This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ፖሽ የእንጨት ስራዎች / Posh wood works
ከመጀመሪያዎቹ መሀል ይሁኑ ! ውጭ ሀገር ያዩት እርሶ ቤትም አይቀርም በሀገራችን የመጀመሪያው የሆኑ የአልሙኒየም ፍሬም መስታዎት በሮችን የተላበሱ የእንጨት ስራ ውጤቶችን ለእናንተ ለደንበኞቻችን ፤ይዘን መተናል
" ልዩ ውበት ይገባዎታል! "
ፖሽ የእንጨት ስራዎች / Posh wood works
Closet / Cupboard
Kitchen cabinet
TV Unit
Dressing
📍አድራሻ፦ ጀሞ 1 የተባበሩት ማደያ ውሰጥ
- 22 ከጎላጎል አጠገብ ኖህ ሪልስቴት 3ኛ ፎቅ
📲 0929414154
📲 0983915600
📲 0954777788 /99
ቴሌ ግራማችንን ይቀላቀሉ
https://yangx.top/webnewood
ከመጀመሪያዎቹ መሀል ይሁኑ ! ውጭ ሀገር ያዩት እርሶ ቤትም አይቀርም በሀገራችን የመጀመሪያው የሆኑ የአልሙኒየም ፍሬም መስታዎት በሮችን የተላበሱ የእንጨት ስራ ውጤቶችን ለእናንተ ለደንበኞቻችን ፤ይዘን መተናል
" ልዩ ውበት ይገባዎታል! "
ፖሽ የእንጨት ስራዎች / Posh wood works
Closet / Cupboard
Kitchen cabinet
TV Unit
Dressing
📍አድራሻ፦ ጀሞ 1 የተባበሩት ማደያ ውሰጥ
- 22 ከጎላጎል አጠገብ ኖህ ሪልስቴት 3ኛ ፎቅ
📲 0929414154
📲 0983915600
📲 0954777788 /99
ቴሌ ግራማችንን ይቀላቀሉ
https://yangx.top/webnewood
#HaileResortJimma
“ ወደ 1.7 ቢሊዮን ብር ፈሰስ ተደርጎበታል" - ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ስላሴ
የሻለቃ ኃይሌ ገብረ ስላሴ ሆቴልና ሪዞርት 10ኛ መዳረሻ በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ ዛሬ (ሐሙስ ታኀሳስ 24 ቀን 2017 ዓ/ም) ተመርቋል።
ሆቴሉ 3 የመመገቢያ አደራሾች፣ የልጆች መጫወቻ፣ ሞሮኮ ባዝ እንዳሉት፣ ለ210 ሰዎች ቋሚ የሥራ እድል እንደፈጠረ፣ ለወደፊት ደግሞ ወደ 400 ለሚሆኑ ሰዎች የሥራ እድል እንደሚፈጥር ተነግሮለታል።
ሆቴሉ አሁን የተጠናቀቁ ወደ 106 ክፍሎች እንዳሉት፣ ሁሉም ሰጠናቀቁ ደግሞ ወደ 114 ክፍሎች እንደሚኖሩት ተመልክቷል።
በመርሀ ግብሩ የተገኙት ሻለቃ ኃይሌ ባደረጉት ንግግር፣ በአንድ ዓመት ከስምንት ወራት የሆቴሉን ግንባታ በአጭር ጊዜ ላጠናቀቁት ሠራተኞች በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል።
ጅማ ላይ የኮንስትራክሽን እቃ ውድ መሆኑን የገለጹት ሻለቃ ኃይሌ፣ “ብሎኬት ከአዲስ አበባ እየተጓጓዘ ነው የተሰራው” ሲሉ ተናግረዋል።
“ኮንስትራክሽኑን ውድ ያደረገው የመንገዱ መበላሸት ነው” ያሉት ኃይሌ፣ “ብሎኬቶች እየተሰባበሩ ነበር። ሁሉ ሰው በአውሮፕላን መጓጓዝ አይችልም” ነው ያሉት።
የሆቴሉን ወጪ በተመለከተ በገለጹበት አውድ ደግሞ፣ “ወደ 1.7 ቢሊዮን ብር ፈሰስ ተደርጎበታል” ብለዋል።
የጅማ ከተማ ከንቲባ አቶ ጣሃ ቀመር በመርሀ ግብሩ ተገኝተው ባደረጉት ገለጻ ደግሞ፣ “ጅማ አባጅፋር ሁሉንም የምታቅፍ ከተማ ናት። ባለሃብቶች ጅማን ለመቀየር ከኅይሌ እንዲማሩ ማሳያ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።
የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ትጃኒ ናስር ፥ “ኃይሌ ሲጠራ እንስቃለን፣ ኃይሌ ሲጠራ እንባችን ይመጣል፣ ኃይሌ እንኳን አገኘንህ” በማለት ደስታቸውን ገልጸዋል።
“ሱልልታ ላይ የኃይሌን ሆቴል ሳይ እንዲህ አይነት ሆቴል ጅማ ላይ ቢገነባ ብዬ ተመኝቼ ነበር። አሁን እንደዚህ ተሰርቶ አየሁትና እንባዬ ነው የመጣው። የተመረቀው ለኃይሌ ሳይሆን ለጅማ ህዝብ ነው” ሲሉ አመስግነዋል።
በ10ሩም የኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች 900 ሩሞች እንዳሉ፣ ለ2500 ሠራተኞች የሥራ እድል እንደተፈጠረ ተመልክቷል።
ፎቶ ፦ በግዛቱ አማረ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ ወደ 1.7 ቢሊዮን ብር ፈሰስ ተደርጎበታል" - ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ስላሴ
የሻለቃ ኃይሌ ገብረ ስላሴ ሆቴልና ሪዞርት 10ኛ መዳረሻ በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ ዛሬ (ሐሙስ ታኀሳስ 24 ቀን 2017 ዓ/ም) ተመርቋል።
ሆቴሉ 3 የመመገቢያ አደራሾች፣ የልጆች መጫወቻ፣ ሞሮኮ ባዝ እንዳሉት፣ ለ210 ሰዎች ቋሚ የሥራ እድል እንደፈጠረ፣ ለወደፊት ደግሞ ወደ 400 ለሚሆኑ ሰዎች የሥራ እድል እንደሚፈጥር ተነግሮለታል።
ሆቴሉ አሁን የተጠናቀቁ ወደ 106 ክፍሎች እንዳሉት፣ ሁሉም ሰጠናቀቁ ደግሞ ወደ 114 ክፍሎች እንደሚኖሩት ተመልክቷል።
በመርሀ ግብሩ የተገኙት ሻለቃ ኃይሌ ባደረጉት ንግግር፣ በአንድ ዓመት ከስምንት ወራት የሆቴሉን ግንባታ በአጭር ጊዜ ላጠናቀቁት ሠራተኞች በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል።
ጅማ ላይ የኮንስትራክሽን እቃ ውድ መሆኑን የገለጹት ሻለቃ ኃይሌ፣ “ብሎኬት ከአዲስ አበባ እየተጓጓዘ ነው የተሰራው” ሲሉ ተናግረዋል።
“ኮንስትራክሽኑን ውድ ያደረገው የመንገዱ መበላሸት ነው” ያሉት ኃይሌ፣ “ብሎኬቶች እየተሰባበሩ ነበር። ሁሉ ሰው በአውሮፕላን መጓጓዝ አይችልም” ነው ያሉት።
የሆቴሉን ወጪ በተመለከተ በገለጹበት አውድ ደግሞ፣ “ወደ 1.7 ቢሊዮን ብር ፈሰስ ተደርጎበታል” ብለዋል።
የጅማ ከተማ ከንቲባ አቶ ጣሃ ቀመር በመርሀ ግብሩ ተገኝተው ባደረጉት ገለጻ ደግሞ፣ “ጅማ አባጅፋር ሁሉንም የምታቅፍ ከተማ ናት። ባለሃብቶች ጅማን ለመቀየር ከኅይሌ እንዲማሩ ማሳያ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።
የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ትጃኒ ናስር ፥ “ኃይሌ ሲጠራ እንስቃለን፣ ኃይሌ ሲጠራ እንባችን ይመጣል፣ ኃይሌ እንኳን አገኘንህ” በማለት ደስታቸውን ገልጸዋል።
“ሱልልታ ላይ የኃይሌን ሆቴል ሳይ እንዲህ አይነት ሆቴል ጅማ ላይ ቢገነባ ብዬ ተመኝቼ ነበር። አሁን እንደዚህ ተሰርቶ አየሁትና እንባዬ ነው የመጣው። የተመረቀው ለኃይሌ ሳይሆን ለጅማ ህዝብ ነው” ሲሉ አመስግነዋል።
በ10ሩም የኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች 900 ሩሞች እንዳሉ፣ ለ2500 ሠራተኞች የሥራ እድል እንደተፈጠረ ተመልክቷል።
ፎቶ ፦ በግዛቱ አማረ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Earthquake : እየተከሰተ ያለው ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ዛሬም ቀጥሏል። ዛሬ ረቡዕ ከጥዋት አንስቶ እስከ ምሽት በተለያየ ጊዜ በሬክተር ስኬል ከ4.5 እስከ 4.9 ድረስ የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ በአዋሽ ፈንታሌና አካባቢው ተከስቷል። ሰሞኑን ጠንከር ያለውና ተደጋግሞም እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ አፋር ላይ የንብረት ጉዳት አድርሷል። ወገኖቻችን የመሬት መንቀጥቀጡ ካየለባቸው ቦታዎች…
#Earthquake
ዛሬ በሬክተር ስኬል 5.1 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ እንደነበር የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ገልጿል።
የመሬት መንቀጥቀጡ ከአዋሽ በሰሜን 36 ኪ/ሜ በኩል ነው የተመዝገበው።
የመሬት መንቀጥቀጡ ንዝረት አዲስ አበባ እና ቦታዎችም የተሰማ ሲሆን በተለይ በአዲስ አበባ ንዝረቱ በደንብ ይሰማ ነበር።
አንድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ፥ " የመሬት ንዝረት እየተሰማ ነው ፤ ያለሁት ቦሌ አካባቢ መኪና ውስጥ ነው ፤ በደቂቃዎች ልዩነት ሁለቴ አጋጥሟል " ሲሉ ቃላቸውን ሰጥተዋል።
ሌላ አንድ የቤተሰባችን አባል " መኪናዬ ውስጥ ሆኜ ትንሽ ንቅንቅ ስል ተሰምቶኛል ወደ አያት አካባቢ ቆሜ ባለሁበት " ሲል ገልጿል።
ከሰሞኑን የተለያየ መጠን ያላቸው ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶች እየተመዘገቡ ሲሆን የዛሬው 5.1 ከፍ ካሉት አንዱ ነው።
በሬክተር ስኬል 5.1 ከተመዘገበው የመሬት መንቀጥቀጥ በኃላ በሬክተር ስኬል 4.5 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥም ነበር።
አፋር ላይ በተለይ የመሬት መንቀጥቀጡ አይሎ በሚሰማባቸው ቦታዎች ንብረት ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን በርካቶችም ከቤታቸው ሸሽተው ሄደዋል።
#TikvahEthiopiaFamily
@tikvahethiopia
ዛሬ በሬክተር ስኬል 5.1 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ እንደነበር የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ገልጿል።
የመሬት መንቀጥቀጡ ከአዋሽ በሰሜን 36 ኪ/ሜ በኩል ነው የተመዝገበው።
የመሬት መንቀጥቀጡ ንዝረት አዲስ አበባ እና ቦታዎችም የተሰማ ሲሆን በተለይ በአዲስ አበባ ንዝረቱ በደንብ ይሰማ ነበር።
አንድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ፥ " የመሬት ንዝረት እየተሰማ ነው ፤ ያለሁት ቦሌ አካባቢ መኪና ውስጥ ነው ፤ በደቂቃዎች ልዩነት ሁለቴ አጋጥሟል " ሲሉ ቃላቸውን ሰጥተዋል።
ሌላ አንድ የቤተሰባችን አባል " መኪናዬ ውስጥ ሆኜ ትንሽ ንቅንቅ ስል ተሰምቶኛል ወደ አያት አካባቢ ቆሜ ባለሁበት " ሲል ገልጿል።
ከሰሞኑን የተለያየ መጠን ያላቸው ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶች እየተመዘገቡ ሲሆን የዛሬው 5.1 ከፍ ካሉት አንዱ ነው።
በሬክተር ስኬል 5.1 ከተመዘገበው የመሬት መንቀጥቀጥ በኃላ በሬክተር ስኬል 4.5 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥም ነበር።
አፋር ላይ በተለይ የመሬት መንቀጥቀጡ አይሎ በሚሰማባቸው ቦታዎች ንብረት ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን በርካቶችም ከቤታቸው ሸሽተው ሄደዋል።
#TikvahEthiopiaFamily
@tikvahethiopia
#ዮናታን_ቢቲ_ፈርኒቸር
በዓሉን አስመልክቶ የተደርገው ልዩ ቅናሽ ሳያመልጥዎ እነዚህን ውብ እቃዎች የግልዎ ያድርጉ።
🌐 የማህበራዊ ገጾቻችንን ይቀላለቀሉ ፦
Telegram 👉 Telegram/yonatanbtfurniture
Facebook 👉 Facebook/yonatanbtfurniture
Instagram 👉 Instagram/yonatanbtfurniture
TikTok 👉 TikTok/yonatanbtfurniture
📍አድራሻችን
1. ፒያሳ እሪ በከንቱ ቢቲ ታወር (ከኢቲዮ ሴራሚክ ዝቅ ብሎ)
2. ከዊንጌት አደባባይ አለፍ ብሎ ከአቢሲኒያ ባንክ ፊትለፊት
3. ከሲኤምሲ አደባባይ ወደ አያት መንገድ መሪ ሳይደርስ (ዘመን ባንክ አጠገብ)
☎️ +251957868686/ +251995272727/ +251993828282
በዓሉን አስመልክቶ የተደርገው ልዩ ቅናሽ ሳያመልጥዎ እነዚህን ውብ እቃዎች የግልዎ ያድርጉ።
🌐 የማህበራዊ ገጾቻችንን ይቀላለቀሉ ፦
Telegram 👉 Telegram/yonatanbtfurniture
Facebook 👉 Facebook/yonatanbtfurniture
Instagram 👉 Instagram/yonatanbtfurniture
TikTok 👉 TikTok/yonatanbtfurniture
📍አድራሻችን
1. ፒያሳ እሪ በከንቱ ቢቲ ታወር (ከኢቲዮ ሴራሚክ ዝቅ ብሎ)
2. ከዊንጌት አደባባይ አለፍ ብሎ ከአቢሲኒያ ባንክ ፊትለፊት
3. ከሲኤምሲ አደባባይ ወደ አያት መንገድ መሪ ሳይደርስ (ዘመን ባንክ አጠገብ)
☎️ +251957868686/ +251995272727/ +251993828282
ከ600 በላይ ተሳታፊዎች የሚኖሩት የምልክት ቋንቋ ጉባዔ በቅርቡ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
የራሷን የምልክት ቋንቋ የምትጠቀመው ኢትዮጵያ 15ኛውን የምልክት ቋንቋ ዓለም-አቀፍ የምርምር ጉባዔን (TISLR) ከመጪው ጥር 6 እስከ 9 በአዲስ አበባ ታስተናግዳለች።
ከዚህ ቀደም በነበሩት ጉባኤዎች ተሳታፊ የነበረው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተወዳድሮ የዘንድሮውን ጉባዔ እንዲያዘገጋጅ መመረጡን ተከትሎ ከሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ጉባዔውን አዘጋጅቷል።
ይህ በየ 3 ዓመቱ የሚካሄደው የምርምር ጉባኤ በአፍሪካ ሲዘጋጅ የመጀመሪያው መሆኑንና ዓለም አቀፍ የዘርፉ ምሁራንን ጨምሮ ከ600 በላይ ተሳታፊዎች የሚሳተፉበት እንደሚሆን ዛሬ በነበረው የቅድመ ጉባኤ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተገልጿል።
ኢትዮጵያ የምልከት ቋንቋን የብሔራዊ ቋንቋ እንዲሆን ከማድረግ አንጻር ምን እየሰራች ትገኛለች ?
የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚ/ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ ለዚህ ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ "የቋንቋ ፖሊሲው ለምልክት ቋንቋ እውቅና ይሰጣል ይህንን ሥራ ማድነቅ ያስፈልጋል፤ የብሔራዊ ቋንቋ ለማድረግ ግን ሰፊ ጥናቶች መስራት ይጠበቅብናል።" ብለዋል።
ይሄም ጉባዔም የምልክት ቋንቋዎችን እንደ ህጋዊና አስፈላጊ ቋንቋዎች እውቅና ለመስጠት የሚደረገውን ጥረት የሚደግፍ ይሆናል ነው ያሉት።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕረዚዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በመግለጫው ወቅት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የምልክት ቋንቋ በማስተማር 15 ዓመታትን ማስቆጠሩን ጠቅሰው በጉባዔው በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታዎች ላይ የተሰሩ ሥራዎች የሚቀርቡበት ነው ብለዋል።
አክለውም፥ የዩኒቨርስቲው ተመራማሪዎች፣ መምህራን፤ ተማሪዎች ተሳታፊ እንዲሆኑ እና ከዓለም አቀፍ አቻዎቻቸው እንዲማማሩ እድል ይሰጣል ያሉት ዶ/ር ሳሙኤል "የምልክት ቋንቋ እውቅና እንዲኖረው የበኩላችንን አስተዋጽኦ የምናበረክትበት ይሆናል" ሲሉ ገልጸዋል።
በዚህ ጉባዔ ኢትዮጵያ ምን የምታቀርበው ነገር አዘጋጅታለች ?
ዶ/ር ኤርጎጌ በዚህ ጉባኤ ከሚቀርቡ የጥናትና ምርምር ሥራዎች በተጨማሪ የተሰሩ ሥራዎችን እንድናቀርብ እድል ይሰጠናል ያሉ ሲሆን፤ በተለይም የመጨረሻ የዝግጅት ምዕራፍ ላይ የሚገኘውን የአካል ጉዳተኞች መብቶች የተጠቃለለ አዋጅን ጠቅሰዋል።
የአካል ጉዳተኞች መብቶች የተጠቃለለ አዋጅ ምን ይዟል?
በዚህ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የአካል ጉዳተኞች ጉዳይ ዳይሬክተር አቶ አሳልፈው አመዲን፥ አዋጁ ተበታትኖ የነበሩትን መብቶች ወደ አንድ በማሰባሰብ በተለይም ተጠያቂነትን የሚያሰፍን እንደሆነ ገልጸውልናል።
ከ90 ያላነሱ አንቀጾችን ይዟል በተባለው በዚህ የተጠቃለለ አዋጅ፥ የምልክት ቋንቋን በተመለከተ መጠቀሱን ያነሱት ዳይሬክተሩ፥ "የምልክት ቋንቋ እንደ አንድ ኢትዮጵያ ውስጥ እውቅና እንደተሰጣቸው ቋንቋዎች ታስቦ ተግባራዊ መደረግ አለበት የሚል ተካቶበታል" ብለዋል።
የምልክት ቋንቋን መጠቀም በኢትዮጵያ አስገዳጅ ነው ?
ይህንን ጥያቄ ያቀረብንላቸው የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የማኅበራዊ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሁሪያ አሊ "በተለይም የመስማት የተሳናቸው ተሳታፊዎች ባሉባቸው መድረኮች እንዲሁም በሚዲያ አዋጁ በግልጽ እንደተቀመጠው የመገናኛ ብዙኃን የምልክት ቋንቋ የመጠቀም ግዴታ ተጥሎባቸዋል" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
የጉባዔው አዘጋጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉባዔው መሳተፍ የሚፈልጉ በዚህ http://tislrethiopia.org/registration/ ሊንክ ተጨማሪ መረጃዎችን መውሰድና መመዝገብ እንደሚችሉ ገልጸዋል።
#TikvahEthiopia
#SignLanguage
#EthSL
@tikvahethiopia
የራሷን የምልክት ቋንቋ የምትጠቀመው ኢትዮጵያ 15ኛውን የምልክት ቋንቋ ዓለም-አቀፍ የምርምር ጉባዔን (TISLR) ከመጪው ጥር 6 እስከ 9 በአዲስ አበባ ታስተናግዳለች።
ከዚህ ቀደም በነበሩት ጉባኤዎች ተሳታፊ የነበረው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተወዳድሮ የዘንድሮውን ጉባዔ እንዲያዘገጋጅ መመረጡን ተከትሎ ከሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ጉባዔውን አዘጋጅቷል።
ይህ በየ 3 ዓመቱ የሚካሄደው የምርምር ጉባኤ በአፍሪካ ሲዘጋጅ የመጀመሪያው መሆኑንና ዓለም አቀፍ የዘርፉ ምሁራንን ጨምሮ ከ600 በላይ ተሳታፊዎች የሚሳተፉበት እንደሚሆን ዛሬ በነበረው የቅድመ ጉባኤ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተገልጿል።
ኢትዮጵያ የምልከት ቋንቋን የብሔራዊ ቋንቋ እንዲሆን ከማድረግ አንጻር ምን እየሰራች ትገኛለች ?
የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚ/ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ ለዚህ ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ "የቋንቋ ፖሊሲው ለምልክት ቋንቋ እውቅና ይሰጣል ይህንን ሥራ ማድነቅ ያስፈልጋል፤ የብሔራዊ ቋንቋ ለማድረግ ግን ሰፊ ጥናቶች መስራት ይጠበቅብናል።" ብለዋል።
ይሄም ጉባዔም የምልክት ቋንቋዎችን እንደ ህጋዊና አስፈላጊ ቋንቋዎች እውቅና ለመስጠት የሚደረገውን ጥረት የሚደግፍ ይሆናል ነው ያሉት።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕረዚዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በመግለጫው ወቅት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የምልክት ቋንቋ በማስተማር 15 ዓመታትን ማስቆጠሩን ጠቅሰው በጉባዔው በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታዎች ላይ የተሰሩ ሥራዎች የሚቀርቡበት ነው ብለዋል።
አክለውም፥ የዩኒቨርስቲው ተመራማሪዎች፣ መምህራን፤ ተማሪዎች ተሳታፊ እንዲሆኑ እና ከዓለም አቀፍ አቻዎቻቸው እንዲማማሩ እድል ይሰጣል ያሉት ዶ/ር ሳሙኤል "የምልክት ቋንቋ እውቅና እንዲኖረው የበኩላችንን አስተዋጽኦ የምናበረክትበት ይሆናል" ሲሉ ገልጸዋል።
በዚህ ጉባዔ ኢትዮጵያ ምን የምታቀርበው ነገር አዘጋጅታለች ?
ዶ/ር ኤርጎጌ በዚህ ጉባኤ ከሚቀርቡ የጥናትና ምርምር ሥራዎች በተጨማሪ የተሰሩ ሥራዎችን እንድናቀርብ እድል ይሰጠናል ያሉ ሲሆን፤ በተለይም የመጨረሻ የዝግጅት ምዕራፍ ላይ የሚገኘውን የአካል ጉዳተኞች መብቶች የተጠቃለለ አዋጅን ጠቅሰዋል።
የአካል ጉዳተኞች መብቶች የተጠቃለለ አዋጅ ምን ይዟል?
በዚህ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የአካል ጉዳተኞች ጉዳይ ዳይሬክተር አቶ አሳልፈው አመዲን፥ አዋጁ ተበታትኖ የነበሩትን መብቶች ወደ አንድ በማሰባሰብ በተለይም ተጠያቂነትን የሚያሰፍን እንደሆነ ገልጸውልናል።
ከ90 ያላነሱ አንቀጾችን ይዟል በተባለው በዚህ የተጠቃለለ አዋጅ፥ የምልክት ቋንቋን በተመለከተ መጠቀሱን ያነሱት ዳይሬክተሩ፥ "የምልክት ቋንቋ እንደ አንድ ኢትዮጵያ ውስጥ እውቅና እንደተሰጣቸው ቋንቋዎች ታስቦ ተግባራዊ መደረግ አለበት የሚል ተካቶበታል" ብለዋል።
የምልክት ቋንቋን መጠቀም በኢትዮጵያ አስገዳጅ ነው ?
ይህንን ጥያቄ ያቀረብንላቸው የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የማኅበራዊ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሁሪያ አሊ "በተለይም የመስማት የተሳናቸው ተሳታፊዎች ባሉባቸው መድረኮች እንዲሁም በሚዲያ አዋጁ በግልጽ እንደተቀመጠው የመገናኛ ብዙኃን የምልክት ቋንቋ የመጠቀም ግዴታ ተጥሎባቸዋል" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
የጉባዔው አዘጋጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉባዔው መሳተፍ የሚፈልጉ በዚህ http://tislrethiopia.org/registration/ ሊንክ ተጨማሪ መረጃዎችን መውሰድና መመዝገብ እንደሚችሉ ገልጸዋል።
#TikvahEthiopia
#SignLanguage
#EthSL
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Haile " ሙሉን አፍርሰን እየገነባን ነው። ከመንግሥት ምንም ማካካሻ አልተደረገልኝም " - ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ከዚህ በፊት በሻሸመኔ በጸጥታ ችግር ስለወደመው ሆቴል ሁኔታ እና በጎንደር ከተማ በሚገኘው ሪዞርት በኩል በጸጥታ ችግር የገጠማቸውን የገቢ መቀዛቀዝን በተመለከተ ዛሬ በወላይታ ሶዶ ከተማ የሆቴል ምረቃ መርሀ ግብር በተገኙበት ወቅት ማብራሪያ ሰጥተዋል። ከዚህ…
“የካሳዋን ጉዳይ አሁንም እየጠበኳት ነው። ግን የለችም” - ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ስላሴ
የሻሸመኔ ኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት ከዚህ ቀደም ከፍተኛ ውድመት እንደደረሰበት የሚታወቅ ሲሆን ፣ አፍርሰው እየሰሩ እንደነበር ሻለቃ ኃይሌ ገ/ስላሴ ገልጸው ነበር።
ከ10 ወራት በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ሙሉውን አፍርሰን እየሰራን ነው። ከመንግስት ምንም አይነት ማካካሻ አልተሰጠኝም ” ነበር ያሉት።
“ እኔ አላቃጠልኩትም። መንግስት እንደ መንግስት መወጣት ነበረበት ” ብለው፣ “ እኛ ለብዙ አመታት እንግዲህ በኢንቨስትመንት ተሰማርተን እየሰራን ነው ” ማለታቸው አይዘነጋም።
አሁንስ ከመንግሰት ካሳ ተከፈላቸው ?
የሻሸመኔው ሆቴልና ሪዞርት ለደረሰው ውድመት መንግስት ከሳ እንዳልከፈለዎት ገልጸው ነበር፣ ተከፈለዎት ? ተብሎ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ጥያቄ ያቀረበላቸው ሻለቃ ኃይሌ አሁንም ካሳ እንዳልተከፈላቸው ተናግረዋል።
“ የካሳዋን ጉዳይ እየጠበኳት ነው ግን የለችም። እሷን ነገር እብቃለሁ ” ነው ያሉት።
የውጪ ኢንቨስተሮች እንዲመጡ እንዲህ አይነት አደጋዎች ሲደርሱ ካሳ ቢከፈል መልካም መሆኑን አስረድተው፣ “ ዞሮ ዞሮ ግን አልሆነም። አልተቀበልኩም ” ብለዋል።
ሆቴሉን ከባለሦስት ወደ ባለአራት ኮከብ አድርገው እየሰሩ መሆኑን ገልጸው፣ “ ህንፃ እያፈረሱ መስሪት ሁለት ሥራ ነው አንደኛ ማፍረስ፣ ሁለተኛ ደግሞ መገንባት አለ ” ሲሉ ተናግረዋል።
“ በአጠቃላይ ግን ስለሆቴልና ሪዞርት ሲወራ እከሌ ሆቴል ከፈተ፣ እከሌ ሪዞርት ከፈተ የሚለው ምንም ፋይዳ የለውም። ማነው የሚተባበረው ? ማነው አብሮት ያለው? ከአዲስ አበባ ከ300 ኪሎ ሜትር ሲመጣ ሴፍ ነው ወይ? የሚሉት ምላሽ የሚፈልጉ ናቸው ” ሲሉም አስገንዝበዋል።
በተያያዘ ዜና በአማራ ክልል በመንግስትና በፋኖ ታጣቂዎች እየተካሄደ ያለውን የተኩስ ልውውጥ ተከትሎ በጎንደር ከተማ ያለው ሆቴላቸው ገቢው እየተቀዛቀዘ መሆኑንም ከዚህ ቀደም መግለጻቸው ይታወሳል።
የጎንደሩ ሆቴል ገቢው በምን ያህል ቀንሷል ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ላቀረበላቸው ጥያቄ ሻለቃ ኃይሌ፣ “ አለ እንዴ ለመሆኑ ቢዝነሱ? 56፣ 57 ሩም ተይዞ 5 ሰዎች ስላሳደርክ ምንድን ነው ገቢው? ” የሚል ጥያቄ አዘል ምላሽ ሰጥተውም ነበር።
አሁንስ የጎንደሩ ሆቴል ገቢ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል? በሚል ዛሬ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ደግሞ፣ “ በጎንደሩ ሆቴል የሚፈለገውን ያህል እየተሰራ አይደለም ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
የቀጣይ የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርቶች መዳረሻ የት እንደሚሆን በዛሬ የጅማ ሪዞርት ምረቃ መርሀ ግብር ላይ ማብራሪያ የሰጡት ሻለቃ ኃይሌ፣ የሻሸመኔውንና የደብረ ብርሃኑን ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፣ “ ድሬዳዋና ሀረርም ቀጣይ መዳረሻችን ይሆናል” ሲሉ ጠቁመዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የሻሸመኔ ኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት ከዚህ ቀደም ከፍተኛ ውድመት እንደደረሰበት የሚታወቅ ሲሆን ፣ አፍርሰው እየሰሩ እንደነበር ሻለቃ ኃይሌ ገ/ስላሴ ገልጸው ነበር።
ከ10 ወራት በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ሙሉውን አፍርሰን እየሰራን ነው። ከመንግስት ምንም አይነት ማካካሻ አልተሰጠኝም ” ነበር ያሉት።
“ እኔ አላቃጠልኩትም። መንግስት እንደ መንግስት መወጣት ነበረበት ” ብለው፣ “ እኛ ለብዙ አመታት እንግዲህ በኢንቨስትመንት ተሰማርተን እየሰራን ነው ” ማለታቸው አይዘነጋም።
አሁንስ ከመንግሰት ካሳ ተከፈላቸው ?
የሻሸመኔው ሆቴልና ሪዞርት ለደረሰው ውድመት መንግስት ከሳ እንዳልከፈለዎት ገልጸው ነበር፣ ተከፈለዎት ? ተብሎ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ጥያቄ ያቀረበላቸው ሻለቃ ኃይሌ አሁንም ካሳ እንዳልተከፈላቸው ተናግረዋል።
“ የካሳዋን ጉዳይ እየጠበኳት ነው ግን የለችም። እሷን ነገር እብቃለሁ ” ነው ያሉት።
የውጪ ኢንቨስተሮች እንዲመጡ እንዲህ አይነት አደጋዎች ሲደርሱ ካሳ ቢከፈል መልካም መሆኑን አስረድተው፣ “ ዞሮ ዞሮ ግን አልሆነም። አልተቀበልኩም ” ብለዋል።
ሆቴሉን ከባለሦስት ወደ ባለአራት ኮከብ አድርገው እየሰሩ መሆኑን ገልጸው፣ “ ህንፃ እያፈረሱ መስሪት ሁለት ሥራ ነው አንደኛ ማፍረስ፣ ሁለተኛ ደግሞ መገንባት አለ ” ሲሉ ተናግረዋል።
“ በአጠቃላይ ግን ስለሆቴልና ሪዞርት ሲወራ እከሌ ሆቴል ከፈተ፣ እከሌ ሪዞርት ከፈተ የሚለው ምንም ፋይዳ የለውም። ማነው የሚተባበረው ? ማነው አብሮት ያለው? ከአዲስ አበባ ከ300 ኪሎ ሜትር ሲመጣ ሴፍ ነው ወይ? የሚሉት ምላሽ የሚፈልጉ ናቸው ” ሲሉም አስገንዝበዋል።
በተያያዘ ዜና በአማራ ክልል በመንግስትና በፋኖ ታጣቂዎች እየተካሄደ ያለውን የተኩስ ልውውጥ ተከትሎ በጎንደር ከተማ ያለው ሆቴላቸው ገቢው እየተቀዛቀዘ መሆኑንም ከዚህ ቀደም መግለጻቸው ይታወሳል።
የጎንደሩ ሆቴል ገቢው በምን ያህል ቀንሷል ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ላቀረበላቸው ጥያቄ ሻለቃ ኃይሌ፣ “ አለ እንዴ ለመሆኑ ቢዝነሱ? 56፣ 57 ሩም ተይዞ 5 ሰዎች ስላሳደርክ ምንድን ነው ገቢው? ” የሚል ጥያቄ አዘል ምላሽ ሰጥተውም ነበር።
አሁንስ የጎንደሩ ሆቴል ገቢ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል? በሚል ዛሬ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ደግሞ፣ “ በጎንደሩ ሆቴል የሚፈለገውን ያህል እየተሰራ አይደለም ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
የቀጣይ የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርቶች መዳረሻ የት እንደሚሆን በዛሬ የጅማ ሪዞርት ምረቃ መርሀ ግብር ላይ ማብራሪያ የሰጡት ሻለቃ ኃይሌ፣ የሻሸመኔውንና የደብረ ብርሃኑን ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፣ “ ድሬዳዋና ሀረርም ቀጣይ መዳረሻችን ይሆናል” ሲሉ ጠቁመዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia