TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
ፍትህ ሚኒስቴር ፤ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲን አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ አውጥቷል። በዚሁ መግለጫ ፤ የሽግግር ፍትህ የባለሞያዎች ቡድን የተሰጠውን ኃላፊነት በወቅቱ ማጠናቀቁን ገልጿል። የሽግግር ፍትህ ፖሊሲው የመጨረሻ ረቂቅ ስራ እንዳለቀ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ተልኮ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ በመንግስት እንደሚፀድቅ ተመላክቷል። (መግለጫው ከላይ ተያይዟል) @tikvahethiopia
#Ethiopia

በረቂቅ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲው ላይ 8 የሰብዓዊ መብት የሲቪክ ድርጅቶች አስተያየት አቅርበዋል።

አስተያየት ያቀረቡት ፦
የመብቶች እና ዴሞክራሲ እድገት ማዕከል (CARD)
የሕግ ባለሙያዎች ለሰብዓዊ መብቶች (LHR)፣
የኢትዮጵያ ሴቶች ማህበራት ቅንጅት (NEWA)፣
ሴታዊት
የኢትዮጵያ ሠራተኞች መብት ተሟጋች (ELRW)፣
ስብስብ ለሰብዓዊ መብቶች በኢትዮጵያ (AHRE)
ሁሉን አቀፍ ራዕይ ለዲሞክራሲያዊ ኢትዮጵያ (IVIDE)
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ማዕከል (EHRDC) ናቸው።

ካቀረቡት አስተያየት መካከል ፦

" የሽግግር ፍትህ ረቂቅ ፖሊሲው እስካሁን ለህዝብ ይፋ ባይደረግም፣ ባጭር ጊዜ ውስጥ በሚኒስትሮች ምክር ቤት እንደሚፀድቅ መረጃዎች በመውጣት ላይ ይገኛሉ።

ነገር ግን ረቂቅ ፖሊሲውን በሚመለከት ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና ለጋሾች ጋር ከተደረጉ አጫጭር ውይይቶች በስተቀር በቂ ውይይት አልተደረገም።

ሰነዱ ይፋ ስላልሆነ ደርዝ ያለው አስተያየት ለመስጠትም ዕድል አልተገኘም።

ረቂቅ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ሰነዱ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቦ ከመፅደቁ በፊት ለህዝብ ይፋ ተደርጎ በባለድርሻ አካላት አስተያየት እንዲሰጥበት በአፅንኦት እንጠይቃለን።

በዚህ ረገድ በሽግግር ፍትህ አማራጮች ላይ ሰፊ ውይይቶች መካሄዳቸውን በበጎ የምንወስደው ቢሆንም፣ በፖሊሲ ዝግጅቱ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንደምንገኝ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ በረቂቅ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲው ላይ በቂ እና ፍሬያማ ውይይት እንዲደረግ አስቀድሞ ረቂቅ የፖሊሲ ሰነዱ ለህዝብ ይፋ እንዲሆን እንጠይቃለን።

ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በተጨማሪ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው ፦
- የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን፣
- የብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን፣
- የእምባ ጠባቂ ተቋም፣
- የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣
- የመገናኛ ብዙሃን፣
- የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣
- ምሁራን እና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ረቂቅ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ሰነዱን በዝርዝር ተመልከተው ከመፅደቁ በፊት አስተያየታቸውን እንዲያቀርቡ ዕድል እና በቂ ጊዜ ሊሰጥ ይገባል።

ይህን ማድረግም ለፖሊሲ ሰንዱ ጠቃሚ ግብዓት ከማስገኘት በተጨማሪ ፣ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲው በህዝብ ዘንድ የተሻለ ተቀባይነት እና ተፈጻሚነት እንዲኖረው ለማድረግ ያግዛል ብለን እናምናለን። "

(ሙሉ አስተያየታቸው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#ዐቢይ_ጾም

ብፁዕ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ለ2016 ዓ/ም የዐቢይ ጾመን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ከመልዕክታቸው የተወሰደ ፦

" ጾም ማለት እህልንና የእንስሳት ውጤቶችን ከመመገብ መከልከል ብቻ አይደለም፤ የእንስሳት ውጤት የሆኑትን ላለመመገብ ከምንወስነው በላይ እኩያት ፍትወታትንና ኃጣውእን ላለማስተናገድ በቁርጥ መወሰን ይጠበቅብናል፡፡

ስንጾም መገዳደልን፣ መጣላትን፣ መለያየትን፣ መገፋፋትን በሆነ ነገር መጐምጀትን እርም ብለን በመተው ዲያብሎስን የምናሸንፍበት የአሸናፊነት ኅሊና መላበስ አሰብን፣ ከክፉ ጎሊና እና ተግባር የተለየን ያህል በአንጻሩ ደግሞ በጎ ነገርን ለመስራት በእጅጉ መበርታት ይጠበቅብናል፡፡

ዲያብሎስ ተስፋ ቆርጦ የሚሸሸው ይቅር ይቅር ስንባባል፤ ለሰላምና ለአንድነት፣ ለፍቅርና ለስምምነት ስንቆም ነው፣ ከዚህም ጋር በእግዚአብሔር ፊት እጅግ ጸያፍ የሆነው ግብረ ኃጢአት በዚህች ምድር እንዳይፈጸም ማኅበረ ሰባችን በተጠንቀቅ ሲቆም ነው፤ እንደዚሁም ደም መፋሰስ፣ አለመተማመንና በሴት ልጆቻችን የሚደርሰው አካላዊ፣ መንፈሳዊና ሞራላዊ ጥቃት ሲቆም ነው፡፡

ጸማችን በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት የሚኖረው የተፈናቀሉት ወገኖቻችን ወደ ቀያቸው ተመልሰው ሰላማዊ ኑሮ መኖር ሲችሉ፣ የተራቡት ሲደገፉ፣ ፍትሕ ያጡት ፍትሕ ሲያገኙ ነው፡፡

ይህ ዓይነት መልካም ሥነ ምግባር በእያንዳንዱ የማኅበረ ሰብ አእምሮ ቦታ አግኝቶ ሲተገበር ትክክለኛውን ጾም ጾምን ማለት እንችላለን፣ ዲያብሎስም በእርግጠኝነት በዚህ ይሸነፋል፣ የሰው ጣዕመ ሕይወትም በዚህ ይለመልማል፣ ምድሪቱም በእግዚአብሔር በረከት ትሞላለች፡፡ ይህ ቅዱስ ተግባር በወርኃ ጾሙ በደንብ እንድንተገብረው ለመላው ኢትዮጵያውያን በተለይም ለኦርቶዶክሳዊው ማኅበረ ሰብ መንፈሳዊና አባታዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡ "

(ሙሉ መልዕክታቸው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#ዐቢይ_ጾም

ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነኢየሱስ ሊቀጳጳሳት ዘካቶሊካውያን የ2016 ዓ.ም የዓብይ ጾም መግቢያን በማስመልከት አስተላልፈዋል።

ከመልዕክታቸው የተወሰደ ፦

" ጌታችን ኢየሱስ ወደ ምድር የመጣው ወንጌሉን ይሰብክ ዘንድ የአባቱን ተልእኮ ሊፈጽም ነፍሳትን ለማዳን የጠፉትን ለመፈለግ ተልእኮ ሲሆን ዲያብሎስ ያቀረበለት ጥያቄ ፈታኝነቱ አምላክን ከማገልገልና እርሱን ከማምለክ ይልቅ ለእኔ ተገዛ አገልጋይ ሁን የሚል አንድምታ ያለው ነው፡፡

የጌታችን ኢየሱስ መልስ ግን ከሰይጣን ጋር መስማማትን ሳይሆን እግዚአብሔር አምላክን ማምለክ ለእርሱ ብቻ መስገድና ለእርሱ አገልጋይ መሆን እንደሚገባ አስረግጦ ይናገራል፡፡

ዛሬም የብዙዎቻችን ፈተና እግዚአብሔር አምላክ በሰጠን ስልጣን ባስቀመጠን የኃላፊነት ቦታ ላይ በፍቅር እናገለግላለን ? ሲሾም ያልሰራ ጡረታ ሲወጣ ይጸጸታል እንላለን ወይንስ ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል በሚል ዓይነት ስልጣናችንን አላገባብ እየተጠቀምን ነው ? ሌሎች በአገልግሎታችን ይደሰታሉ ? አምላክን ያመሰግናሉ ? ወይስ በእኛ የአገልግሎት አሰጣጥ ይማረራሉ ? ይህ የጾም ወቅት ራሳችንን የምናይበት እና የምንፈተንበት ጊዜ ነው፡፡

ኃላፊነት ከሰሩበት ካገለገሉበት በረከቱ ለሁላችንም ነው፤ ፈተናችን የሚሆነው መስራት በሚገባን ጊዜና ቦታ ለሕዝባችን ማገልገል ሲገባን ስልጣናችንን ለማሳየትና ሌላ ተጨማሪ ከፍያ ተጨማሪ ክብር ከፈለግን፣ በማገልገላችን ልንከበር ሲገባ ቦታው ላይ በመቀመጣችን ብቻ ክብር ካልተሰጠን የሚል ስሜት ከተሰማን፣ ፈተናውን ወደቅን ማለት ነው፡፡

ፈተና የምንወስደው ለማለፍ እንጂ ለመውደቅ አይደለም፤ በዚህ የጾም ወራት ፈተናችንን ለማለፍ ልንዘጋጅ ይገባል፡፡ እንዲሁ የሚደረግ ጾም የለምና ለጥያቄአችን መልስ እንድናገኝና እግዚአብሔርን በማዳመጥ ፈቃዱን ለማድረግ እንጹም፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ፈተናችንን አልፈን ፣ ንስሐ በመግባት ከእርሱና ከሰዎች ሁሉ ጋር ታርቀን ካለን ላይ ለወገኖቻችን አካፍለን እርሱ ወደፈለገው የፍቅርና የሰላም ኑሮ መኖር እንድንችል ጾምና ጸሎታችንን ይቀበልልን፡፡

ለትንሳኤው ብርሃን በሰላም ያድርሰን፡፡ "

(ሙሉ መልዕክታቸው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
የርገን ክሎፕ እና ፔፕ ጋርዲዮላ በፕሪሚየር ሊጉ የሚያደርጉት የመጨረሻ ፍልሚያ እንደሚሆን ይጠበቃል… ይህ ታሪካዊ ጨዋታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት በቀጥታ አያምልጥዎ።

🔥 በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሊቨርፑል እና ማንቸስተር ሲቲ ክምሽቱ 12፡45 የዋንጫ ግስጋሴያቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸውን ወሳኝ ፍልሚያ በሱፐርስፖርት ቻናሎች ይከታተሉ🔥

ይህ ታሪካዊ ፉክክር እንዳያመልጥዎ…

👉 ዛሬውኑ ፓኬጅዎን ያሳድጉ። ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ይከታተሉ!

የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://mydstv.onelink.me/vGln/eth2

#PremierLeagueOnDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET
#Ethiopia

በአማራ ክልል በተለይ በሰሜን ሸዋ እና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ትላንት በተጠናቀቀው የካቲት ወር በተፈፀሙ ጥቃቶች በርካቶች ተገድለዋል። ጉዳትም ደርሷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በወሩ ስለነበሩት ሁኔታዎች ከሚመለከታቸው አካላት ምላሽ ለማግኘት እጅግ በርካታ ቀናትን የወሰደ ሙከራ ቢያደርግም ምንም ምላሽ የሚሰጠ አካል አላገኘም።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ግን ስለነበሩት ሁኔታዎች እንደማያውቅ እና ክትትል ላይ እንደነበር በመግለፅ ያለውን ትንሽም ቢሆን አስተያየት ሰጥቶናል።

የተዘጋጀውን ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-03-10

@tikvahethiopia