱ የሕክምና ትምህርትን መማር እንደሆነ…
#DrBinyamEsayas
ዶክተር ቢኒያም ኢሳያስ በከፍተኛ ውጤት ተመረቀ።
ዛሬ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ያሰለጠናቸውን 179 ተማሪዎች አስመርቋል።
ከተመራቂዎቹ አንዱ ዶክተር ቢኒያም ኢሳያስ ነው።
በትምህርት ቆይታው ያጋጥሙትን ውስብስብ ችግሮች በማሸንፍ ለበርካቶች አርአያ የሆነው ተማሪ ቢኒያም ኢሳያስ በከፍተኛ ወጤት ተመርቋል።
ዶክተር ቢኒያም በትምህርት ቆይታው ያጋጥሙትን ውስብስብ ችግሮች አልፎ ዛሬ ለደረሰበት ስኬት በመብቃቱ መደሰቱን ገልጿል።
ዶክተር ቢኒያም እናትና አባትም ልጃቸው ከልጅነቱ ጀምሮ ጎበዝ ተማሪ መሆኑን ገልጸው፤ ለህልሙ መሳካት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት መወጣታቸውን ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና የጤና ሳይንስ ኮሌጅ አካዳሚክ ኮሚሽን በጋራ ባካሄዱት ስብሰባ ተማሪ ቢንያም ኢሳያስ የሕክምና ትምህርቱን እንዲቀጥል መወሰኑ ይታወሳል።
#EPA
@tikvahethiopia
ዶክተር ቢኒያም ኢሳያስ በከፍተኛ ውጤት ተመረቀ።
ዛሬ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ያሰለጠናቸውን 179 ተማሪዎች አስመርቋል።
ከተመራቂዎቹ አንዱ ዶክተር ቢኒያም ኢሳያስ ነው።
በትምህርት ቆይታው ያጋጥሙትን ውስብስብ ችግሮች በማሸንፍ ለበርካቶች አርአያ የሆነው ተማሪ ቢኒያም ኢሳያስ በከፍተኛ ወጤት ተመርቋል።
ዶክተር ቢኒያም በትምህርት ቆይታው ያጋጥሙትን ውስብስብ ችግሮች አልፎ ዛሬ ለደረሰበት ስኬት በመብቃቱ መደሰቱን ገልጿል።
ዶክተር ቢኒያም እናትና አባትም ልጃቸው ከልጅነቱ ጀምሮ ጎበዝ ተማሪ መሆኑን ገልጸው፤ ለህልሙ መሳካት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት መወጣታቸውን ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና የጤና ሳይንስ ኮሌጅ አካዳሚክ ኮሚሽን በጋራ ባካሄዱት ስብሰባ ተማሪ ቢንያም ኢሳያስ የሕክምና ትምህርቱን እንዲቀጥል መወሰኑ ይታወሳል።
#EPA
@tikvahethiopia
“ የአንድ አዞ ቆዳ አንድ ሴንቲሜትር 5 ዶላር ነው የሚሸጠው ” - የጋሞ ልማት ማኀበር
በተለይ የውጪ አገር የገበያ ትስስር ባለመኖሩ ኢትዮጵያ ከአዞ ሽያጭ እስከ 60 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ገቢ እያጣች መሆኑን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባምንጭ የጋሞ ልማት ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
ከሦስት ዓመታት በፊት ትንሽ የአዞ ስጋና ቆዳ ለውጪ አገራት ይሸጥ እንደነበር፣ ከዚያ በኋላ በገበያ ትስስር ክፍተት ገቢው በመቀዛቀዙ እንደ አዲስ ለማንሰራራት እየተሰራ መሆኑን ማኀበሩ አስረድቷል።
ስለአዞ ሽያጭ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ የጠየቃቸው የማህበሩ አርባምንጭ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳዊት ዳኘ፣ “ ከ3 አመታት በፊት 10፣ 15 ነበር የሚሸጠው። ከ3000 እስከ 5000 አዞዎች ሲሸጡ የነበረው ከ10 ዓመት በፊት ነው። እየቀሰ መጥቷል ” ብለዋል።
የማኀበሩ ሥራ የአርባምንጭ አስኪያጅ አቶ ዲዊት ዳኘ ምን አሉ ?
“ የአዞ ቆዳ የሽያጭ ሂደቱ ተቀዛቅዞ ቆይቶ አሁን ሽያጭ አልተጀመረም። አሁን በማኀበሩ ተወስዶ እየተሰራ ነው። ቆዳቸው ለሽያጭ የደረሱ ከ2500 በላይ አዞዎች አሉን። እንዴት እንደሚቀጥል ከአገር ውስጥ ካምፓኒዎች ጋር እያወራን ነው።
አሁን ተነጋግረን የውል ሂደት ላይ ነው ያለነው እሱን ጨርሰን ሽያጩ ይካሄዳል ብለን እናስባለን። በፊት ሲሸጥ የነበረው ቆዳው ብቻ ነው። ግን የአዞ ስጋው፣ ጥርሱ፣ ይፈለጋል። ስጋው በሌሎች አገራት በጣም ይፈለጋል።
አሁን 4,000 የአዞ ጫጩቶችን ለመሰብሰብ እንቁላል ዝግጁ ሆኖ ነው ያለው። ከሦስት ወራት በኋላ ጫጩት ከተፈለፈለ በኋላ ከሀይቁ ወደ ማኀበር ይመጣሉ።
የአዞ ቆዳና ስጋ በጣም ዋጋው ውድ ነው። ስለዚህ ትክክለኛ ማርኬት ሊንኬጅ ተፈጥሮ ስርዓቱ ቢዘረጋ እንደ አገር ትልቅ ገቢ እናገኛለን። በተለይ በዘርፉ የሚሰሩ የውጪ አገር ካምፓኒዎችን እያነጋነርን ነው ” ብለዋል።
ከ2,500 በላይ አዞዎች ለሽያጭ ቢቀርቡ ምን ያክል ገቢ ማግኘት ይቻላል ? ስንል የጠየቅናቸው አቶ ዳዊት፣ የአንድ አዞ ቆዳ አንድ ሴንቲሜትር 5 ዶላር እንደሚሸጥ፣ የአንድ አዞ ቆዳ እስከ 45 ሴንቲሜትር እንደሚሆን፣ አንድ አዞ በትንሹ እስከ 22 ሺሕ ብር እንደሚሸጥ፣ በጠቅላላ ከ55 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ሊገኝ እንደሚችል አስረድተዋል።
በማኀበሩ ስንት ሠራተኞች አሉ ? የአዞ ስጋ ምግብነት ላይ ይውላል ወይ ? ለሚለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ አቶ ዳዊት፣ “ የአዞ ስጋ ይበላል። በኛ አልተለመደም። ግን የኛ ሰዎች የ40 ዓመት ልምድ አላቸው። ብራንቹ ተቋቁሞ 41 ዓመቱ ነው። ረጅም ልምድ ያላቸው ሰዎች አዞ የመመገብ ልምድ አላቸው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
አቶ ዳዊትና አንድ የማኀበሩ አስጎብኝ በኢትዮጵያ ብዙ እንዳልተለመደ፣ ኬኒያን ጨምር በሌሎች አካባቢዎች አዞ ለምግብነት እንደሚውል ተናግረዋል።
አቶ ዳዊት፣ “ የአዞ ሬስቶራንት ለመክፈት ” እንዳሰቡ ገልጸው፣ “ ፈረንጆች ይመጣሉ እዚህ ይመገባሉ፤ ቀስ በቀስ የኛ ሰዎችም እያዩ እየተመገቡ ይሄዳሉ ” ነው ያሉት።
አክለው፣ በማኀበሩ ወደ 35 ገደማ ሠራተኞች እንዳሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጹ ሲሆን፣ የማኀበሩ አስጎብኝ በሰጡት ገለጻ ደግሞ፣ “60 በመቶ የሚሆኑት ሰራተኞች የአዞ ስጋ ይመገባሉ” ብለዋል።
አንድ አዞ ለሽያጭ ለመቅረብ ብቁ እስከሚሆን ድረስ 62 ኪሎ ግራም ስጋ እንደሚመገብ፣ አዞ የሚመገበው የአሳ፣ የአዞ ስጋ እንደሆነ፣ አሳማ ሌሎች የእንስሳት ዝርያዎች እንዳሉ፣ የህክምናና ሌሎችን ጨምሮ በአጠቃላይ ማኀበሩ በአመት እስከ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ እንደሚደረግ ተመልክቷል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በተለይ የውጪ አገር የገበያ ትስስር ባለመኖሩ ኢትዮጵያ ከአዞ ሽያጭ እስከ 60 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ገቢ እያጣች መሆኑን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባምንጭ የጋሞ ልማት ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
ከሦስት ዓመታት በፊት ትንሽ የአዞ ስጋና ቆዳ ለውጪ አገራት ይሸጥ እንደነበር፣ ከዚያ በኋላ በገበያ ትስስር ክፍተት ገቢው በመቀዛቀዙ እንደ አዲስ ለማንሰራራት እየተሰራ መሆኑን ማኀበሩ አስረድቷል።
ስለአዞ ሽያጭ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ የጠየቃቸው የማህበሩ አርባምንጭ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳዊት ዳኘ፣ “ ከ3 አመታት በፊት 10፣ 15 ነበር የሚሸጠው። ከ3000 እስከ 5000 አዞዎች ሲሸጡ የነበረው ከ10 ዓመት በፊት ነው። እየቀሰ መጥቷል ” ብለዋል።
የማኀበሩ ሥራ የአርባምንጭ አስኪያጅ አቶ ዲዊት ዳኘ ምን አሉ ?
“ የአዞ ቆዳ የሽያጭ ሂደቱ ተቀዛቅዞ ቆይቶ አሁን ሽያጭ አልተጀመረም። አሁን በማኀበሩ ተወስዶ እየተሰራ ነው። ቆዳቸው ለሽያጭ የደረሱ ከ2500 በላይ አዞዎች አሉን። እንዴት እንደሚቀጥል ከአገር ውስጥ ካምፓኒዎች ጋር እያወራን ነው።
አሁን ተነጋግረን የውል ሂደት ላይ ነው ያለነው እሱን ጨርሰን ሽያጩ ይካሄዳል ብለን እናስባለን። በፊት ሲሸጥ የነበረው ቆዳው ብቻ ነው። ግን የአዞ ስጋው፣ ጥርሱ፣ ይፈለጋል። ስጋው በሌሎች አገራት በጣም ይፈለጋል።
አሁን 4,000 የአዞ ጫጩቶችን ለመሰብሰብ እንቁላል ዝግጁ ሆኖ ነው ያለው። ከሦስት ወራት በኋላ ጫጩት ከተፈለፈለ በኋላ ከሀይቁ ወደ ማኀበር ይመጣሉ።
የአዞ ቆዳና ስጋ በጣም ዋጋው ውድ ነው። ስለዚህ ትክክለኛ ማርኬት ሊንኬጅ ተፈጥሮ ስርዓቱ ቢዘረጋ እንደ አገር ትልቅ ገቢ እናገኛለን። በተለይ በዘርፉ የሚሰሩ የውጪ አገር ካምፓኒዎችን እያነጋነርን ነው ” ብለዋል።
ከ2,500 በላይ አዞዎች ለሽያጭ ቢቀርቡ ምን ያክል ገቢ ማግኘት ይቻላል ? ስንል የጠየቅናቸው አቶ ዳዊት፣ የአንድ አዞ ቆዳ አንድ ሴንቲሜትር 5 ዶላር እንደሚሸጥ፣ የአንድ አዞ ቆዳ እስከ 45 ሴንቲሜትር እንደሚሆን፣ አንድ አዞ በትንሹ እስከ 22 ሺሕ ብር እንደሚሸጥ፣ በጠቅላላ ከ55 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ሊገኝ እንደሚችል አስረድተዋል።
በማኀበሩ ስንት ሠራተኞች አሉ ? የአዞ ስጋ ምግብነት ላይ ይውላል ወይ ? ለሚለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ አቶ ዳዊት፣ “ የአዞ ስጋ ይበላል። በኛ አልተለመደም። ግን የኛ ሰዎች የ40 ዓመት ልምድ አላቸው። ብራንቹ ተቋቁሞ 41 ዓመቱ ነው። ረጅም ልምድ ያላቸው ሰዎች አዞ የመመገብ ልምድ አላቸው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
አቶ ዳዊትና አንድ የማኀበሩ አስጎብኝ በኢትዮጵያ ብዙ እንዳልተለመደ፣ ኬኒያን ጨምር በሌሎች አካባቢዎች አዞ ለምግብነት እንደሚውል ተናግረዋል።
አቶ ዳዊት፣ “ የአዞ ሬስቶራንት ለመክፈት ” እንዳሰቡ ገልጸው፣ “ ፈረንጆች ይመጣሉ እዚህ ይመገባሉ፤ ቀስ በቀስ የኛ ሰዎችም እያዩ እየተመገቡ ይሄዳሉ ” ነው ያሉት።
አክለው፣ በማኀበሩ ወደ 35 ገደማ ሠራተኞች እንዳሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጹ ሲሆን፣ የማኀበሩ አስጎብኝ በሰጡት ገለጻ ደግሞ፣ “60 በመቶ የሚሆኑት ሰራተኞች የአዞ ስጋ ይመገባሉ” ብለዋል።
አንድ አዞ ለሽያጭ ለመቅረብ ብቁ እስከሚሆን ድረስ 62 ኪሎ ግራም ስጋ እንደሚመገብ፣ አዞ የሚመገበው የአሳ፣ የአዞ ስጋ እንደሆነ፣ አሳማ ሌሎች የእንስሳት ዝርያዎች እንዳሉ፣ የህክምናና ሌሎችን ጨምሮ በአጠቃላይ ማኀበሩ በአመት እስከ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ እንደሚደረግ ተመልክቷል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት #AddisAbaba
ከዛሬ ለሊት 6:00 ሠዓት ጀምሮ እስከ ነገ 7:00 ሠዓት ድረስ መንገዶች ይዘጋሉ።
129ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ነገ ፒያሳ በሚገኘው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ይከበራል።
ይህን ተከትሎ ፦
- በቸርችል ጎዳና በቴዎድሮስ አደባባይ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ባንኮ ዲሮማ መብራት
- ከአራት ኪሎ በራስ መኮንን ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ራስ መኮንን ድልድይ
- ከመነን አካባቢ እና የካቲት 12 ሆስፒታል በአፍንጮ በር ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ አፍንጮ በር
- ከእሪ በከንቱ በኤሌክትሪክ ህንፃ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ደጎል አደባባይ
- ከአዲሱ ገበያ በሰሜን ሆቴል ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ሰሜን መብራት
- ከመርካቶ በአቡነ ጴጥሮስ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ደጃዝማች ሀብተጊዮርጊስ ድልድይ
- ከእንቁላል ፋብሪካ በቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ዮሐንስ መብራት የሚወስዱት መንገዶች ከዛሬ የካቲት 22 ቀን 2017 ዓ/ም ከለሊቱ 6፡00 ሠዓት ጀምሮ እስከ የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 7፡00 ሠዓት ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።
ህብረተሰቡም ማንኛውም አጠራጣሪ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ በ 011-1-11-01-11 ወይም በነፃ ስልክ መስመር 991 መጠቀም የሚቻል መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።
@tikvahethiopia
ከዛሬ ለሊት 6:00 ሠዓት ጀምሮ እስከ ነገ 7:00 ሠዓት ድረስ መንገዶች ይዘጋሉ።
129ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ነገ ፒያሳ በሚገኘው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ይከበራል።
ይህን ተከትሎ ፦
- በቸርችል ጎዳና በቴዎድሮስ አደባባይ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ባንኮ ዲሮማ መብራት
- ከአራት ኪሎ በራስ መኮንን ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ራስ መኮንን ድልድይ
- ከመነን አካባቢ እና የካቲት 12 ሆስፒታል በአፍንጮ በር ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ አፍንጮ በር
- ከእሪ በከንቱ በኤሌክትሪክ ህንፃ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ደጎል አደባባይ
- ከአዲሱ ገበያ በሰሜን ሆቴል ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ሰሜን መብራት
- ከመርካቶ በአቡነ ጴጥሮስ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ደጃዝማች ሀብተጊዮርጊስ ድልድይ
- ከእንቁላል ፋብሪካ በቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ዮሐንስ መብራት የሚወስዱት መንገዶች ከዛሬ የካቲት 22 ቀን 2017 ዓ/ም ከለሊቱ 6፡00 ሠዓት ጀምሮ እስከ የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 7፡00 ሠዓት ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።
ህብረተሰቡም ማንኛውም አጠራጣሪ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ በ 011-1-11-01-11 ወይም በነፃ ስልክ መስመር 991 መጠቀም የሚቻል መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።
@tikvahethiopia