#ATTENTION
የኦሮሚያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር እና ልማት ተነሺዎች ኮሚሽን በደቡብ ምሥራቅ ኦሮሚያ በ7 ዞኖች ድርቅ መከሰቱን አሳውቋል።
በድርቁ ከ800 ሺህ በላይ ሰዎች ተጎጂ መሆናቸውን ኮሚሽኑ ገልጿል።
የኦሮሚያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር እና ልማት ተነሺዎች ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሙስጠፋ ከድር ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል ፥ " በቦረና ፣ ምስራቅ ጉጂ እና ባሌ ውስጥ ድርቁ በከፍተኛ ሁኔታ ተስተውሏል። በምዕራብ ጉጂ ፣ ምዕራብ ባሌ እና በምዕራብ እና ምስራቅ ሀረርጌ በአጠቃላይ በደቡብ ምስራቅ ኦሮሚያ ድርቁ ተከስቷል ፤ ይህ የሆነው ባለፈው አመት የመኸር እና የክረምት ዝናብ ሳይዘብ በመቅረቱ ነው " ብለዋል።
ዝናብ ሳይዘንብ በመቅረቱ ሳር አለመብቀሉን፣ ምንጮችም መድረቃቸውን አቶ ሙስጠፋ ተናግረዋል።
በአጠቃላይ 800,244 ሰዎች እርዳታ ለመጠበቅ መገደዳቸውንም አክለው ገልፀዋል።
በድርቅ ሳቢያ በእስሳት ላይ ስለደረሰው ጉዳት በተመለከተ ፥ " በ7ቱ ዞኖች በድርቁ የተጎዱ እንስሳት ቁጥር ከ188 ሺህ በላይ ሆኗል። አብዛኛዎቹ በሰው ድጋፍ ነው ከመሬት የሚነሱት። ቦረና ውስጥ ከ6 ሚሊዮን በላይ የቁም እንስሳት እንዳለ ነው የሚታወቀው በእነዚህ ላይ ጉዳት እየደረሰ ነው " ብለዋል።
ኮሚሽነሩ መንግስት በድርቅ የተጎዱ ወገኖችን ለመደገፍ እና ለእንስሳት መኖ በማቅረብ ጉዳት ለመቀነስ እየሰራ ነው ብለው ፤ ነገር ግን በቂ አንዳልሆነ አስገንዝበዋል፤ መንግስታዊ የሆኑ እና መንግስታዊ ያልሆኑ እንዲሁም የግል ድርጅቶች፣ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ያሉ ሰዎች እንዲረባረቡ ጥሪ አቅርበዋል።
አቶ ሙስጠፋ ከድር እስካሁን በድርቁ የሰው ህይወት አለማለፉን ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
የኦሮሚያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር እና ልማት ተነሺዎች ኮሚሽን በደቡብ ምሥራቅ ኦሮሚያ በ7 ዞኖች ድርቅ መከሰቱን አሳውቋል።
በድርቁ ከ800 ሺህ በላይ ሰዎች ተጎጂ መሆናቸውን ኮሚሽኑ ገልጿል።
የኦሮሚያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር እና ልማት ተነሺዎች ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሙስጠፋ ከድር ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል ፥ " በቦረና ፣ ምስራቅ ጉጂ እና ባሌ ውስጥ ድርቁ በከፍተኛ ሁኔታ ተስተውሏል። በምዕራብ ጉጂ ፣ ምዕራብ ባሌ እና በምዕራብ እና ምስራቅ ሀረርጌ በአጠቃላይ በደቡብ ምስራቅ ኦሮሚያ ድርቁ ተከስቷል ፤ ይህ የሆነው ባለፈው አመት የመኸር እና የክረምት ዝናብ ሳይዘብ በመቅረቱ ነው " ብለዋል።
ዝናብ ሳይዘንብ በመቅረቱ ሳር አለመብቀሉን፣ ምንጮችም መድረቃቸውን አቶ ሙስጠፋ ተናግረዋል።
በአጠቃላይ 800,244 ሰዎች እርዳታ ለመጠበቅ መገደዳቸውንም አክለው ገልፀዋል።
በድርቅ ሳቢያ በእስሳት ላይ ስለደረሰው ጉዳት በተመለከተ ፥ " በ7ቱ ዞኖች በድርቁ የተጎዱ እንስሳት ቁጥር ከ188 ሺህ በላይ ሆኗል። አብዛኛዎቹ በሰው ድጋፍ ነው ከመሬት የሚነሱት። ቦረና ውስጥ ከ6 ሚሊዮን በላይ የቁም እንስሳት እንዳለ ነው የሚታወቀው በእነዚህ ላይ ጉዳት እየደረሰ ነው " ብለዋል።
ኮሚሽነሩ መንግስት በድርቅ የተጎዱ ወገኖችን ለመደገፍ እና ለእንስሳት መኖ በማቅረብ ጉዳት ለመቀነስ እየሰራ ነው ብለው ፤ ነገር ግን በቂ አንዳልሆነ አስገንዝበዋል፤ መንግስታዊ የሆኑ እና መንግስታዊ ያልሆኑ እንዲሁም የግል ድርጅቶች፣ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ያሉ ሰዎች እንዲረባረቡ ጥሪ አቅርበዋል።
አቶ ሙስጠፋ ከድር እስካሁን በድርቁ የሰው ህይወት አለማለፉን ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ... እንስሳት የሚበሉትን አጥተው አብዛኛዎቹ አልቀዋል፤ ከእንስሳትም አልፎ ለሰው ህይወትም እየሰጋን ነው " - አቶ ጎዳና ሎራ
#NakorMelkaVoA
በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን የድሬ ነዋሪ የሆኑት አቶ ጎዳና ሎራ ባለፈው ዓመት መዝነብ የነበረበት የመኸር እና ክረምት ዝናብ ባለመዝነቡ በሰዎች እና በእንስሳት ላይ ጉዳት መድረሱን ገልፀው ፤ ተጨማሪ ጉዳት ለመከላከል ርብርብ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።
አቶ ጎዳና ሎራ ፦
" ከዝናብ እጥረት የተነሳ ድርቅ አጋጥሞናል።
ክረትም የዘራነው ዘር ሳይበቅል ነው የቀረው። እንስሳትም የሚበሉትን አጥተው አብዛኛዎቹ አልቀዋል፤ ከእንስሳትም አልፎ ለሰው ህይወትም እየሰጋን ነው። ለምሳሌ እኔ 30 ከብቶችን አጥቻለው 80 የሚሆኑ ከብቶች ያለቁበትም አለ።
ባለንበት ቀበሌ በድርቅ ምክንያት ከ10 በላይ ሰዎች ታመው ሰውነታቸው አብጧል።
የቦረና የኑሮ መሰረት የከብት እርባታ ነው። ድርቁ እያሳደረሰው ካለው ጉዳት አንፃር በእዚህ የሚቀጥል ከሆነ የባሰ አደጋ ያጋጥመናል።
መንግስታዊ የሆኑና ያልሆኑም ድርጅቶች እንዲሁም ህዝቡ ድርቁ ሊያመጣ የሚችለውን አደጋ ለመቀነስ ሊረባረቡ ይገባል "
@tikvahethiopia
#NakorMelkaVoA
በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን የድሬ ነዋሪ የሆኑት አቶ ጎዳና ሎራ ባለፈው ዓመት መዝነብ የነበረበት የመኸር እና ክረምት ዝናብ ባለመዝነቡ በሰዎች እና በእንስሳት ላይ ጉዳት መድረሱን ገልፀው ፤ ተጨማሪ ጉዳት ለመከላከል ርብርብ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።
አቶ ጎዳና ሎራ ፦
" ከዝናብ እጥረት የተነሳ ድርቅ አጋጥሞናል።
ክረትም የዘራነው ዘር ሳይበቅል ነው የቀረው። እንስሳትም የሚበሉትን አጥተው አብዛኛዎቹ አልቀዋል፤ ከእንስሳትም አልፎ ለሰው ህይወትም እየሰጋን ነው። ለምሳሌ እኔ 30 ከብቶችን አጥቻለው 80 የሚሆኑ ከብቶች ያለቁበትም አለ።
ባለንበት ቀበሌ በድርቅ ምክንያት ከ10 በላይ ሰዎች ታመው ሰውነታቸው አብጧል።
የቦረና የኑሮ መሰረት የከብት እርባታ ነው። ድርቁ እያሳደረሰው ካለው ጉዳት አንፃር በእዚህ የሚቀጥል ከሆነ የባሰ አደጋ ያጋጥመናል።
መንግስታዊ የሆኑና ያልሆኑም ድርጅቶች እንዲሁም ህዝቡ ድርቁ ሊያመጣ የሚችለውን አደጋ ለመቀነስ ሊረባረቡ ይገባል "
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በፌዴሬሽን ምክር ቤት የተረጋገጠ የፌስቡክ ገፅ ላይ ተጋርቶ የነበረው መልዕክት አሁን ላይ ጠፍቷል። መልዕክቱ ለ1 ሰዓት ሳይጠፋ የቆየ ሲሆን የተሰጠ ማብራሪያ የለም። @tikvahethiopia
" ... ተለጥፎ የነበረው መልዕክት ከእውቅናዬ ውጭ ነው ፤ የምክር ቤቱንም አቋም አይወክልም " - ፌዴሬሽን ምክር ቤት
የፌዴሬሽን ምክር ቤት ከሰዓታት በፊት በተረጋገጠ የፌስቡክ ገፁ ላይ ስለተለጠፈው መልዕክት አጭር መልዕክት አስተላልፏል።
ምክር ቤቱ በገፁ ላይ ተለጥፎ የነበረው መልእክት ከምክር ቤቱ እውቅና ውጪ የተለጠፈ መሆኑን ገልጿል።
እንዲሁም መልዕክቱ የምክር ቤቱን አቋም እንደማይወክል አሳውቋል።
ም/ቤቱ በተረጋገጠ ገፁ ላይ መልዕክቱን ማን እንዳጋራውና እንዴት ሊጋራ እንደቻለ፣ ለዚህ ሚጠየቅ አካል ይኖር እንደሆነ የሰጠው ማብራሪያ የለም።
@tikvahethiopia
የፌዴሬሽን ምክር ቤት ከሰዓታት በፊት በተረጋገጠ የፌስቡክ ገፁ ላይ ስለተለጠፈው መልዕክት አጭር መልዕክት አስተላልፏል።
ምክር ቤቱ በገፁ ላይ ተለጥፎ የነበረው መልእክት ከምክር ቤቱ እውቅና ውጪ የተለጠፈ መሆኑን ገልጿል።
እንዲሁም መልዕክቱ የምክር ቤቱን አቋም እንደማይወክል አሳውቋል።
ም/ቤቱ በተረጋገጠ ገፁ ላይ መልዕክቱን ማን እንዳጋራውና እንዴት ሊጋራ እንደቻለ፣ ለዚህ ሚጠየቅ አካል ይኖር እንደሆነ የሰጠው ማብራሪያ የለም።
@tikvahethiopia
#DireDawaUniversity
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የአንደኛ ዓመት የሕክምና ሳይንስ ተማሪ የነበረው ታሪኩ ሶሪ ሐሙስ ጥር 19/2014 ዓ.ም እኩለ ቀን አካባቢ ራሱን ማጥፉቱን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
የተማሪውን ህልፈት ምክንያት ለማጣራት ከጸጥታ አካላት ጋር እየሰራ እንደሚገኝ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።
የተማሪው አስክሬን ወደ አዲስ አበባ ጳውሎስ ሆስፒታል ተልኮ ምርመራ እንደተደረገበት የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የዓለም ዐቀፍና ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ደቻሳ ጋንፉሬ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል።
ዩኒቨርሲቲው የምርመራው ውጤቱ እንደደረሰው ለመገናኛ ብዙሃን ይፋ እንደሚያደርግ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።
" ተማሪ ታሪኩ ታንቆ ራሱን እንዳጠፋ ነው የምናቀው " ያሉት ዳይሬክተሩ፤ "ከህልፈቱ ጋር እየተነሱ ያሉ ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ምርመራ እየተደረገ ነው" ብለዋል።
የተማሪው አስክሬን ትላንት ቤተሰቦቹ ወደሚገኙበት ወለጋ ዞን ሆሩ ጉዱሩ መላኩን ዳይሬክተሩ ለቲክቫህ ገልጸዋል።
More : @tikvahuniversity
@tikvahethiopia
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የአንደኛ ዓመት የሕክምና ሳይንስ ተማሪ የነበረው ታሪኩ ሶሪ ሐሙስ ጥር 19/2014 ዓ.ም እኩለ ቀን አካባቢ ራሱን ማጥፉቱን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
የተማሪውን ህልፈት ምክንያት ለማጣራት ከጸጥታ አካላት ጋር እየሰራ እንደሚገኝ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።
የተማሪው አስክሬን ወደ አዲስ አበባ ጳውሎስ ሆስፒታል ተልኮ ምርመራ እንደተደረገበት የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የዓለም ዐቀፍና ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ደቻሳ ጋንፉሬ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል።
ዩኒቨርሲቲው የምርመራው ውጤቱ እንደደረሰው ለመገናኛ ብዙሃን ይፋ እንደሚያደርግ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።
" ተማሪ ታሪኩ ታንቆ ራሱን እንዳጠፋ ነው የምናቀው " ያሉት ዳይሬክተሩ፤ "ከህልፈቱ ጋር እየተነሱ ያሉ ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ምርመራ እየተደረገ ነው" ብለዋል።
የተማሪው አስክሬን ትላንት ቤተሰቦቹ ወደሚገኙበት ወለጋ ዞን ሆሩ ጉዱሩ መላኩን ዳይሬክተሩ ለቲክቫህ ገልጸዋል።
More : @tikvahuniversity
@tikvahethiopia
#ትምህርት_ሚኒስቴር
" በሁሉም ክልሎች በችሎታቸው የተመረጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸው 50 ትምህርት ቤቶች ይገነባሉ " - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
ትምህርት ሚኒስቴር በሁሉም ክልሎች በችሎታቸው የተመረጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸው 50 ትምህርት ቤቶች እንደሚገነቡ አሳወቀ።
ትምህርት ቤቶቹ የ8ኛ ክፍል ፈተና የወሰዱና በችሎታቸው የተመረጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸው ናቸው ተብሏል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) በሁሉም ክልሎች በዓይነታቸው ልዩ የሆኑና የልህቀት ማዕከል የሚሆኑ 50 ትምህርት ቤቶች ይገነባሉ ብለዋል።
ት/ ቤቶቹ ቀጣይ የአገር መሪ የሚሆኑ ብቁና ተወዳዳሪ ተማሪዎች የሚፈልቁበት በችሎታቸው ብቻ የሚመረጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸው መሆናቸውን ተናግረዋል።
በትምህርት ቤቶቹ የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት መሠረት ባደረገና የትምህርት ሚኒስቴር በሚያወጣውን መመዘኛ የሚያሟሉ ተማሪዎች የሚማሩባቸው መሆናቸው ተገልጿል።
በሁሉም ክልሎች በሚገነቡት እነዚህ የልህቀት ማዕከላት ከሁሉም የአገሪቱ ክልሎች የሚመለመሉ ተማሪዎችን ተቀብለው የሚያስተምሩ ይሆናሉ።
ይህንን መረጃ ያጋራው የትምህርት ሚኒስቴር የማህበራዊ ትስስር ገፅ ሚኒስትሩ የትምህርት ቤቶቹ ግንባታ መቼ ተጀምሮ መቼ ለማጠናቀቅ እቅድ እንደተያዘ የተናገሩት ነገር ስለመኖሩ ያለው ነገር የለም።
@tikvahethiopia
" በሁሉም ክልሎች በችሎታቸው የተመረጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸው 50 ትምህርት ቤቶች ይገነባሉ " - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
ትምህርት ሚኒስቴር በሁሉም ክልሎች በችሎታቸው የተመረጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸው 50 ትምህርት ቤቶች እንደሚገነቡ አሳወቀ።
ትምህርት ቤቶቹ የ8ኛ ክፍል ፈተና የወሰዱና በችሎታቸው የተመረጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸው ናቸው ተብሏል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) በሁሉም ክልሎች በዓይነታቸው ልዩ የሆኑና የልህቀት ማዕከል የሚሆኑ 50 ትምህርት ቤቶች ይገነባሉ ብለዋል።
ት/ ቤቶቹ ቀጣይ የአገር መሪ የሚሆኑ ብቁና ተወዳዳሪ ተማሪዎች የሚፈልቁበት በችሎታቸው ብቻ የሚመረጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸው መሆናቸውን ተናግረዋል።
በትምህርት ቤቶቹ የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት መሠረት ባደረገና የትምህርት ሚኒስቴር በሚያወጣውን መመዘኛ የሚያሟሉ ተማሪዎች የሚማሩባቸው መሆናቸው ተገልጿል።
በሁሉም ክልሎች በሚገነቡት እነዚህ የልህቀት ማዕከላት ከሁሉም የአገሪቱ ክልሎች የሚመለመሉ ተማሪዎችን ተቀብለው የሚያስተምሩ ይሆናሉ።
ይህንን መረጃ ያጋራው የትምህርት ሚኒስቴር የማህበራዊ ትስስር ገፅ ሚኒስትሩ የትምህርት ቤቶቹ ግንባታ መቼ ተጀምሮ መቼ ለማጠናቀቅ እቅድ እንደተያዘ የተናገሩት ነገር ስለመኖሩ ያለው ነገር የለም።
@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ዶ/ር ደብረፅዮን በቢቢሲ ኒውስ ሀወር ላይ ቀርበው ምን አሉ ?
የህወሓት ሊቀመንበር የሆኑት ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ዛሬ ከቢቢሲ ኒውስ ሀወር ጋር በነበራቸው ቆይታ ከፌዴራል መንግስቱ ጋር በሌሎች አካላት አማካኝነት (ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ ) ንግግርና ውይይት መደረግ መጀመሩን ገልፀዋል።
በዚህም ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ተገኝተዋል ብለዋል።
ከፌዴራል መንግስት ጋር በሌሎች አካላት አማካኝነት (በUN ፣AU እና ኬንያ) የተጀመረው ውይይት ግጭቱ እንዲቆም ተስፋ የሚሰጥ ምልክት መሆኑን ነገር ግን የዲፕሎማሲ ውጤቱ በመጠበቅ ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ዶ/ር ደብረጽዮን አሁንም ለችግሮች ሰላማዊ መፍትሔዎችን እንፈልጋለን ሲሉ ተደምጠዋል።
ቢቢሲ ኒውስ ሀወር በዚህ ዘገባው ከፌዴራል መንግስት በኩል ሰዎችን አላነጋገረም።
ዶ/ር ደብረፅዮን ቃላቸውን የሰጡበት የቢቢሲ ኒውስ ሀወር ፕሮግራም: www.bbc.co.uk/sounds/play/w172xv5kpz8pyk8?s=09
ከሰሞኑን ጠ/ሚ ዶክተር ዐብይ አህመድ ከዳያስፖራዎች ጋር በነበራቸው ዝግ ውይይት የሀገሪቱን ጥቅም የሚያስቀድም ምክንያታዊ ድርድር ይካሄዳል ስለማለታቸው አንድ የዳይስፖራ ተወካይ መናገሩን ኤፒ ዘግቦ ነበር።
ይህንንም ተከትሎ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ፤ ይህ እንዳልተባለ፤ ህወሓት አሁንም በህግ ሽብርተኛ ድርጅት በመሆኑ ሽብርተኛ ከሆነ ድርጅት ጋር እንነጋገራለን የሚል አቋም የተገለፀበት አጋጣሚ እንደሌለ አሳውቀው ነበር።
አሁንም ትግራይ ክልልን ከአፋር እንዲሁም ከአማራ በሚያዋስኑ አካባቢዎች ባለው ግጭት ሰዎች እየተፈናቀሉ መሆኑ ሪፖርት እየተደረገ ነው። በተለይ በአፋር ክልል ከ200 ሺህ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸው በተመድ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕከተኛ ፅ/ቤት ሪፖርት ማደረጉ አይዘነጋም።
@tikvahethiopia
የህወሓት ሊቀመንበር የሆኑት ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ዛሬ ከቢቢሲ ኒውስ ሀወር ጋር በነበራቸው ቆይታ ከፌዴራል መንግስቱ ጋር በሌሎች አካላት አማካኝነት (ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ ) ንግግርና ውይይት መደረግ መጀመሩን ገልፀዋል።
በዚህም ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ተገኝተዋል ብለዋል።
ከፌዴራል መንግስት ጋር በሌሎች አካላት አማካኝነት (በUN ፣AU እና ኬንያ) የተጀመረው ውይይት ግጭቱ እንዲቆም ተስፋ የሚሰጥ ምልክት መሆኑን ነገር ግን የዲፕሎማሲ ውጤቱ በመጠበቅ ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ዶ/ር ደብረጽዮን አሁንም ለችግሮች ሰላማዊ መፍትሔዎችን እንፈልጋለን ሲሉ ተደምጠዋል።
ቢቢሲ ኒውስ ሀወር በዚህ ዘገባው ከፌዴራል መንግስት በኩል ሰዎችን አላነጋገረም።
ዶ/ር ደብረፅዮን ቃላቸውን የሰጡበት የቢቢሲ ኒውስ ሀወር ፕሮግራም: www.bbc.co.uk/sounds/play/w172xv5kpz8pyk8?s=09
ከሰሞኑን ጠ/ሚ ዶክተር ዐብይ አህመድ ከዳያስፖራዎች ጋር በነበራቸው ዝግ ውይይት የሀገሪቱን ጥቅም የሚያስቀድም ምክንያታዊ ድርድር ይካሄዳል ስለማለታቸው አንድ የዳይስፖራ ተወካይ መናገሩን ኤፒ ዘግቦ ነበር።
ይህንንም ተከትሎ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ፤ ይህ እንዳልተባለ፤ ህወሓት አሁንም በህግ ሽብርተኛ ድርጅት በመሆኑ ሽብርተኛ ከሆነ ድርጅት ጋር እንነጋገራለን የሚል አቋም የተገለፀበት አጋጣሚ እንደሌለ አሳውቀው ነበር።
አሁንም ትግራይ ክልልን ከአፋር እንዲሁም ከአማራ በሚያዋስኑ አካባቢዎች ባለው ግጭት ሰዎች እየተፈናቀሉ መሆኑ ሪፖርት እየተደረገ ነው። በተለይ በአፋር ክልል ከ200 ሺህ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸው በተመድ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕከተኛ ፅ/ቤት ሪፖርት ማደረጉ አይዘነጋም።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UAE የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዩኤኢ ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካን ቡድናቸው ለይፋዊ የስራ ጉብኝት በተባበሩት አረብ ኢምሬትስ፣ አቡ ዳቢ ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ጋር የጋራ በሆኑ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። ምንጭ፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት @tikvahethiopia
#UAE #ETHIOPIA
የኢትዮጵያ ጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ ጦር ምክትል አዛዥ ሼክ መሐመድ ቢን ዛይድ በኡቡ ዳቢ ውይይት አድርገው ነበር።
ውይይቱ በትብብር በጋራ ስለሚሰሯቸው ስራዎች እንዲሁም የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ማጠናከር ላይ ያተኮረ እንደነበር ዋም ዘግቧል።
መሪዎቹ በምሥራቅ አፍሪካ ሰላም ለማውረድ የሚደረገውን ጥረት ጨምሮ በቀጠናዊ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተወይይተዋል።
ዶክተር ዐቢይ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ሼክ መሐመድ ቢን ዛይድ ለኢትዮጵያ ህዝብ ሰላም፣ መረጋጋት እና አንድነትን ተመኝተዋል።
ልማትን ለማሳካት ፣ የህዝቦችን መልካም የወደፊት ተስፋ ለመገንባት የመረጋጋት ፣ የሰላም ፣ የአብሮ መኖር እና የመተሳሰብ ምሰሶዎች ላይ ጠንካራ መሰረት መገንባት እንደሚያስፈልግ ሀገራቸው ያላትን ጽኑ እምነት ገልፀዋል።
ሼክ መሐመድ ቢን ዛይድ ፤ የኢትዮጵያ መንግስት የ " ሁቲ አማፅያን " በሀገራቸው ላይ የፈፀሙትን ጥቃት በማውገዝ ላሳየው አቋምና ከዩኤኢ ጎን በመሆን አጋርነቱን በመግለፁ አመስግነዋል።
በሌላ በኩል እኤአ በየካቲት ወር በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ስኬትን እና መልካም እድልን ተመኝተዋል።
ዶ/ር ዐቢይ በበኩላቸው የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ላላት አቋም እና ለኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋት ስለምታደርገው ድጋፍ ምስጋናቸውንና አድናቆታቸውን ገልጸው ለተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ቀጣይ እድገትና ልማት ተመኝተዋል።
በተጨማሪም የተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ከሌሎች ሀገራት ጋር ያላት ግንኙነት በጥበብ እና ሚዛናዊ በሆነ ዲፕሎማሲ ላይ የተመሰረተ እና በተለያዩ የዓለም ሀገራት መረጋጋትንና በተለይ በቀውስ ወቅት ሰላምን ለማስፈን ጥረት እያደረገች ያለውን ግንኙነት እና የጋራ ችግሮችን ለመፍታት ከአገራት ጋር ያላትን ትብብር አድንቀዋል።
ዶ/ር ዐቢይ ፥ የተባበሩት አረብ ኤምሬት የጸጥታ እና የግዛት አንድነቷን ለማስጠበቅ በምትወስዳቸው እርምጃዎች ሁሉ ኢትዮጵያ አጋርነቷን እንደምትገልፅ አረጋገጠዋል።
የሽብር ጥቃቱ ለቀጣናው ሰላምና ደህንነት ከፍተኛ ስጋት የሚፈጥር፣ በቀጠናው ሚካሄደውን የሰላም ጥረት የሚያዳክም እና ሁሉንም ዓለም አቀፍ እና ሰብአዊ ደንቦችን እና ህጎችን የሚጥስ መሆኑንም ገልፀዋል።
ዛሬ ወደ ዩ.ኤ.ኢ ያቀናው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የመሩት የልዑካን ቡድን የመከላከያ ሚኒስትሩ ዶ/ር አብርሃም በላይ ፣ የብሔራዊ መረጃ እና ደሕንነት አገልግሎት መሥሪያ ቤት ዳይሬክተር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ፣ የሰለም ሚኒስትር ብናልፍ አንዱአለም ፣ የብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ፣ የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል የተካተቱበት ነው።
ይህን ዝርዝር መረጃ ያገኘውነው የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ መንግስት ከሚቆጣጣረው ከዋም ነው።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ ጦር ምክትል አዛዥ ሼክ መሐመድ ቢን ዛይድ በኡቡ ዳቢ ውይይት አድርገው ነበር።
ውይይቱ በትብብር በጋራ ስለሚሰሯቸው ስራዎች እንዲሁም የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ማጠናከር ላይ ያተኮረ እንደነበር ዋም ዘግቧል።
መሪዎቹ በምሥራቅ አፍሪካ ሰላም ለማውረድ የሚደረገውን ጥረት ጨምሮ በቀጠናዊ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተወይይተዋል።
ዶክተር ዐቢይ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ሼክ መሐመድ ቢን ዛይድ ለኢትዮጵያ ህዝብ ሰላም፣ መረጋጋት እና አንድነትን ተመኝተዋል።
ልማትን ለማሳካት ፣ የህዝቦችን መልካም የወደፊት ተስፋ ለመገንባት የመረጋጋት ፣ የሰላም ፣ የአብሮ መኖር እና የመተሳሰብ ምሰሶዎች ላይ ጠንካራ መሰረት መገንባት እንደሚያስፈልግ ሀገራቸው ያላትን ጽኑ እምነት ገልፀዋል።
ሼክ መሐመድ ቢን ዛይድ ፤ የኢትዮጵያ መንግስት የ " ሁቲ አማፅያን " በሀገራቸው ላይ የፈፀሙትን ጥቃት በማውገዝ ላሳየው አቋምና ከዩኤኢ ጎን በመሆን አጋርነቱን በመግለፁ አመስግነዋል።
በሌላ በኩል እኤአ በየካቲት ወር በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ስኬትን እና መልካም እድልን ተመኝተዋል።
ዶ/ር ዐቢይ በበኩላቸው የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ላላት አቋም እና ለኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋት ስለምታደርገው ድጋፍ ምስጋናቸውንና አድናቆታቸውን ገልጸው ለተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ቀጣይ እድገትና ልማት ተመኝተዋል።
በተጨማሪም የተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ከሌሎች ሀገራት ጋር ያላት ግንኙነት በጥበብ እና ሚዛናዊ በሆነ ዲፕሎማሲ ላይ የተመሰረተ እና በተለያዩ የዓለም ሀገራት መረጋጋትንና በተለይ በቀውስ ወቅት ሰላምን ለማስፈን ጥረት እያደረገች ያለውን ግንኙነት እና የጋራ ችግሮችን ለመፍታት ከአገራት ጋር ያላትን ትብብር አድንቀዋል።
ዶ/ር ዐቢይ ፥ የተባበሩት አረብ ኤምሬት የጸጥታ እና የግዛት አንድነቷን ለማስጠበቅ በምትወስዳቸው እርምጃዎች ሁሉ ኢትዮጵያ አጋርነቷን እንደምትገልፅ አረጋገጠዋል።
የሽብር ጥቃቱ ለቀጣናው ሰላምና ደህንነት ከፍተኛ ስጋት የሚፈጥር፣ በቀጠናው ሚካሄደውን የሰላም ጥረት የሚያዳክም እና ሁሉንም ዓለም አቀፍ እና ሰብአዊ ደንቦችን እና ህጎችን የሚጥስ መሆኑንም ገልፀዋል።
ዛሬ ወደ ዩ.ኤ.ኢ ያቀናው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የመሩት የልዑካን ቡድን የመከላከያ ሚኒስትሩ ዶ/ር አብርሃም በላይ ፣ የብሔራዊ መረጃ እና ደሕንነት አገልግሎት መሥሪያ ቤት ዳይሬክተር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ፣ የሰለም ሚኒስትር ብናልፍ አንዱአለም ፣ የብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ፣ የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል የተካተቱበት ነው።
ይህን ዝርዝር መረጃ ያገኘውነው የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ መንግስት ከሚቆጣጣረው ከዋም ነው።
@tikvahethiopia
ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን ጠርቷል ?
ወልድያ ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎቹ መልዕክት አስተላልፏል።
በሀገራችን በተከሰተ ሰላም እጦት ምክኒያት የዩኒቨርሲቲው የመማር ማስተማር ሂደት መቋረጡን አስታውሷል።
ነገር ግን በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ወልድያ ዩኒቨርሲቲ ለአዲስ ተማሪዎች ጥሪ እንዳስተላለፈ ተደርጎ እየተወራ እንደሚገኝ ገልጿል።
ዩኒቨርሲቲው እስከ አሁን ምንም አይነት የጥሪ ማስታወቂያ #እንዳላስተላለፈ አስገንዝቧል።
የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ይህን አውቀው አዲስ ማስታወቂያ ሲኖር #በተረጋገጡ የዩኒቨርሲቲው ማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ እንደሚያሳራጭ ወልድያ ዩኒቨርሲቲ ገልጿል።
@tikvahethiopia
ወልድያ ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎቹ መልዕክት አስተላልፏል።
በሀገራችን በተከሰተ ሰላም እጦት ምክኒያት የዩኒቨርሲቲው የመማር ማስተማር ሂደት መቋረጡን አስታውሷል።
ነገር ግን በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ወልድያ ዩኒቨርሲቲ ለአዲስ ተማሪዎች ጥሪ እንዳስተላለፈ ተደርጎ እየተወራ እንደሚገኝ ገልጿል።
ዩኒቨርሲቲው እስከ አሁን ምንም አይነት የጥሪ ማስታወቂያ #እንዳላስተላለፈ አስገንዝቧል።
የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ይህን አውቀው አዲስ ማስታወቂያ ሲኖር #በተረጋገጡ የዩኒቨርሲቲው ማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ እንደሚያሳራጭ ወልድያ ዩኒቨርሲቲ ገልጿል።
@tikvahethiopia
#ZHAddis
እጆላይ ያለው ካሜራ ጊዜ በሄደ ቁጥር የሚሰጠው ጥቅም ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ዝቅ እንደሚል ያቃሉ ከማይፈለግ እቃጋ ሳይመደብ አሁኑኑ እኛ ዘንድ ይዘው ይምጡ እንዳይቆጩ አርገን በጥሩ ዋጋ እንገዞታለን።
ይደውሉልን : 0911156257 ከታች ያለውንlink በመጫን የቴሌግራም አባል ይሁኑhttps://yangx.top/joinchat/AAAAAEUTeB3LSYVFukiuQw
ቦሌ ወሎሰፈር HMM ህንፃ 2ኛ ፍቅ205
እጆላይ ያለው ካሜራ ጊዜ በሄደ ቁጥር የሚሰጠው ጥቅም ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ዝቅ እንደሚል ያቃሉ ከማይፈለግ እቃጋ ሳይመደብ አሁኑኑ እኛ ዘንድ ይዘው ይምጡ እንዳይቆጩ አርገን በጥሩ ዋጋ እንገዞታለን።
ይደውሉልን : 0911156257 ከታች ያለውንlink በመጫን የቴሌግራም አባል ይሁኑhttps://yangx.top/joinchat/AAAAAEUTeB3LSYVFukiuQw
ቦሌ ወሎሰፈር HMM ህንፃ 2ኛ ፍቅ205
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ፎቶ : የኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ የማስታወሻ ሐውልት ዛሬ በሆሳዕና ከተማ ተመርቋል።
ሀውልቱ በሀዲያ ልማት ማህበር (ሀልማ) የተሰራ ሲሆን 17.5 ሜትር ቁመት ያለው ሲሆን በ5 መቶ 30 ካሬ ሜትር መሬት ላይ ያረፈ ነው።
በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ የኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ ቤተሰቦች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ከፍተኛ የክልልና የዞን ባለስጣናት ፣ የቀድሞ የአየር ኃይል ባልደረቦችና ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተው ነበር።
በሆሳዕና ከተማ የተገነባው የኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ ማስታወሻ ሀውልት ለሀገራቸው ላደረጉት ውለታና ለፈፀሙት ጀብድ ክብር የቆመ ነው።
Photo Credit : ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
ሀውልቱ በሀዲያ ልማት ማህበር (ሀልማ) የተሰራ ሲሆን 17.5 ሜትር ቁመት ያለው ሲሆን በ5 መቶ 30 ካሬ ሜትር መሬት ላይ ያረፈ ነው።
በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ የኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ ቤተሰቦች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ከፍተኛ የክልልና የዞን ባለስጣናት ፣ የቀድሞ የአየር ኃይል ባልደረቦችና ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተው ነበር።
በሆሳዕና ከተማ የተገነባው የኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ ማስታወሻ ሀውልት ለሀገራቸው ላደረጉት ውለታና ለፈፀሙት ጀብድ ክብር የቆመ ነው።
Photo Credit : ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ColonelBezabihPetros
ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ በኢትዮጲያ አየር ኃይል ታሪክ ውስጥ በብዙዎች ዘንድ የብሔራዊ ጀግና ተምሳሌት ተደርገው ይቆጠራሉ።
በተለይም በ1969 ዓ.ም በተካሄደው የኢትዮ ሶማሊያ ጦርነት /ሚግ 23 ጀት በማብረርና ሞቃዲሾ ድረስ በመዝለቅ / በሰይድ ባሬ ወታደራዊ ጦር ሰፈር ላይ ያደረሱት ተደጋጋሚ ጥቃት ዛሬም ድረስ ይነገርላቸዋል።
በ1977 ከኤርትራ ሻዕቢያ ኃይሎች ጋር በነበረ ውጊያ በናቅፋ ግንባር አውሮፕላኑ ተመቶ ወደቀ በኃላም በሻዕቢያ እጅ ገቡ ታስረውም ቆዩ በ1983 (ከ7 ዓመት በኃላ) ግን ከእስር ተፈቱ።
በኃላም ኢትዮጵያ እና ኤርትራ በባድመ ድንበር ውዝግብ ምክንያት ወደ ጦርነት በገቡበት ወቅት ኮሎኔሉ ለሀገር ክብር በድጋሚ ሻዕቢያን ለመደምሰስ ዘመቱ።
የኤርትራ አየር ኃይል የኢትዮጵያን አየር ጥሶ ትግራይ ግብቶ በአይደር ትምህርት ቤት ላይ ያደረሰውን ድብደባ ለመበቀል የኤርትራን የአየር ክልል ጥሰው ገቡ።
ግን ኮሎኔሉ ሲያበሩት የነበረው ጀት ተመቶ መውደቁን ተከትሎ / በምርኮ በኤርትራ ወታደሮች እጅ ከገቡ በኋላ / እስከዛሬ ከምናልባት በስተቀር ስለአሳቸው አውነተኛ መረጃዎችን ማግኘት አልተቻለም።
ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ ለሀገራቸው በኢትዮ ሶማሊ ጦርነት ሆነ ከሻዕቢያ ጋር በተደረገው ጦርነት የሰሯቸው የጀብድ ታሪኮች በርካታ እንደሆኑ ይነገርላቸዋል።
ይበልጥ በእሳቸው ዙሪያ የተፃፉ ፅሁፎችን መፅሀፍትን አግኝታችሁ ብታነቡ ለሀገራቸው ስለሰሯቸው ስራዎች ብዙ ታውቃላችሁ።
@tikvahethiopia
ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ በኢትዮጲያ አየር ኃይል ታሪክ ውስጥ በብዙዎች ዘንድ የብሔራዊ ጀግና ተምሳሌት ተደርገው ይቆጠራሉ።
በተለይም በ1969 ዓ.ም በተካሄደው የኢትዮ ሶማሊያ ጦርነት /ሚግ 23 ጀት በማብረርና ሞቃዲሾ ድረስ በመዝለቅ / በሰይድ ባሬ ወታደራዊ ጦር ሰፈር ላይ ያደረሱት ተደጋጋሚ ጥቃት ዛሬም ድረስ ይነገርላቸዋል።
በ1977 ከኤርትራ ሻዕቢያ ኃይሎች ጋር በነበረ ውጊያ በናቅፋ ግንባር አውሮፕላኑ ተመቶ ወደቀ በኃላም በሻዕቢያ እጅ ገቡ ታስረውም ቆዩ በ1983 (ከ7 ዓመት በኃላ) ግን ከእስር ተፈቱ።
በኃላም ኢትዮጵያ እና ኤርትራ በባድመ ድንበር ውዝግብ ምክንያት ወደ ጦርነት በገቡበት ወቅት ኮሎኔሉ ለሀገር ክብር በድጋሚ ሻዕቢያን ለመደምሰስ ዘመቱ።
የኤርትራ አየር ኃይል የኢትዮጵያን አየር ጥሶ ትግራይ ግብቶ በአይደር ትምህርት ቤት ላይ ያደረሰውን ድብደባ ለመበቀል የኤርትራን የአየር ክልል ጥሰው ገቡ።
ግን ኮሎኔሉ ሲያበሩት የነበረው ጀት ተመቶ መውደቁን ተከትሎ / በምርኮ በኤርትራ ወታደሮች እጅ ከገቡ በኋላ / እስከዛሬ ከምናልባት በስተቀር ስለአሳቸው አውነተኛ መረጃዎችን ማግኘት አልተቻለም።
ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ ለሀገራቸው በኢትዮ ሶማሊ ጦርነት ሆነ ከሻዕቢያ ጋር በተደረገው ጦርነት የሰሯቸው የጀብድ ታሪኮች በርካታ እንደሆኑ ይነገርላቸዋል።
ይበልጥ በእሳቸው ዙሪያ የተፃፉ ፅሁፎችን መፅሀፍትን አግኝታችሁ ብታነቡ ለሀገራቸው ስለሰሯቸው ስራዎች ብዙ ታውቃላችሁ።
@tikvahethiopia
#Save_the_Children
በኦሮሚያ፣ ደቡብ እና ሲዳማ ክልሎች የህፃናት አድን ድርጅት (Save the Children) በ136 ትምህርት ቤቶች ላይ የምገባ ፕሮግራም እየሰጠ መሆኑን ለኢትዮጵያ ትምህርት ቴሌቪዥን አሳውቋል።
ለ90 ሺህ ተማሪዎች በ136 ትምህርት ቤቶች ላይ በኦሮሚያ ፣ ደቡብ እና ሲዳማ ክልሎች በ4 ወረዳዎች GPE ከተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት በተገኘ ድጋፍ የምገባ ፕሮግራም ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን የኢትየጵያ ደቡባዊ አካባቢ ማናጀር የሆኑት ዶክተር ሀይሉ ተስፋዬ ገልፀዋል።
በዚህ የትምህርት ቤት የምገባ ፕሮግራም ምክንያት በርካታ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ማድረጉንና በተማሪዎች ትምህርት ውጤት እና የትምህርት ጥራት ላይ ከፍተኛ መሻሻል እንዲመጣ ማድርጉን ማናጀሩ ጨምረው ገልፀዋል።
ዶክተር ሀይሉ ተስፋዬ በቀጣይ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር Save the Children ዋነኛ አላማ ያደረገው የህፃናትን ትምህርትንና የምገባ ፕሮግራም የሚደረስና ጥራቱን የመጠበቅ ተግባር እንቀጥላለን ብለዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ስራው እንዲሳካ ለሚያደርገው ደግፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ትምህርት ቴሌቪዥን
@tikvahethiopia
በኦሮሚያ፣ ደቡብ እና ሲዳማ ክልሎች የህፃናት አድን ድርጅት (Save the Children) በ136 ትምህርት ቤቶች ላይ የምገባ ፕሮግራም እየሰጠ መሆኑን ለኢትዮጵያ ትምህርት ቴሌቪዥን አሳውቋል።
ለ90 ሺህ ተማሪዎች በ136 ትምህርት ቤቶች ላይ በኦሮሚያ ፣ ደቡብ እና ሲዳማ ክልሎች በ4 ወረዳዎች GPE ከተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት በተገኘ ድጋፍ የምገባ ፕሮግራም ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን የኢትየጵያ ደቡባዊ አካባቢ ማናጀር የሆኑት ዶክተር ሀይሉ ተስፋዬ ገልፀዋል።
በዚህ የትምህርት ቤት የምገባ ፕሮግራም ምክንያት በርካታ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ማድረጉንና በተማሪዎች ትምህርት ውጤት እና የትምህርት ጥራት ላይ ከፍተኛ መሻሻል እንዲመጣ ማድርጉን ማናጀሩ ጨምረው ገልፀዋል።
ዶክተር ሀይሉ ተስፋዬ በቀጣይ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር Save the Children ዋነኛ አላማ ያደረገው የህፃናትን ትምህርትንና የምገባ ፕሮግራም የሚደረስና ጥራቱን የመጠበቅ ተግባር እንቀጥላለን ብለዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ስራው እንዲሳካ ለሚያደርገው ደግፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ትምህርት ቴሌቪዥን
@tikvahethiopia
የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ማስጠንቀቂያ !
የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በተለያዩ የግንባታ ሳይቶች ከሚገኙ የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል ግንባታቸው ተጠናቆ ቁልፍ እንዲወሰዱ የተነገራቸው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕድለኞች ባለመምጣታቸው፣ በቀናት ውስጥ ቁልፍ እንዲወስዱ ማስጠንቀቂያ ሰጠ፡፡
ኮርፖሬሽኑ ቁልፍ ላልተወሰደባቸው ቤቶች የሚያደርገውን ጥበቃ እንደሚያነሳ አስታውቋል፡፡
የጋራ መኖሪያ ቤቶች በሚገኙባቸው ፕሮጀክት ሳይቶች በሙሉ የተለጠፈው የኮርፖሬሽኑ ማስጠንቀቂያ፣ የሕንፃና የቤት ቁልፍ ርክክብ ከተጀመረ ብዙ ወራት ቢቆጠሩም ነዋሪው ቤቱን ተረክቦ እያደሰና እየገባ አለመሆኑን ይገልፃል።
በዚህም ምክንያት የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቶች ለተለያዩ ችግሮች እየተዳረጉ በመሆናቸው፣ ነዋሪዎች ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እስከ የካቲት 15 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ መጥተው ቁልፍ እንዲረከቡ ያሳስባል፡፡
ያንብቡ : https://telegra.ph/Reporter-01-30
ምንጭ፦ ሪፖርተር
የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በተለያዩ የግንባታ ሳይቶች ከሚገኙ የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል ግንባታቸው ተጠናቆ ቁልፍ እንዲወሰዱ የተነገራቸው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕድለኞች ባለመምጣታቸው፣ በቀናት ውስጥ ቁልፍ እንዲወስዱ ማስጠንቀቂያ ሰጠ፡፡
ኮርፖሬሽኑ ቁልፍ ላልተወሰደባቸው ቤቶች የሚያደርገውን ጥበቃ እንደሚያነሳ አስታውቋል፡፡
የጋራ መኖሪያ ቤቶች በሚገኙባቸው ፕሮጀክት ሳይቶች በሙሉ የተለጠፈው የኮርፖሬሽኑ ማስጠንቀቂያ፣ የሕንፃና የቤት ቁልፍ ርክክብ ከተጀመረ ብዙ ወራት ቢቆጠሩም ነዋሪው ቤቱን ተረክቦ እያደሰና እየገባ አለመሆኑን ይገልፃል።
በዚህም ምክንያት የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቶች ለተለያዩ ችግሮች እየተዳረጉ በመሆናቸው፣ ነዋሪዎች ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እስከ የካቲት 15 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ መጥተው ቁልፍ እንዲረከቡ ያሳስባል፡፡
ያንብቡ : https://telegra.ph/Reporter-01-30
ምንጭ፦ ሪፖርተር
Telegraph
Reporter
#ADDISABABA የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በተለያዩ የግንባታ ሳይቶች ከሚገኙ የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል ግንባታቸው ተጠናቆ ቁልፍ እንዲወሰዱ የተነገራቸው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕድለኞች ባለመምጣታቸው፣ በቀናት ውስጥ ቁልፍ እንዲወስዱ ማስጠንቀቂያ ሰጠ፡፡ ኮርፖሬሽኑ ቁልፍ ላልተወሰደባቸው ቤቶች የሚያደርገውን ጥበቃ እንደሚያነሳ አስታውቋል፡፡ የጋራ መኖሪያ ቤቶች…