TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.13K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Earthquake : ዛሬ ቅዳሜ ምሽት ጨምሮ ቀን ላይ ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ እንደነበር የአፋር ቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ገልጸዋል።

የመሬት መንቀጥቀጥ ድግግሞሹ እየጨመረ ነው ብለዋል።

አንድ የቤተሰባችን አባል፥ " አላህ መፍትሄውን ይስጠን ፤ ያረጋጋው እንጂ እጅግ በጣም ያስፈራል ፤ የዓለሙ ፈጣሪ አላህ መጨረሻችንን ያሳምረው " ሲል ገልጿል።

መሬት መንቀጥቀጡ እየፈጠረ ያለው ንዝረት በተለያዩ ከተሞችም መሰማቱን ለመረዳት ችለናል።

በፈንታሌ አካባቢ በተደጋጋሚ የተለያየ መጠን ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ እየተከሰተ የሚገኝ ሲሆን ትላንትና ከፍተኛ የሆነው በሬክተር ስኬል 5 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ነበር።

#TikvahEthiopiaFamilyAfar

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Earthquake አዋሽ አካባቢ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ መቀጠሉን የአካባቢው ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እየገለጹ ናቸው።

ትላንት ምሽት እንዲሁም ዛሬ ጥዋት አካባቢ ጠንከር ያለ የመሬት መንቀጥቀጥ እንደነበር ጠቁመዋል።

እንደ ' አሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ ድረገጽ ' መረጃ  ዛሬ እሁድ ከአዋሽ 33 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሬክተር ስኬል 4.8 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ነበር።

@tikvahethiopia