TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.9K photos
1.52K videos
215 files
4.17K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#AddisAbaba

ከ2.5 ቢልየን ብር በላይ ወጪ የተገነባው ሀይሌ ግራንድ አዲስ ባለ 5 ኮከብ ሆቴል በይፋ ስራ ጀመረ።

በመዲናችን አዲስ አበባ በየካ ክፍለ ከተማ ላም በረት መናኽሪያ አካባቢ በ15 ሺህ ካ.ሜ ቦታ ላይ ያረፈውና ባለቤትነቱ የሻለቃ አትሌት ሀይሌ ገ/ስላሴ የሆነው የሀይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች ስምንተኛ መዳረሻ " ሀይሌ ግራንድ አዲስ አበባ " ሙሉ በሙሉ ስራ መጀመሩ ዛሬ ተገልጿል።

2.5 ቢልየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት "ሃይሌ ግራንድ አዲስ አበባ" እ.ኤ.አ ከጥቅምት 01/2022 ጀምሮ በሙከራ ደረጃ አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል።

ሆቴሉ ለ450 ሰራተኞች ቋሚ እና ጊዜያዊ የስራ እድል የፈጠረ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ለ120 #አዲስ_ተመራቂ ሰራተኞች ስልጠና በመስጠት ስራ እንዱጀምሩ መደረጉ ተገልጿል።

ሆቴሉ በውስጡ ፦

- 130 ክላሲክ ፤ 14 ስዊት ፤ 12 ፕሪሚየር እና 1 ፕሬዝዳንሻል ባጠቃላይ 175 አልጋዎችን የያዘ 157 ምቹና ሰፊ የመኝታ ክፍሎችን
- 4 ሬስቶራንቶች እና 2 PDR ፤
- 4 ባር፤
- 1pastery & coffe shop፤ 
- 1 የተሟላ የባህል ምግብ አዳራሽ፤
- 8 የስብሰባ አዳራሾች እና 2 ትላልቅ Ballrooms
- የጤና እና የውበት መጠበቂያ ማዕከል
- ጂም እንዲሁም 200 ተሽከርካሪዎችን የሚይዝ የመኪና ማቆሚያ ስፍራ ይዟል።

ሆቴሉ የተገነባው በኢትዮጵያውያን ሰራተኞች ብቻ መሆኑ የተነገረ ሲሆን በቀጣይ #ሐምሌ ወር ላይ #የወላይታ_ሶዶው ሆቴል እንደሚመረቅ፤ #የሻሸመኔው ሪዞርትም ጥገና ላይ እንዳለ ተገልጿል።

Tikvah Family (Addis Ababa)

@tikvahethiopia
ፎቶ፦ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ት ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካቸው ለስራ ጉብኝት #ሱዳን፤ ካርቱም ገብቷል።

የስራ ጉብኝቱ ለአንድ ቀን እንደሆነ ተገልጿል።   

የሱዳን ሪፐብሊክ የሽግግር ሉዓላዊነት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ጄኔራል አብደል ፈታሕ አል ቡርሃን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ልዑካቸው አቀባበል አድርገውላቸዋል።

Photo Credit : PMOEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት መቼ ይገለፃል ? በርካታ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች በሁለት ዙር ለመጀመሪያ ጊዜ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ የሚደረግበትን ቀን እየጠየቁ ይገኛሉ። በቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የመልዕክት መቀበያ አድራሻም እጅግ በርካታ መልዕክቶች ከውጤት ጋር ተያይዞ ከተማሪዎች እና በተማሪ ወላጆች ደርሶናል። የፈተናው ውጤት መዘግየቱን…
ከ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ጋር በተያያዘ ምን አዲስ ነገር አለ ?

እጅግ በጣም በርካታ ወላጆች እና ተማሪዎች " የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ጉዳይ ከምን ደረሰ ? ይፋ የሚደረግበት ቀን ታውቋል ወይ ? " የሚሉ ጥያቄዎችን ካለፈው ሰኞ / ጥር 15 ጀምሮ በቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መልዕክት መቀበያ @OfficialTikvahethiopiaBot ላይ እያስቀመጡ ይገኛሉ።

የተቀመጡት የወላጆች እና ተማሪዎች ጥያቄ ብዙ መሆናቸውን ተከትሎ እና ተማሪዎችም ያለመደበኛ ትምህርት እያሳለፉ ያሉት ቀናት እጨመረ በመሆኑ ከትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ለማግኘት ጥረት አድርገናል።

ባለፈው ሳምንት ላይ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር " የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መቼ ይፋ ይደረጋል ? " ብለን ጠይቀናቸው ፤ ከጥር 15 ጀምሮ ባሉት ቀናት የሚል ምላሽ ሰጥተውን ነበር።

ዛሬ ይህንኑ ጥያቄ በድጋሚ ለትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር አቅርበን ውጤት ይፋ ማድረጊያ ቀኑ  " ከነገ እንደማያልፍ " በዚገይ ደግሞ እስከ ቅዳሜ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመውናል።

ለመጀመሪያ ጊዜ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የተሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ930 ሺ በላይ ተማሪዎች መውሰዳቸው መገለፁ የሚዘነጋ አይደለም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ዛሬ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መክፈቻ ጸሎት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተከናውኗል። የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ምእመናን የሦስት ቀናት ጸሎት አውጇል። ምልዓተ ጉባኤው በነገው ዕለት ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ የሚሰበሰብ ሲሆን ከቀናት በፊት ቤተክርስቲያን ሕገ ወጥ ስትል በጠራችው ሹመት ዙሪያ ውሳኔ እንደሚያስተላልፍ ይጠበቃል። Photo Credit : EOTC …
#NewsAlert

ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ አሳለፈ።

ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሶዶ ዳጩ ወረዳ ሐሮ ባለወልድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ፦
1ኛ. አባ ሳዊሮስ
2ኛ. አባ ኤዎስጣቴዎስ
3ኛ. አባ ዜና ማርቆስ የቤተ ክርስቲያንን ቀኖና በመጣስ ባልተሰጣቸው ስልጣን 26 ኤጴስ ቆጰሳትን ሾመናል፤ ሲኖዶስ አቋቁመናል በማለት በማኅህበራዊ እና በብሮድካስት ሚዲያዎች በሰጡት መግለጫ የተረጋገጠ መሆኑን ገልጿል።

በዚሁ ድርጊታቸውም በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭው ዓለም የሚኖረውን ሕዝበ ክርስቲያንን በማታለል የክህደት እና የኑፋቄ ተግባር ፈፅመዋል ብሏል።

ቅዱስ ሲኖዶስ ይህንን ተግባር እንደሚያወግዝ ገልጾ ከቤተ ክርስቲያን የተሰጣቸውን ከዲቁና ጀምሮ ያለው ሙሉ ሥልጣነ ክህነት በመሻር አውግዞ እንደለያቸው አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ አሳለፈ። ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሶዶ ዳጩ ወረዳ ሐሮ ባለወልድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ፦ 1ኛ. አባ ሳዊሮስ 2ኛ. አባ ኤዎስጣቴዎስ 3ኛ. አባ ዜና ማርቆስ የቤተ ክርስቲያንን ቀኖና በመጣስ ባልተሰጣቸው ስልጣን 26 ኤጴስ ቆጰሳትን ሾመናል፤ ሲኖዶስ አቋቁመናል በማለት በማኅህበራዊ እና በብሮድካስት ሚዲያዎች…
#NewsAlert

1ኛ. አባ ሳዊሮስ
2ኛ. አባ ኤዎስጣቴዎስ
3ኛ. አባ ዜና ማርቆስ

ሥልጣነ ክህነታቸውና የማዕረግ ስማቸው በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ መነሳቱ ተገልጿል። ከዛሬ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በቀድሞ ዓለማዊ ስማቸው እንዲጠሩ መወሰኑን ቅዱስ ሲኖዶስ አሳውቋል።

በቤተ ክርስቲያኗ መንፈሳዊ አገልግሎት ዙርያም በሕይወትም ሆነ በሞት ማናቸውንም መንፈሳዊ አገልግሎት እንዳያገኙ ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ ከቤተ ክርስቲያን እንደለያቸው አሳውቋል።

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ አውግዞ በለያቸው ግለሰቦች ይመሯቸው በነበሩ አህጉረ ስብከት መንፈሳዊ አገልግሎት በማከናወን ሀገረ ስብከቱን የሚመሩ ብፁዐን አባቶችን፦
- ለደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት
- ለኬንያ፤ኡጋንዳ፤ታንዛኒያ እና ሩዋንዳ ሀገረ ስብከት
- ለኢሉ አባቦራ እና በኖ በደሌ ሀገረ ስብከት
- በሰሜን አሜሪካ ለሜኒሶታ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት
- ለጉጂ፤ምዕራብ ጉጂ እና ቦረና ሊበን ዞኖች ሀገረ ስብከት
- ለምስካዬ ኅዙናን መድኃኒዓለም ገዳም በአባትነት የሚመሩ አበው ሊቃነ ጳጳሳት እንዲመደቡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ወስኗል፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ " በስም ተጠቅሰው የተወገዙት ግለሰቦች በሠሩት የቀኖና ጥሰት ተጸጽተው ይቅርታን ቢጠይቁ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምህረት ደጆች ሁል ጊዜ ክፈት መሆናቸውና በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት የምንቀበላቸው " ይሆናል ብሏል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ከ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ጋር በተያያዘ ምን አዲስ ነገር አለ ? እጅግ በጣም በርካታ ወላጆች እና ተማሪዎች " የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ጉዳይ ከምን ደረሰ ? ይፋ የሚደረግበት ቀን ታውቋል ወይ ? " የሚሉ ጥያቄዎችን ካለፈው ሰኞ / ጥር 15 ጀምሮ በቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መልዕክት መቀበያ @OfficialTikvahethiopiaBot ላይ እያስቀመጡ ይገኛሉ። የተቀመጡት የወላጆች…
#Update

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤትን ተማሪዎች ከዛሬ ለሊት ጀምሮ ማየት እንደሚችሉ ተገልጿል።

ተፈታኞች ከዛሬ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም #ከሌሊቱ 5፡30 ጀምሮ ፡-

• በዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ወይም
• በ6284 አጭር የጽሑፍ መልዕክት መላኪያ ላይ የምዝግባ ቁጥራቸውን (Registration Number) ብቻ በመላክ ወይም
• በቴሌግራም ላይ https://yangx.top/eaesbot
ማየት የሚችሉ መሆኑን ተገልጿል።

ማሳሰቢያ፡-

• ማንኛውም ቅሬታ ያላቸው ተፈታኞች በአካል መምጣት ሳያስፈልግ እስከ ጥር 26/2015 ዓ.ም ድረስ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ላይ Compliant የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ማቅረብ ይችላሉ ተብሏል።

• ተማሪዎች ፤ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አድራሻ ላይ ብቻ እንዲጠቀሙ #ከተመሳሳይ እና #የተዛባ_መረጃ ለማሰራጫት ከሚሞክሩ አካላት እራሳቸውን እንዲጠብቁ መልዕክት ተላልፏል።

ምንጭ ፦ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ ተደረገ።

ተማሪዎች ውጤታቸውን ፦

• በዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ወይም
• በ6284 አጭር የጽሑፍ መልዕክት መላኪያ ላይ የምዝግባ ቁጥራቸውን (Registration Number) ብቻ በመላክ ወይም
• በቴሌግራም ላይ  https://yangx.top/eaesbot
ማየት ይችላሉ።

የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ውጤታቸውን የተመለከቱ ተማሪዎች ውጤት ይፋ መደረጉን አረጋግጠዋል።

ባለው #የኔትዎርክ_መጨናነቅ ምክንያት በርካታ ተማሪዎች ውጤታቸውን ለማየት እንደተቸገሩ እየገለፁ ሲሆን ተማሪዎች በትዕግስት አማራጭ የውጤት መመልከቻ ዘዴዎችን እንዲጠቀሙ ይመከራል።

More : @tikvahuniversity

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ ተደረገ። ተማሪዎች ውጤታቸውን ፦ • በዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ወይም • በ6284 አጭር የጽሑፍ መልዕክት መላኪያ ላይ የምዝግባ ቁጥራቸውን (Registration Number) ብቻ በመላክ ወይም • በቴሌግራም ላይ  https://yangx.top/eaesbot ማየት ይችላሉ። የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ውጤታቸውን የተመለከቱ ተማሪዎች ውጤት…
#ውጤት

የ12ኛ ክፍል የብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጎ ተማሪዎች እና የተማሪዎች ወላጆች ውጤት እየተመለከቱ ይገኛል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ እስካሁን ባደረገው ምልከታ እና ከቤተሰቡ አባላት የተላኩት የውጤት መግለጫ መልዕክቶች ከላይ ተያይዘዋል።

የዩኒቨርሲቲ መግቢያ መቁረጫ ነጥብ እስካሁን ያልተገለፀ ሲሆን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች የመቁረጫው ነጥብ ይፋ እንደተደረገ ተደርጎ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው።

More : @tikvahuniversity

@tikvahethiopia