#Ethiopia
ከሁለት ዓመት በፊት በአውሮፕላን መከስከስ አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ ኢትዮጵያዊያን የመታሰቢያ ሐውልት ሊቆምላቸው ነው።
አደጋው የደረሰበት የግምቢቹ ወረዳ ቱሉፈራ እና በአጎራባች ቀበሌዎች ነዋሪዎች ተጠቃሚ የሚያደርጉ አራት ፕሮጀክቶች ሊተገበሩ መሆኑ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ፅሕፈት ቤት ዋና ጸሐፊ ዶ/ር አባ ተሾመ ፍቅሬ እንዳሉት ቦይንግ ኩባንያ ለተጎጂ ቤተሰቦች በሰጠው ድጋፍ መሰረት በኢትዮጵያ ጉዳት የደረሰባቸው 18 ሰዎች ቤተሰቦች አደጋው በደረሰበት ስፍራ ያሉ ነዋሪዎች ላደረጉት ሰብዊነት በስፍራው ሐውልት እንዲሰራ ይሁንታ ሰጥተዋል።
የሰውነት ተምሳሌት የሆኑ ነዋሪዎች በአደጋው ለተጎዱት ዜጎች ያደረጉት ክብር አድንቀው፤ አደጋ በደረሰበት ስፍራ ነዋሪዎች በአደጋው ያለፉ ሰዎች በመሆናቸው ብቻ ተጎጂዎች ያደረጉት ተግባር ከቦይንግ በተገኘ ገንዘብ ድጋፍ አምስት አይነት ፕሮጀክቶች እንዲተገበሩ ተወስኗል።
ፕሮጀክቶቹ በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ልማት ድርጅት አማካኝት ነው የሚተገበረው።
የፕሮጀክቶችን ክንውን የሚቆጣጠር ከኦሮሚያ ክልልና ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የተውጣጣ ኮሚቴ ተዋቅሯል።
በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ፈፃሚነት ስራዎች ተጀመሩ ሲሆን ፦
- ፕሮጀክቶች ሶስት ጥልቅ የውሃ ጉድጓዶች፣
- እያንዳንዳቸው 5 ብሎክ ህንፃዎች ያላቸው ሁለት የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች
- 1 ጤና ኬላ ግንባታና
- ሰባት ድልድዮች የፕሮጀክቱ አካል ናቸው ተብሏል።
ፕሮጀክቶቹ በግቢቹ ወረዳ 4 ቀበሌዎች የሚኖሩ 13,852 አባውራዎችን ተጠቃሚ ያደርጋሉ ተብሏል።
በቦይንግ ኩባንያ 106 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ መገኘቱን ገልጸው ፕሮጀክቶቹ በ1 ዓመት ከ6 ወር ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆኑ ይደረጋል ብለዋል። #ኢዜአ
@tikvahethiopia
ከሁለት ዓመት በፊት በአውሮፕላን መከስከስ አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ ኢትዮጵያዊያን የመታሰቢያ ሐውልት ሊቆምላቸው ነው።
አደጋው የደረሰበት የግምቢቹ ወረዳ ቱሉፈራ እና በአጎራባች ቀበሌዎች ነዋሪዎች ተጠቃሚ የሚያደርጉ አራት ፕሮጀክቶች ሊተገበሩ መሆኑ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ፅሕፈት ቤት ዋና ጸሐፊ ዶ/ር አባ ተሾመ ፍቅሬ እንዳሉት ቦይንግ ኩባንያ ለተጎጂ ቤተሰቦች በሰጠው ድጋፍ መሰረት በኢትዮጵያ ጉዳት የደረሰባቸው 18 ሰዎች ቤተሰቦች አደጋው በደረሰበት ስፍራ ያሉ ነዋሪዎች ላደረጉት ሰብዊነት በስፍራው ሐውልት እንዲሰራ ይሁንታ ሰጥተዋል።
የሰውነት ተምሳሌት የሆኑ ነዋሪዎች በአደጋው ለተጎዱት ዜጎች ያደረጉት ክብር አድንቀው፤ አደጋ በደረሰበት ስፍራ ነዋሪዎች በአደጋው ያለፉ ሰዎች በመሆናቸው ብቻ ተጎጂዎች ያደረጉት ተግባር ከቦይንግ በተገኘ ገንዘብ ድጋፍ አምስት አይነት ፕሮጀክቶች እንዲተገበሩ ተወስኗል።
ፕሮጀክቶቹ በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ልማት ድርጅት አማካኝት ነው የሚተገበረው።
የፕሮጀክቶችን ክንውን የሚቆጣጠር ከኦሮሚያ ክልልና ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የተውጣጣ ኮሚቴ ተዋቅሯል።
በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ፈፃሚነት ስራዎች ተጀመሩ ሲሆን ፦
- ፕሮጀክቶች ሶስት ጥልቅ የውሃ ጉድጓዶች፣
- እያንዳንዳቸው 5 ብሎክ ህንፃዎች ያላቸው ሁለት የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች
- 1 ጤና ኬላ ግንባታና
- ሰባት ድልድዮች የፕሮጀክቱ አካል ናቸው ተብሏል።
ፕሮጀክቶቹ በግቢቹ ወረዳ 4 ቀበሌዎች የሚኖሩ 13,852 አባውራዎችን ተጠቃሚ ያደርጋሉ ተብሏል።
በቦይንግ ኩባንያ 106 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ መገኘቱን ገልጸው ፕሮጀክቶቹ በ1 ዓመት ከ6 ወር ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆኑ ይደረጋል ብለዋል። #ኢዜአ
@tikvahethiopia
ሰሞነኛው የግብፅ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ጎረቤት ሀገራት ዙሪያ :
#Djibouti
• የግብፁ ፕሬዝደንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ ከጂቡቲ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት እስማኤል ኦማር ጌሌ ጋር ለመወያየት ዛሬ ማለዳ ወደ ጅቡቲ አቅንተዋል፡፡
- የፕሬዚዳንቱ የጅቡቲ ጉብኝት በዓይነቱ የመጀመሪያ ነው ተብሏል።
- የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በጋራ ትብብር እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚወያዩ ታውቋል። በተለይም በፀጥታ ፣ በወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የሁለቱን ሀገራት ትብብር ማጠናከር የውይይቱ ዓላማ መሆኑ ተጠቁሟል።
- የግብፅና የጅቡቲ መሪዎች የጋራ በሆኑ ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት እና ሀሳቦችን ለመለዋወጥም አቅደዋል፡፡
#Kenya
• ግብፅ እና ኬንያ በትናንትናው እለት ወታደራዊ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
- በናይሮቢ የተፈረመው ስምምነት ዓላማ የሁለቱን ሀገራት የጋራ ጥቅም ለማስጠበቅ የሚደረገው የሁለትዮሽ ትብብር አካል ነው።
- ግብፅ ከኬንያ ጋር ያደረገችው ወታደራዊ ስምምነት እ.ኤ.አ. በ2021 በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ ሀገራት ጋር ያደረገችው አራተኛ ስምምነት ነው፡፡
- ከኬንያ በተጨማሪ ከሱዳን ፣ ከኡጋንዳ እን ከብሩንዲ ጋር ግብፅ ወታደራዊ ስምምነት ፈርማለች፡፡
#Sudan
• ግብፅ እና ሱዳን በትናንትናው ዕለት ለ 6 ቀናት የሚቆይ ሁለገብ የጋራ ወታደራዊ ልምምድ በሱዳን ጀምረዋል፡፡
ኢትዮጵያ በሕዳሴው ግድብ ጉዳይ ከሁለቱ ሀገራት ጋር ውጥረት ውስጥ በምትገኝበት በዚህ ወቅት የሚካሔደው ይህ ልምምድ ፣ የናይል ጠባቂዎች (Nile Protectors/ናይል ፕሮቴክተርስ) የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡
#አልአይን
@tikvahethiopia
#Djibouti
• የግብፁ ፕሬዝደንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ ከጂቡቲ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት እስማኤል ኦማር ጌሌ ጋር ለመወያየት ዛሬ ማለዳ ወደ ጅቡቲ አቅንተዋል፡፡
- የፕሬዚዳንቱ የጅቡቲ ጉብኝት በዓይነቱ የመጀመሪያ ነው ተብሏል።
- የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በጋራ ትብብር እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚወያዩ ታውቋል። በተለይም በፀጥታ ፣ በወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የሁለቱን ሀገራት ትብብር ማጠናከር የውይይቱ ዓላማ መሆኑ ተጠቁሟል።
- የግብፅና የጅቡቲ መሪዎች የጋራ በሆኑ ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት እና ሀሳቦችን ለመለዋወጥም አቅደዋል፡፡
#Kenya
• ግብፅ እና ኬንያ በትናንትናው እለት ወታደራዊ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
- በናይሮቢ የተፈረመው ስምምነት ዓላማ የሁለቱን ሀገራት የጋራ ጥቅም ለማስጠበቅ የሚደረገው የሁለትዮሽ ትብብር አካል ነው።
- ግብፅ ከኬንያ ጋር ያደረገችው ወታደራዊ ስምምነት እ.ኤ.አ. በ2021 በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ ሀገራት ጋር ያደረገችው አራተኛ ስምምነት ነው፡፡
- ከኬንያ በተጨማሪ ከሱዳን ፣ ከኡጋንዳ እን ከብሩንዲ ጋር ግብፅ ወታደራዊ ስምምነት ፈርማለች፡፡
#Sudan
• ግብፅ እና ሱዳን በትናንትናው ዕለት ለ 6 ቀናት የሚቆይ ሁለገብ የጋራ ወታደራዊ ልምምድ በሱዳን ጀምረዋል፡፡
ኢትዮጵያ በሕዳሴው ግድብ ጉዳይ ከሁለቱ ሀገራት ጋር ውጥረት ውስጥ በምትገኝበት በዚህ ወቅት የሚካሔደው ይህ ልምምድ ፣ የናይል ጠባቂዎች (Nile Protectors/ናይል ፕሮቴክተርስ) የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡
#አልአይን
@tikvahethiopia
#PP
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ስብሰባ መጀመሩን ገለፁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ሚዲያ ገፃቸው፥ "አያሌ ወሳኝ ጉዳዮች ላይ አተኩሮ የሚከናወነው የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴያችን ስብሰባ ዛሬ ተጀምሯል" ብለዋል።
@tikvahethiopia
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ስብሰባ መጀመሩን ገለፁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ሚዲያ ገፃቸው፥ "አያሌ ወሳኝ ጉዳዮች ላይ አተኩሮ የሚከናወነው የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴያችን ስብሰባ ዛሬ ተጀምሯል" ብለዋል።
@tikvahethiopia
4G LTE በማዕከላዊ ምሥራቅ ሪጅን ጀመረ።
ኢትዮ-ቴሌኮም ማዕከላዊ ምሥራቅ ሪጅን ለ227 ሺህ ደንበኞችን አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን 4G LTE Advanced ፈጣን ኢንተርኔት አገልግሎት ማስጀመሩን ኢፕድ ዘግቧል።
በማዕከላዊ ምሥራቅ ሪጅን ፦
- ሐረር፣
- አወዳይ
- ሀሮማያ ከተሞች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡
የተጀመረው የኢንተርኔት አገልግሎት በሪጅኑ የነበረውን የኢንተርኔት አገልግሎት ፍጥነት በ14 እጥፍ እንደሚያሻሽለው ተገልጻል።
@tikvahethiopia
ኢትዮ-ቴሌኮም ማዕከላዊ ምሥራቅ ሪጅን ለ227 ሺህ ደንበኞችን አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን 4G LTE Advanced ፈጣን ኢንተርኔት አገልግሎት ማስጀመሩን ኢፕድ ዘግቧል።
በማዕከላዊ ምሥራቅ ሪጅን ፦
- ሐረር፣
- አወዳይ
- ሀሮማያ ከተሞች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡
የተጀመረው የኢንተርኔት አገልግሎት በሪጅኑ የነበረውን የኢንተርኔት አገልግሎት ፍጥነት በ14 እጥፍ እንደሚያሻሽለው ተገልጻል።
@tikvahethiopia
#ሞጣ
ዛሬ "ሕብር እና ፍቅር ከሰባቱ ዋርካ ስር" በሚል መሪ ቃል በሞጣ ከተማ አስተዳደር እና በሁለት እጁ እነሴ ወረዳ አዘጋጅነት የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የመተሳሰብ፣ የአብሮነት፣ የአንድነት እና የወንድማማችነት መርሃ ግብር በሞጣ ሁለገብ ስታዲየም እየተካሄድ ነው።
ከ2 ቀናት በፊት "በፍቅር እንኖራለን፤ በአንድነት እንሻገራለን” በሚል መሪ ቃል የሞጣ ከተማ ነዋሪዎች የይቅርታ መድረክ አካሂደዋል።
መረጃው የሞጣ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።
@tikvahethiopia
ዛሬ "ሕብር እና ፍቅር ከሰባቱ ዋርካ ስር" በሚል መሪ ቃል በሞጣ ከተማ አስተዳደር እና በሁለት እጁ እነሴ ወረዳ አዘጋጅነት የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የመተሳሰብ፣ የአብሮነት፣ የአንድነት እና የወንድማማችነት መርሃ ግብር በሞጣ ሁለገብ ስታዲየም እየተካሄድ ነው።
ከ2 ቀናት በፊት "በፍቅር እንኖራለን፤ በአንድነት እንሻገራለን” በሚል መሪ ቃል የሞጣ ከተማ ነዋሪዎች የይቅርታ መድረክ አካሂደዋል።
መረጃው የሞጣ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።
@tikvahethiopia
እየተፈጠረ_ያለ_ችግር_ጋዜጣዊ_መግለጫ_18_09_13.pdf
964 KB
#እናት_ፓርቲ
እናት ፓርቲ በላከልን መግለጫ ፓርቲው በተለያዩ ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ስር በሚገኙ ምርጫ ክልሎች በምርጫ ሂደት ፣ በዕጩዎች እና አባሎቹ ላይ እየደረሱ ነው ያላቸውን ችግሮች በዝርዝር አስረድቷል።
ደርሰዋል የተባሉት ችግሮች ፦
- ማስፈራርት፣
- በሽጉጥ የመግደል ሙከራ ማድረግ፣
- እስር ፣
- ዕጩዎች ላይ ክትትል የማድረግ ትእዛዝ መስጠት፣
- ባነር እና ማስታወቂያዎች መገንጠል፣
- በገጠር ቀበሌ ህዝብን እየሰበሰቡ የፓርቲው ስም እንዲጠፋ የማድረግ፣
- ስድብ እና ሌሎችም በርካታ ጉዳዮች ናቸው።
ከእናት ፓርቲ የተላከልን መግለጫ እንደሚያስረዳው ፓርቲው አጋጠመኝ ያላቸው ችግሮች በአማራ ፣ በደቡብ ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ኦሮሚያ፣ ሐረር ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች ነው።
* ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ በPDF ተያይዟል።
@tikvahethiopia
እናት ፓርቲ በላከልን መግለጫ ፓርቲው በተለያዩ ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ስር በሚገኙ ምርጫ ክልሎች በምርጫ ሂደት ፣ በዕጩዎች እና አባሎቹ ላይ እየደረሱ ነው ያላቸውን ችግሮች በዝርዝር አስረድቷል።
ደርሰዋል የተባሉት ችግሮች ፦
- ማስፈራርት፣
- በሽጉጥ የመግደል ሙከራ ማድረግ፣
- እስር ፣
- ዕጩዎች ላይ ክትትል የማድረግ ትእዛዝ መስጠት፣
- ባነር እና ማስታወቂያዎች መገንጠል፣
- በገጠር ቀበሌ ህዝብን እየሰበሰቡ የፓርቲው ስም እንዲጠፋ የማድረግ፣
- ስድብ እና ሌሎችም በርካታ ጉዳዮች ናቸው።
ከእናት ፓርቲ የተላከልን መግለጫ እንደሚያስረዳው ፓርቲው አጋጠመኝ ያላቸው ችግሮች በአማራ ፣ በደቡብ ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ኦሮሚያ፣ ሐረር ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች ነው።
* ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ በPDF ተያይዟል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Shire የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ወታደሮች ሰኞ ምሽት በትግራይ ሽረ ከተማ ተፈናቃዮች ከሚገኙበት አራት ካምፖች ከ500 በላይ ወጣት ወንዶችና ሴቶች በግዳጅ ይዘው መወሰዳቸውን 3 የእርዳታ ሰራተኞች እና አንድ ዶ/ር እንደነገሩት ሮይተርስ አስነብቧል። የእርዳታ ሰራተኞቹና ዶክተሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መኪናዎች ላይ ተጭነው ተወስደዋል ሲሉ ፤ የአይን እማኞችን ዋቢ በማድረግ ተናግረዋል። ከእርዳታ…
"...የሲቪል ሰዎችን ደህንነትና ሰላም አደጋ ላይ የሚጥሉ ማናቸውንም አይነት ተግባራትን ያወግዛል" - ኢሰመኮ
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከግንቦት 16/2013 ጀምሮ በትግራይ ሽረ ከተማ ከሚገኙ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሚገኙባቸው የመጠለያ ካምፖች ውስጥ በፀጥታ ኃይሎች የተወሰዱ በርካታ ተፈናቃዮች ስላሉበት ሁኔታ ክትትል እያደረገ መሆኑ አሳውቋል።
መጠለያዎች መደበኛ መኖሪያ ቦታቸው ያለውን የደህንነት ስጋት ሸሽተው የመጡ ሰዎች ብቸኛ የደህንነት ቦታዎች ሲሆኑ ፤ የሰብዓዊ አቅርቦት ፍላጎቱ አሁንም ከፍተኛ መሆኑ ይታወቃል ብሏል።
ኢሰመኮ በመጠለያዎቹ የሚወሰዱ ማናቸውም ህግ ማስከበር እርምጃዎችም ሆነ በመጠለያዎቹ ይገኛሉ ተብለው የሚታሰቡ ተጠርጣሪዎችን የመያዝ እርምጃ ተገቢውን የህግ ሂደት የተከተለ እና በመጠለያዎቹ ያሉ ተፈናቃዮችን ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ መሆን እንዳለበት አስገንዝቧል።
ኮሚሽኑ የሲቪል ሰዎችን ደህንነት እና ሰላም አደጋ ላይ የሚጥሉ ማናቸውም አይነት ተግባራት የሚያወግዝ መሆኑን በመግለፅ አፋጣኝ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ በአፅንኦት አሳስቧል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከግንቦት 16/2013 ጀምሮ በትግራይ ሽረ ከተማ ከሚገኙ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሚገኙባቸው የመጠለያ ካምፖች ውስጥ በፀጥታ ኃይሎች የተወሰዱ በርካታ ተፈናቃዮች ስላሉበት ሁኔታ ክትትል እያደረገ መሆኑ አሳውቋል።
መጠለያዎች መደበኛ መኖሪያ ቦታቸው ያለውን የደህንነት ስጋት ሸሽተው የመጡ ሰዎች ብቸኛ የደህንነት ቦታዎች ሲሆኑ ፤ የሰብዓዊ አቅርቦት ፍላጎቱ አሁንም ከፍተኛ መሆኑ ይታወቃል ብሏል።
ኢሰመኮ በመጠለያዎቹ የሚወሰዱ ማናቸውም ህግ ማስከበር እርምጃዎችም ሆነ በመጠለያዎቹ ይገኛሉ ተብለው የሚታሰቡ ተጠርጣሪዎችን የመያዝ እርምጃ ተገቢውን የህግ ሂደት የተከተለ እና በመጠለያዎቹ ያሉ ተፈናቃዮችን ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ መሆን እንዳለበት አስገንዝቧል።
ኮሚሽኑ የሲቪል ሰዎችን ደህንነት እና ሰላም አደጋ ላይ የሚጥሉ ማናቸውም አይነት ተግባራት የሚያወግዝ መሆኑን በመግለፅ አፋጣኝ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ በአፅንኦት አሳስቧል።
@tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ሴናተር ጂም ኢንሆፍ ለአሜሪካ ሴኔት ምንድነው ያሉት ?
- ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀን ድርጅት (ሕወሃት)ን ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ተመሳሳይ ደረጃ ላይ ማስቀመጥ ተገቢ አይደለም ብለዋል።
- የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በትግራይ የሰብአዊ ድጋፍ እንዳይደርስ ጫና ያደረጉና የሰብአዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ አካላት ለፍርድ እንደሚያቀርቡ መናገራቸውን ገልጸዋል፡፡
- እአአ ከ2005 ጀምሮ በተለያዩ 19 ጊዜያት ኢትዮጵያ እንደጎበኙና ኢትዮጵያን በደንብ እንደሚያውቋት ገልፀዋል ፤ ኢትዮጵያ ነፃነቷን አስከብራ የቆየች አገር ናት ብለዋል፡፡
- የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በአገሪቱ ሰላም እንዲሰፍን ፣ የህዝቦች አንድነት እንዲጠናከርና ዴሞክራሲ እንዲሰፍን ቁርጠኝነት ያላቸው ሲሉ ተደምጠዋል።
- ጠ/ሚኒስትሩ በአገሪቱ ሪፎርም በማድረግ የፖለቲካ እስረኞች ና ጋዜጠኞች ከእስር እንዲፈቱ አድርገዋል ፤ እንዲሁም ከኤርትራ ጋር ስምምነት በማድረግ የማይቻል ሲመስለን የነበረውን ነገር እንደሚቻል አሳይተዋል ብለዋል።
- ጠ/ሚኒስትሩ በተወሰኑ ክልሎች ላይ ብቻ ትኩረት ሳያደርጉ አገርን በአንድነት ለመምራት ጥረት በሚያደርጉበት ወቅት ለዓመታት የኢትዮጵያ ፖለቲካ በበላይነት ሲዘውር የነበረው በሽብርተኛነት የተፈረጀ "ህወሓት" የበላይነቱን ላለማጣት ስለሚፈልግ ደስተኛ አልነበረም ብለዋል።
- ከኤርትራ ጋር በተደረገው የሰላም ድርድር ላይ "ህወሓት" ደስተኛ አልነበረም ፥ በአገሪቱ ሪፎርም ውስጥ ለመሳተፍ ፍቃደኛ አልነበረም ብለዋል፡፡
- አሜሪካ በኢትዮጰያ ያለውን ሁኔታ በመረዳት በአገሪቱ ውስጥ ሰላም እንዲኖር መርዳት እንጂ፣ ማዕቀብ መጣል ተገቢ እንዳልሆነ ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
- ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀን ድርጅት (ሕወሃት)ን ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ተመሳሳይ ደረጃ ላይ ማስቀመጥ ተገቢ አይደለም ብለዋል።
- የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በትግራይ የሰብአዊ ድጋፍ እንዳይደርስ ጫና ያደረጉና የሰብአዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ አካላት ለፍርድ እንደሚያቀርቡ መናገራቸውን ገልጸዋል፡፡
- እአአ ከ2005 ጀምሮ በተለያዩ 19 ጊዜያት ኢትዮጵያ እንደጎበኙና ኢትዮጵያን በደንብ እንደሚያውቋት ገልፀዋል ፤ ኢትዮጵያ ነፃነቷን አስከብራ የቆየች አገር ናት ብለዋል፡፡
- የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በአገሪቱ ሰላም እንዲሰፍን ፣ የህዝቦች አንድነት እንዲጠናከርና ዴሞክራሲ እንዲሰፍን ቁርጠኝነት ያላቸው ሲሉ ተደምጠዋል።
- ጠ/ሚኒስትሩ በአገሪቱ ሪፎርም በማድረግ የፖለቲካ እስረኞች ና ጋዜጠኞች ከእስር እንዲፈቱ አድርገዋል ፤ እንዲሁም ከኤርትራ ጋር ስምምነት በማድረግ የማይቻል ሲመስለን የነበረውን ነገር እንደሚቻል አሳይተዋል ብለዋል።
- ጠ/ሚኒስትሩ በተወሰኑ ክልሎች ላይ ብቻ ትኩረት ሳያደርጉ አገርን በአንድነት ለመምራት ጥረት በሚያደርጉበት ወቅት ለዓመታት የኢትዮጵያ ፖለቲካ በበላይነት ሲዘውር የነበረው በሽብርተኛነት የተፈረጀ "ህወሓት" የበላይነቱን ላለማጣት ስለሚፈልግ ደስተኛ አልነበረም ብለዋል።
- ከኤርትራ ጋር በተደረገው የሰላም ድርድር ላይ "ህወሓት" ደስተኛ አልነበረም ፥ በአገሪቱ ሪፎርም ውስጥ ለመሳተፍ ፍቃደኛ አልነበረም ብለዋል፡፡
- አሜሪካ በኢትዮጰያ ያለውን ሁኔታ በመረዳት በአገሪቱ ውስጥ ሰላም እንዲኖር መርዳት እንጂ፣ ማዕቀብ መጣል ተገቢ እንዳልሆነ ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
2021.04.19_MUSE_REPORT.pdf
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#EmmanuelMacron
የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ሩዋንዳ ይገኛሉ።
በ1994 ሩዋንዳ ውስጥ በነበረው አስከፊ የ "ዘር ጭፍጨፋ" ወቅት ፈረንሳይ 'ኃላፊነቷን' መወጣት አለመቻሏን/በጭፍጨፋው የነበራትን ሚና በይፋ እዉቅና ሰጥተዋል።
ፕሬዜዳንቱ እውቅናውን የሰጡት በኪጋሊ የዘር ማጥፋት መታሰቢያ ባደረጉት ንግግር ነው።
በወቅቱ የዘር ማጥፋት አገዛዝን ከመደገፍ አንስቶ ከጭፍጨፋው ጋር በተገናኘ የቅድመ ማስጠንቀቂያ መልዕክቶችን ፈረንሳይ ችላ ብላ ነበር ብለዋል።
ፕሬዜዳትቱ ባደረጉት ንግግር ላይ ግልፅ እና ይፋዊ ይቅርታ አልጠየቁም።
ማክሮን ባሰሙት ንግግር ፥ ፈረንሳይ የዘር ጭፍጨፋው ተባባሪ አይደለችም ያሉ ሲሆን በወቅቱ ሀገሪቱ ለነበራት ኃላፊነት ፈረንሳይን ይቅር ሊሉ የሚችሉት ከአስከፊው ጭፍጨፋ የተረፉት ሩዋንዳውያን ናቸዉ ብለዋል።
የሩዋንዳው ፕሬዜዳንት ፖል ካጋሜ ፤ የማክሮን ቃላቶች ከይቅርታም የበለጠ ዋጋ ያላቸው ነበሩ ሲሉ ገልፀዋል።
ከአንድ ወር በፊት በሩዋንዳ በ100 ቀን ውስጥ ብቻ 800 ሺ ገደማ ቱትሲዎች በተጨፈጨፉበት የ1994ቱ የሩዋንዳ ጭፍጨፋ ፈረንሳይ የተባባሪነት ሚና እንደነበራት የሚያመለክት የምርመራ ሪፖርት ይፋ ሆኖ እንደነበር አይዘነጋም።
@tikvahethiopia
የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ሩዋንዳ ይገኛሉ።
በ1994 ሩዋንዳ ውስጥ በነበረው አስከፊ የ "ዘር ጭፍጨፋ" ወቅት ፈረንሳይ 'ኃላፊነቷን' መወጣት አለመቻሏን/በጭፍጨፋው የነበራትን ሚና በይፋ እዉቅና ሰጥተዋል።
ፕሬዜዳንቱ እውቅናውን የሰጡት በኪጋሊ የዘር ማጥፋት መታሰቢያ ባደረጉት ንግግር ነው።
በወቅቱ የዘር ማጥፋት አገዛዝን ከመደገፍ አንስቶ ከጭፍጨፋው ጋር በተገናኘ የቅድመ ማስጠንቀቂያ መልዕክቶችን ፈረንሳይ ችላ ብላ ነበር ብለዋል።
ፕሬዜዳትቱ ባደረጉት ንግግር ላይ ግልፅ እና ይፋዊ ይቅርታ አልጠየቁም።
ማክሮን ባሰሙት ንግግር ፥ ፈረንሳይ የዘር ጭፍጨፋው ተባባሪ አይደለችም ያሉ ሲሆን በወቅቱ ሀገሪቱ ለነበራት ኃላፊነት ፈረንሳይን ይቅር ሊሉ የሚችሉት ከአስከፊው ጭፍጨፋ የተረፉት ሩዋንዳውያን ናቸዉ ብለዋል።
የሩዋንዳው ፕሬዜዳንት ፖል ካጋሜ ፤ የማክሮን ቃላቶች ከይቅርታም የበለጠ ዋጋ ያላቸው ነበሩ ሲሉ ገልፀዋል።
ከአንድ ወር በፊት በሩዋንዳ በ100 ቀን ውስጥ ብቻ 800 ሺ ገደማ ቱትሲዎች በተጨፈጨፉበት የ1994ቱ የሩዋንዳ ጭፍጨፋ ፈረንሳይ የተባባሪነት ሚና እንደነበራት የሚያመለክት የምርመራ ሪፖርት ይፋ ሆኖ እንደነበር አይዘነጋም።
@tikvahethiopia
ወ/ሮ ኬሪያ ምስክርነታቸው ተነስቶ ፍርድ ቤት ቀረቡ።
ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም የምስክርነት ጥበቃቸው ተነስቶ ዳግም ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ገለጸ።
ወ/ሮ ኬሪያ ዛሬ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል።
የጠቅላይ አቃቤ ሕግ የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ አቶ አወል ሱልጣን እንደገለጹት፤ ወ/ሮ ኬሪያ ከተከሳሽነት ወደ ምስክርነት ተቀይረው ነበር ብለዋል።
ወ/ሮ ኬሪያ በጠቋሚዎችና ምስክሮች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 699 /2003 በገቡት ሥምምነት ዝርዝር የምስክርነት ቃላቸውን በፈቃዳቸው ሰጥተው ነበር።
በገዛ ፈቃዳቸው በጽሑፍና በሲዲ ምስክርነታቸውን ሰጥተው በኃላም በፍ/ቤት ውሳኔ ከእስር እንደተለቀቁና ጎን ለጎንም ለግለሰቧ አስፈላጊውን የምስክርነት ጥበቃ ሲደረግላቸው ነበር ብለዋል።
ይሁንና ወ/ሮ ኬሪያ ቆይተው ምስክር የመሆን ፍላጎት እንደሌላቸው እና ምስክርነት ሲሰጡ የቆዩት ተገደው እንደነበር በመግለፅ ምስክረነታቸው መቋረጡን አስረድተዋል።
በምስክሮች እና ጠቋሚዎች አዋጅ ቁጥር 699/2003 በአንቀፅ 11 መሰረት የጥበቃ ተጠቃሚው ሥምምነቱንና ግዴታውን የማያከብር ከሆነ የጥበቃ ስምምነት ውሉ ስለሚቋረጥ አቃቤ ሕግም ለወ/ሮ ኬሪያ ምስክር በመሆናቸው ይሰጣቸው የነበረውን ጥበቃ ለማንሳት መገደዱን ነው የተናገሩት።
"ከዚህም በኋላ ወይዘሮ ኬሪያ ከዚህ ቀደም በተጠረጠሩበት ወንጀል የቅድመ ምርመራ ስራ እንዲጀመር አቃቤ ሕግ ዛሬ ለፍርድ ቤት ጥያቄ አቅርቧል" ብለዋል።
የተጠርጣሪ ጠበቆች በጉዳዩ ላይ ለመከራከር አልተዘጋጀንም ብለዋል።
ፍ/ቤቱ ወ/ሮ ኬሪያ በመጪው ሰኞ ዳግም ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ አዟል።
ወ/ሮ ኬሪያ እስከ ሰኞ በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንዲቆዩ ፍ/ቤቱ መወሰኑን ኢዜአ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም የምስክርነት ጥበቃቸው ተነስቶ ዳግም ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ገለጸ።
ወ/ሮ ኬሪያ ዛሬ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል።
የጠቅላይ አቃቤ ሕግ የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ አቶ አወል ሱልጣን እንደገለጹት፤ ወ/ሮ ኬሪያ ከተከሳሽነት ወደ ምስክርነት ተቀይረው ነበር ብለዋል።
ወ/ሮ ኬሪያ በጠቋሚዎችና ምስክሮች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 699 /2003 በገቡት ሥምምነት ዝርዝር የምስክርነት ቃላቸውን በፈቃዳቸው ሰጥተው ነበር።
በገዛ ፈቃዳቸው በጽሑፍና በሲዲ ምስክርነታቸውን ሰጥተው በኃላም በፍ/ቤት ውሳኔ ከእስር እንደተለቀቁና ጎን ለጎንም ለግለሰቧ አስፈላጊውን የምስክርነት ጥበቃ ሲደረግላቸው ነበር ብለዋል።
ይሁንና ወ/ሮ ኬሪያ ቆይተው ምስክር የመሆን ፍላጎት እንደሌላቸው እና ምስክርነት ሲሰጡ የቆዩት ተገደው እንደነበር በመግለፅ ምስክረነታቸው መቋረጡን አስረድተዋል።
በምስክሮች እና ጠቋሚዎች አዋጅ ቁጥር 699/2003 በአንቀፅ 11 መሰረት የጥበቃ ተጠቃሚው ሥምምነቱንና ግዴታውን የማያከብር ከሆነ የጥበቃ ስምምነት ውሉ ስለሚቋረጥ አቃቤ ሕግም ለወ/ሮ ኬሪያ ምስክር በመሆናቸው ይሰጣቸው የነበረውን ጥበቃ ለማንሳት መገደዱን ነው የተናገሩት።
"ከዚህም በኋላ ወይዘሮ ኬሪያ ከዚህ ቀደም በተጠረጠሩበት ወንጀል የቅድመ ምርመራ ስራ እንዲጀመር አቃቤ ሕግ ዛሬ ለፍርድ ቤት ጥያቄ አቅርቧል" ብለዋል።
የተጠርጣሪ ጠበቆች በጉዳዩ ላይ ለመከራከር አልተዘጋጀንም ብለዋል።
ፍ/ቤቱ ወ/ሮ ኬሪያ በመጪው ሰኞ ዳግም ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ አዟል።
ወ/ሮ ኬሪያ እስከ ሰኞ በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንዲቆዩ ፍ/ቤቱ መወሰኑን ኢዜአ ዘግቧል።
@tikvahethiopia