TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.13K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
“ አንዳንድ ጊዜ አደጋዎች ከተስፋፉ በኋላ የመደወል ሁኔታ አለ። በ939 ፈጥኖ መደወልም ያስፈልጋል ቶሎ ደርሰን እንድንቆጣጠር ” - ኮሚሽኑ

ዛሬ አዲስ አበባ ፤ ኮልፌ ቀራኒዮ፣ ወረዳ 2 በተለምዶ ካሬ ቆሬ ብቄላ መናፈሻ አካባቢ ተነስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በሰው ላይ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የእሳትና አደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ንጋቱ ማሞ በሰጡን ቃል፣ “ እሳቱ ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል ” ብለዋል።

“ የፍራሽ መስሪያ የሚሆኑ (ቁርጥራጭ ጨርቅ) የመሳሰሉ ግብዓቶች መጋዘን ላይ ነው የእሳት አደጋው ያጋጠመው ” ያሉት አቶ ንጋቱ፣ የኮሚሽኑ ሰራተኞች፣ ህብረተሰቡ ባደረጉት ርብርብ እሳቱ ወደ መስጊድና መኖሪያ ቤት ሳይዛመት መቆጣጠር መቻሉን አስረድተዋል።

“ በእሳት አደጋው ሰው ላይ ጉዳት አልደሰም። የቀረው መረጃ በኢኮኖሚ ላይ የደረሰው ጉዳትና የአደጋ መንስኤ ነው። እሱን ከፓሊሶች ጋር ሆነን እያጣራን ነው ” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። 

የእሳት አደጋ እየተደጋገመ ያለበት ሁኔታ እየተስተዋለ ነው፤ ማህበረሰቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ? ስንል ሳቀረብንላቸው ጥያቄ አቶ ንጋቱ፣ “ ትክክል ነው እሳት አደጋ የተደጋገመመበት ሁኔታ አለ። አሁን ያለንበት ወቅት ነፋሻማና ደረቅ አየር ነው ” የሚል ምላሽ ስጥተዋል።

“ እሳት እንዲከሰት ከሚያደርጉ ሦስት መሰረታዊ ጉዳዮች ውስጥ ሁለቱን አሁን ካለው የአየር ፀባይ እናገኛለንና መዘናጋትና ቸልተኝነት ዋጋ የሚያስከፍልበት ሂደት ስላለ ህብረተሰቡ በመኖሪያ፣ በስራ አካባቢ እሳትና የኤለክትሪክ ኃይል ምንጮችን ሲጠቀም ከወትሮው በተለዬ ሁኔታ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል ” ሲሉ አክለዋል።

“ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ያድርግ። ከዚህ አልፎ ለሚያጋጥም አደጋ፥ አንዳንድ ጊዜ አደጋዎች ከተስፋፉ በኋላ የመደወል ሁኔታ አለ። በ939ኝን ፈጥኖ መደወልም ያስፈልጋል ቶሎ ደርሰን እንድንቆጣጠር” ሲሉ አሳስበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Caption:

Empower Your Entrepreneurial Journey with Jasiri!

The Jasiri Talent Investor is calling all aspiring women entrepreneurs to join our 8th cohort. Seize this opportunity to transform your vision into reality, build your business from the ground up, and achieve the entrepreneurial success you've always dreamed of!

Apply today 👉 https://bit.ly/40Ai4oR

For more information @jasiri4Africa
የአውሮፓ የሻምፕየንስ ሊግ የመጀመሪያ ዙር ጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች የካቲት 25 እና 26 ይደረጋሉ!

ማን ይሆን ወደ ሩብ ፍፃሜ የሚደርሰው?

ሁሉንም የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎችን እና ምርጥ ምርጥ መዝናኛዎችን ያካተቱ ከ125 በላይ በአዲሱ ሜዳ ስፖርት ፓኬጅ!

🎊 ከጥር 5 እስከ መጋቢት 22 ባሉት ቀናት አሁን ካሉበት ከቤተሰብ ፓኬጅ ወደ ሜዳ ከፍ ሲሉ… እኛ ሜዳ ስፖርት ፓኬጅን እንመርቅሎታለን!

ፓኬጅዎን ያሳድጉ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh

#ChampionsLeagueAllonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET #StepUp
ከUK ገንዘብ በM-PESA እንቀበል 10% ስጦታ እና 1 ጊ.ባ ኢንተርኔት ተጨማሪ አሁኑኑ እናግኝ! *ቪዛ* ፣ *ማስተርካርድ* ወይም *አሜክስ ካርድ* በመጠቀም በካሽ ጎን በኩል እንላክ።

በምንዛሬ ተመን
*1 GBP = 172 ብር*

ካሽ ጎን ይህንን ሊንክ ተጠቅመን ማውረድ እንችላለን፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=com.bankofabyssinia.cashgo

ገንዘቦን በዳሽን ባንክ እለታዊ ምንዛሬ ያግኙ + 10%ስጦታ ።

#MPESAEthiopia #MPESASafaricom
#Ethiopia #Somalia

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ረፋድ በሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል።

ሁለቱ ሀገራት ገብተውበት ከነበረው የዲፕሎማሲ እና የፖለቲካ ውጥረት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ መሆኑ ነው።

የሶማሊያው ፕሬዚደንት ሐሰን ሼክ መሐሙድም ቱርክ ሁለቱን ሀገራት አንካራ ላይ ካስማማች በኋላ ባለፈው ጥር 3 ቀን አዲስ አበባን ጎብኝተዋል።

አስከትለውም በአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ታድመው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ተነጋግረዋል።

በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በጋራ በወጣው መግለጫ " ይህ ጉብኝት ባለፉት ጥቂት ወራት ውስጥ የተደረጉ ተከታታይ ግንኙነቶችን የተከተለ፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነትም ወደ መደበኛ ሁኔታ የሚመልስ ነው " ብሏል።

ሁለቱ መሪዎች ለጋራ ጥቅም ትብብራቸውን ለማጠናከር ቁርጠኝነታቸውን ስለማረጋገጣቸው እና በዲፕሎማሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ትብብር " መተማመንን ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል " ተብሏል።

የዚህ ጉብኝት እንደምታን በሚመለከት ቃላቸውን ለዶቼ ቨለ ሬድዮ የሰጡት ፤ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲቲዩት የአፍሪካ ጉዳዮች የሥራ ክፍል ኃላፊ እና ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ግዛቸው አስራት ፥ ሁለቱ ሀገራት መተማመን በሚያስችል ሁኔታ መነጋገር የሚችሉበት ዕድል እንደሚሆን ገልፀዋል።

" የቴክኒክ ቡድኑ (የአንካራ ስምምነት) ከሁለት ሳምንት በፊት አንካራ ላይ ተገናኝቶ ሲነጋገር ተመልክተናል። መስማማቶች እና መግባባቶች ላይ የደረሱበት፣ መተማመን በሚያስችል ሁኔታ ንግግሮች እያደረጉ ያሉበት ሂደት ነው " ብለዋል።

" የቱርክ መንግሥት አካባቢውን ካላስፈላጊ ውጥረት ታድጓል "  ያሉት ተመራማሪው እንዲህ ያሉ መልካም ልምዶች በዚህ ቀጣና ብዙም አይታዩም ብለዋል። ይህን መሳይ የውይይት፣ የድርድር እና የሰላም መንገዶች ሲታዩ ማመስገን ያስፈልጋል ብለዋል። 

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የጋራ ጥቅሞችን በማሳደግ፣ ሰላምና ደህንነትን በማስፈን እና የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን በማጠናከር ለዜጎቻቸውና ለሰፊው የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና በጋራ ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውም ጉብኝቱን ተከትሎ በወጣው የጋራ መግለጫ ላይ ተጠቅሷል።

ዶክተር ግዛቸው አስራት " ቀጣናዊ ትብብርን " የተመለከቱ ውይይቶች እንደሚኖሩ ገልፀዋል።

የዛሬውን ጉብኝት በሚመለከት አስቀድመው የወጡ ዘገባዎች ሞቃዲሾ ውስጥ ከፍተኛ የፀጥታ ጥበቃ መደረጉን ያመለክታሉ።
#DW

@TIKVAHETHIOPIA
" በአደራ የሰበሰብነውን ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ ለተለያዩ አገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ለግሰናል " - ዳሽን ባንክ

ዳሽን ባንክ ዛሬ “ ሸሪክ ” የተሰኘውን ከወለድ ነፃ አገልግሎት የ7ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በዋና መስሪያ ቤቱ አክብሯል።

በዚህም ከደንበኞቹ በአደራ የሰበሰበውን ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ ለተለያዩ አገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅቶች መለገሱን አስታውቋል፡፡ 

በዛሬው ዕለትም ለ31 ሀገር በቀል ግብረ ሰናይ ድርጅቶች የገንዘብ ድጋፍ መደረጉ ነው የተገለጸው።

በከወለድ ነፃ አገልግሎት ብቻ ከ1 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች ማፍራት መቻሉ የተገለጸ ሲሆን፣ የአገልግሎቱ ቺፍ ኦፊሰር አቶ መስፍን በዙ ባደረጉት ንግግር አመኔታቸውን ለሰጡ ደንበኞች ምስጋና አቅርበዋል።

የካቲት 26/2010 ዓ/ም በአንድ መስኮት የተጀመረው አገልግሎት አድጎ ከ80 በላይ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የሚሰጡ ቅርንጫፎችና ከ800 በላይ በሆኑ ቅርንጫፎች በመስኮት ለደንበኞቹ የተሟላ የባንክ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ተጠቁሟል።

በሱማሌ ክልል ለሚገኙ ሴት ስራ ፈጣሪዎች ከወለድ ነጻ በሆነ መንገድ 100 ሚሊዮን ብር ተዘዋዋሪ ብድር ማቅረቡን አስታውሷል።

" ሸሪክ " እ.ኤ.አ ህዳር 28/ 2023 በባህሬን ማናማ በተካሄደው 9ኛው የኢስላሚክ ሪቴል ባንክ ሽልማት ላይ “ጠንካራ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በኢትዮጵያ የሚሰጥ ባንክ” በሚል አይ ኤፍ ኤ ከተሰኘው ድርጅት ዕውቅና ማግኘቱ ተገልጿል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🔊 #የጤናባለሙያዎችድምጽ 🔴 “ የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ ዘጠኝ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” - የሆስፒታሉ ሠራተኞች ➡️ “ እነርሱ ጋ ብቻ አይደለም ያልተከፈለው፤ ከ2000 በላይ ሠራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ ”  - የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ፣ የይርጋጨፌ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎችና የአስተዳደር ባለሙያዎች “ በጸጥታ…
#Update

🔴 “ ወደ አራት ጤና ባለሙያዎች ገና አልተፈቱም። የጠየቁት መብታቸውን ስለሆነ ሊፈቱ ይገባል ” - ቤተሰቦች

➡️ “ ሰልፍ ላይ ስለተገኙ ብቻ ነው የተያዙት ” - ጤና ባለሙያ


የአራት ወራት አዲሱ ደወመዝ ክፍያ ስላልተፈጸመላቸው የሥራ ማቆም አድማ በመምታታቸው ከታሰሩት የይርጋጨፌ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎች መካከል አራቱ እንዳልተፈቱ ቤተሰቦቻቸውና የጤና ባለሙያዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

መጀመሪያ የታሰሩት ዘጠኝ እንደነበሩ ሠራተኞቹ ከቀናት በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ከዚያ በኋላ እስራቱ ቀጥሎ በአጠቃላይ 12 ሰዎች ታስረው እንደነበርና አራቱ እንዳልተፈቱ ነግረውናል።

የታሳሪ ቤተሰቦችና ጤና ባለሙያዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?

አንድ ጤና ባለሙያ በሰጡን ቃል፤ “ የተፈቱና ሌሎቹም በሥራ ገበታ ላይ ናቸው። የነዚህ የአራቱ አለመፈታት ግን እስካሁን ምስጢር ሆኖብናል። ሰልፍ ላይ ስለተገኙ ብቻ ነው የታሰሩት ” ሲሉ ተናግረዋል።

የታሳሪ ቤተሰቦች በበኩላቸው “ አራት ጤና ባለሙያዎች ገና አልተፈቱም። የጠየቁት መብታቸውን ስለሆነ ሊፈቱ ይገባል ” ብለዋል።

“ ጥያቄው የሆስፒታሉ አካላት ሁሉ ነው። የፓለቲካ ጉዳይ የሌለበት የደመወዝ ጥያቄም ነው። ከደመወዝ ይከፈለን ውጪ ያነሱት ጥያቄ የለሞ ” ሲሉም ሞግተዋል።

አንዲት የታሳሪ ቤተሰብ በሰጡን ቃል፣ ባለቤታቸው ከታሰሩ ቀናት እንዳስቆጠሩ፣ እስካሁንም እንዳልተፈቱ፣ ያሉበትን ሁኔታም እንደማያውቁ ገልጸዋል።

ሌላኛው የታሳሪዋ የቅርብ ሰው የ10 ወር ጨቅላ ህፃን ያላት ጤና ባለሙያ እንደታሰረች ገልጸው፣ በዋስ እንደትለቀቅ እንኳ ቢሞከር ፈቃደኛ አካል አለመኖሩን ጠቁመዋል።

“ አጥቢ ከመሆኗ አንፃር ቀነ ገደብ ተጠይቆ ነበር። ፍርድ ቤት ዋስትና እንዲሰጣት ውሳኔ ቢያስተላልፍም እንዳትወጣ በፓሊስ ተከልክላለች ” ሲሉ ነው የወቀሱት።

የታሳሪ ቤተሰቦች፣ የታሰሩት የጤና ባለሙያዎች እንደሆኑ፣ ብዙ የህክምና ተገልጋዮች መጉላላታቸውም ከግምት ሊገባ እንደሚገባ አሳስበው፣ በፍጥነት እንዲፈቱ ጠይቀዋል።

የታሰሩት ለምን እንዳልተፈቱ ምላሽ ለማግኘት የጸጥታ አካላትን ለማካተት የተደረገው መከራ ስልክ ለማንሳት ፈቃደኞች ባለሆናቸው ለጊዜው አልተሳካም።

የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ከዚህ ቀደም  ጠይቀነው፣ በሌሎች ሆስፒታሎችም ጭምር ከ2000 በላይ ሠራተኞች ክፍያው እንዳልተፈጸመላቸው፣ የታሰሩትን ለማስፈታትም እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ነበር።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶአደሮች ተፈናቅለዋል " - የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር 🚨" አሁንም ከኬንያ ቱርካና ግዛት በኩል ዛቻዎች ስላሉ ስጋት ዉስጥ ነን ጥበቃና ከለላ ይደረግልን " - አርብቶአደሮች በኢትዮጵያና ኬንያ ድንበር ደቡብ ኦሞ ዳሰነች ወረዳና በኬንያ ቱርካና ግዛት አዋሳኝ አከባቢ ባለፉት ሁለት ቀናት በአሳ ማስገሪያ መረብና ጀልባ ስርቆቶች እንደተቀሰቀሰ በተነገረዉ ግጭት የበርካቶች…
" ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እየተመለሱ ነዉ ፤ የአስክሬን ፍለጋዉም ተጠናክሮ ቀጥሏል " - የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ እና በሰሜን ኬንያ ቱርካና የድንበር አከባቢ ተከስቶ በነበረዉ ግጭት ምክንያት ስየስ ከተባለ የዳሰነች መንደር ተፈናቅለዉ የነበሩ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶአደሮች ወደ ቀያቸዉ መመለስ መጀመራቸዉን የዳሰነች ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በቀጠናዉ በአሳ ማስገሪያ መረብና ጀልባ ስርቆቶች መነሻ እንደተቀሰቀሰ በተገለፀዉ ግጭት ከሁለቱም ሀገሮች ከ30 በላይ አርብቶአደሮች ሕይወት መጥፋቱን መዘገባችን አይዘነጋም።

ግጭቱን ተከትሎም ኬንያን ከኢትዮጵያ ጋር የሚያዋስናት የቱርካና ሀይቅ ሰሜናዊ ጠረፍ ላለፉት አምስት ቀናት ከእንቅስቃሴ ዉጪ ሲሆን ከዳሰነች ወረዳ ስየስ መንደር በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶ አደሮች በአቅራቢያቸዉ ወደሚትገኘዉ ሌላ መንደር ተፈናቅለዉ ነበር።

በትናትዉ ዕለት የዳሰነችና የቱርካና አከባቢ አስተዳደሮች ባሉበት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ እና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር የተመራ ልዑክ ከኢትዮጵያ በኩል በኬንያ የቱርካና ካውንቲ የፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነርና የአከባበው የፓርላማ ተወካይ የተመራ ልዑክ በሁለቱ ሀገራት የድንበር አከባቢ ተፈጠሮ የነበረዉን ግጭት በፍጥነት ለመፍታትና አከባቢውን ወደነበረበት ሰላም ለመመለስ መነጋገራቸዉን ተከትሎ ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸዉ የመመለስ እየተሰራ እንደሆነ አቶ ታደለ ሀቶ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ከዚሁ ጎን ለጎን በሀይቅ ዉስጥ የጠፉ አስከሬኖች የማፈላለጉ ስራም ተጠናክሮ መቀጠሉን ያነሱት አቶ ታደለ በሁለቱም ወገን የተወሰዱ ንብረቶችን የማስመለስና በአከባቢዉ ጠንካራ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ሥራዎችን ተጠናክረዉ በሚቀጥሉበት ዙሪያ ዉይይት ማድረጋቸዉን አስታዉቀዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
" ከየካቲት 24 በኋላ የፋይዳ መታወቂያ የሌለው ደንበኛ የኢትዮ ጅቡቲ የባቡር ትኬት መቁረጥ አይችልም " - የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር አክስዮን ማህበር

የኢትዮ ጅቡቲ የባቡር መንገድ አክስዮን ማህበር ለመንገደኞች የጉዞ ትኬት የሚያገኙበትን መንገድ ከሰኞ የካቲት 17/2017 ዓ/ም ጀምሮ  ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ ማድረጉን ገልጿል።

ከሁለት ቀን በፊት የተጀመረውን በኦንላይን ትኬት የመቁረጥ ሂደት አገልግሎቱን ለማግኘት የፋይዳ መታወቂያ ግዴታ መደረጉን የኢትዮጵያ ጅቡቲ የባቡር መንገድ አክስዮን ማህበር የኮምዩኒኬሽን ባለሞያ የሆኑት ወ/ሮ እስራኤል ወልደ መስቀል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ወ/ሮ እስራኤል " ማስታወቂያዎችን ስንሰራ የቆየን በመሆኑ የፋይዳ መታወቂያ ግዴታ ነው ነገር ግን ይሄንን ሳምንት ልዩ በሆነ መንገድ እና ሰውም የአጠቃቀም ጉድለት ስላለ የጉዞ ትኬት እየቆረጥን እንገኛለን ከሚቀጥለው ሳምንት ሰኞ በኃላ ግን ያለ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የባቡሩን ትኬት ማግኘት አይቻልም " ብለዋል።

ክፍያው የሚፈጸመው በቴሌ ብር ሲሆን አገልግሎቱን ለማግኘት ለሃገር ውስጥ ተጠቃሚዎች የፋይዳ የምዝገባ ቁጥራቸውን ኢትዮጵያዊ ላልሆኑ ተጠቃሚዎች ደግሞ ፓስፖርታቸውን በመጠቀም ትኬት ማግኘት እንደሚችሉ አሳውቀዋል።

ባለሞያዋ በትኬት ዋጋ ላይ ምንም አይነት ጭማሪ አለመኖሩን አንስተው በነባሩ ዋጋ ዲጂታላይዝ ብቻ መደረጉን ጠቁመዋል።

ከዚህ ቀደም አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ ፉሪ የሚገኙ የትኬት ሽያጭ ቢሮዎች አሰራሩ ዲጂታላይዝ ስለሆነ የመንገደኞችን የአገልግሎት ትኬት የመቁረጥ ስራ እንደማይሰሩ ወ/ሮ እስራኤል ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ፎቶ ፦ ከሌሊቱ 10:35 ሰዓት ላይ በአዲስ ከተማ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 7 ሀብተጊዮርጊስ ድልድይ አካባቢ በመኖሪያና ንግድ ቤቶች ላይ የእሳት አደጋ አጋጥሞ እንደነበር የእሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር የኮሚሽን አሳውቋል።

የእሳት አደጋው በቁጥጥር ስር ማዋል የተቻለ ሲሆን የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ፣ የጸጥታ አካላት የአካባቢዉ ማህበረሰብ እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ከፍተኛ ርብርብ ማድረጋቸውን ገልጿል።

ኮሚሽኑ " አደጋ የደረሰበት ቦታና አካባቢ በከተማ ደረጃ ለእሳት አደጋ ተጋላጭ ተብለዉ ከተለዩ የመኖሪያና የንግድ አካባቢዎች አንዱ ነው " ያለ ሲሆን " ቤቶቹ የተገነቡበት ግብአት የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታዉ እንዲሁም የአደጋ ጊዜ ተሽከርካሪዎችን አለማስገባቱ ተደማምሮ የእሳት አደጋዉ እንዲሰፋ ምክንያት ሆኗል " ብሏል።

በእሳት አደጋዉ በሰዉና በንብረት ላይ የደረሰዉን ጉዳት እንዲሁም የአደጋዉ መንስዔ ተጣርቶ እንደሚገለጽ አመልክቷል።

@tikvahethiopia