ለእነ ብርጋዴር ጄነራል ተፈራ ማሞ የክስ መዝገብ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ!
የእነ ብርጋዴር ጄነራል ተፈራ ማሞ የክስ መዝገብ ለነሃሴ 17/2011 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ፡፡ የባሕር ዳር ከተማና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጉዳዩ ውስብስብና መርማሪ ቡድኑ ለጠየቀው ይግባኝ ውሳኔ ለመስጠት ተጨማሪ ጊዜ በማስፈለጉ ለነገ ነሐሴ 17/2011 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ነሐሴ 15/ 2011 ዓ.ም በነበረዉ ችሎት ከሳሽ አካል ቅድመ ምርመራ በማቋረጡ ኮሎኔል አለባቸዉ ብዙነህ ክሱ ተነስቶላቸዋል።
Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የእነ ብርጋዴር ጄነራል ተፈራ ማሞ የክስ መዝገብ ለነሃሴ 17/2011 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ፡፡ የባሕር ዳር ከተማና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጉዳዩ ውስብስብና መርማሪ ቡድኑ ለጠየቀው ይግባኝ ውሳኔ ለመስጠት ተጨማሪ ጊዜ በማስፈለጉ ለነገ ነሐሴ 17/2011 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ነሐሴ 15/ 2011 ዓ.ም በነበረዉ ችሎት ከሳሽ አካል ቅድመ ምርመራ በማቋረጡ ኮሎኔል አለባቸዉ ብዙነህ ክሱ ተነስቶላቸዋል።
Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#update የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዝደንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ከUK መንግስት ሴክሩተሪ አሎክ ሻርማ ጋር ኢስተርን ኢንደስተሪ ዞን በመገኘት ዩኒሌቨር ኩባንያን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡ ከጉብኝቱ በኃላ በዱክም ከተማ በጋራ ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል፡፡
Via #OBN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via #OBN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የከፍተኛ ትምህርት አግባብነት እና ጥራት ኤጀንሲ በአዲስ አበባና ዙሪያ ብቻ 18 ካምፓሶችን በጥራት ጉድለት ዘግቻለሁ አለ።
የኤጀንሲው ም/ል ዋና ዳይሬክተር አቶ ታምራት እንዳሉት በአዲስ አበባ እና ዙሪያ ብቻ በተደረገ ፍተሻ እና ምርመራ በጥራት ጉደለት 18 የግል ካምፓሶች እንዲዘጉ ተደርገዋል ብለዋል። ኤጀንሲው በተዘጉት ካምፓሶች እየተማሩ ያሉትን ተማሪዎች እጣ ፈንታ አለመወሰኑንም እክለዋል።
በክልል ደረጃም ቢሆን መቀሌ፣ሀረር እና ሌሎችም ቦታዎች ላይ ከጥራት እና ፍቃድ ጋር በተያያዛ የዘጋቸው ካንፓሶች መኖራቸውን ምክትል ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። በአዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን በክልል ደረጃም መሰል እርምጃዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አቶ ታምራት ተናግረዋል።
ኤጀንሲው ከቀናት በፊት እኔ ሳላውቅ ከግል ኮሌጆች ጋር በትብብር ሲሰሩ አግኝቻቸዋለሁ ያላቸውን 4 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን ካምፓስ መዝጋቱ ይታወሳል።
ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኤጀንሲው ም/ል ዋና ዳይሬክተር አቶ ታምራት እንዳሉት በአዲስ አበባ እና ዙሪያ ብቻ በተደረገ ፍተሻ እና ምርመራ በጥራት ጉደለት 18 የግል ካምፓሶች እንዲዘጉ ተደርገዋል ብለዋል። ኤጀንሲው በተዘጉት ካምፓሶች እየተማሩ ያሉትን ተማሪዎች እጣ ፈንታ አለመወሰኑንም እክለዋል።
በክልል ደረጃም ቢሆን መቀሌ፣ሀረር እና ሌሎችም ቦታዎች ላይ ከጥራት እና ፍቃድ ጋር በተያያዛ የዘጋቸው ካንፓሶች መኖራቸውን ምክትል ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። በአዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን በክልል ደረጃም መሰል እርምጃዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አቶ ታምራት ተናግረዋል።
ኤጀንሲው ከቀናት በፊት እኔ ሳላውቅ ከግል ኮሌጆች ጋር በትብብር ሲሰሩ አግኝቻቸዋለሁ ያላቸውን 4 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን ካምፓስ መዝጋቱ ይታወሳል።
ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኢራን በራሷ አቅም እንዳመረተችው የገለጸችውን የረጅም ርቀት የምድረገፅና የአየር ላይ የሚሳኤል መቃወሚያ መሳሪያን ለዕይታ አብቅታለች። ባቫር-373 የተሰኘው የሚሳኤል መቃወሚያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሮሃኒ በተገኙበት በይፋ ለዕይታ ክፍት ሆኗል።
የኢራን መገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት መሳሪያው ሲነጻጸር ከሩሲያው ኤስ-300 የሚሳኤል መቃወሚያ ጋር እኩል የሚሆን ነው። የመከላከያ ሚኒስትሩ አሚር ሃታሚ በቴሌቪዥን በተላለፈው ንግግራቸው በዚህ የረጅም ርቀት የሚሳኤል መቃወሚያ የአየር ላይ የጥቃት ኢላማዎችን እስከ 300 ኪሎሜትር ርቀት የሚጠቁም፣ በ200 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ደግሞ ጄቶችን መምታት የሚችል ነው ብለዋል። የጦር መሳሪያው ይፋ የሆነው የኢራን ብሔራዊ የመከላከያ ኢንዱስትሪ ቀንን አስመልክቶ ነው።
ምንጭ፦ ሬውተርስ/#ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢራን መገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት መሳሪያው ሲነጻጸር ከሩሲያው ኤስ-300 የሚሳኤል መቃወሚያ ጋር እኩል የሚሆን ነው። የመከላከያ ሚኒስትሩ አሚር ሃታሚ በቴሌቪዥን በተላለፈው ንግግራቸው በዚህ የረጅም ርቀት የሚሳኤል መቃወሚያ የአየር ላይ የጥቃት ኢላማዎችን እስከ 300 ኪሎሜትር ርቀት የሚጠቁም፣ በ200 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ደግሞ ጄቶችን መምታት የሚችል ነው ብለዋል። የጦር መሳሪያው ይፋ የሆነው የኢራን ብሔራዊ የመከላከያ ኢንዱስትሪ ቀንን አስመልክቶ ነው።
ምንጭ፦ ሬውተርስ/#ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert
የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ በቁጥጥር ሥር ዋለ!
33 ሰዎች በተከሰሱበት የክስ መዝገብ ለአንድ ዓመት በፖሊስ ሲፈለግ የነበረው የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ቴድሮስ ገቢባ በትናንትናው ዕለት በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡
ተከሳሹ ከሰኔ 05 እስከ 12/2010 ዓ.ም በሀዋሳ ከተማ የወላይታና ሲዳማ ብሔሮችን በማጋጨት ለሰው ሕይወት መጠፋት እና ንብረት መውደም እንዲከሰት የዕርስ በርስ ግጭት በማነሳሳትና በመጠንሰስ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተከሶ ሲፈለግ የቆየ መሆኑ ይታወሳል፡፡
ከአንድ ዓመት በኃላ የፌዴራል ፖሊስ ባደረገው ክትትል ነሃሴ 15 ቀን 2011 ዓ.ም በቁጥጥር ሥር የዋለ ሲሆን ተከሳሹ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 13ኛ የወንጀል ችሎት ሆሳዕና ተዘዋዋሪ ችሎት ቀርቧል፡፡
Via የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ በቁጥጥር ሥር ዋለ!
33 ሰዎች በተከሰሱበት የክስ መዝገብ ለአንድ ዓመት በፖሊስ ሲፈለግ የነበረው የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ቴድሮስ ገቢባ በትናንትናው ዕለት በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡
ተከሳሹ ከሰኔ 05 እስከ 12/2010 ዓ.ም በሀዋሳ ከተማ የወላይታና ሲዳማ ብሔሮችን በማጋጨት ለሰው ሕይወት መጠፋት እና ንብረት መውደም እንዲከሰት የዕርስ በርስ ግጭት በማነሳሳትና በመጠንሰስ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተከሶ ሲፈለግ የቆየ መሆኑ ይታወሳል፡፡
ከአንድ ዓመት በኃላ የፌዴራል ፖሊስ ባደረገው ክትትል ነሃሴ 15 ቀን 2011 ዓ.ም በቁጥጥር ሥር የዋለ ሲሆን ተከሳሹ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 13ኛ የወንጀል ችሎት ሆሳዕና ተዘዋዋሪ ችሎት ቀርቧል፡፡
Via የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀሰተኛ መረጃ ነበር!
ከዚህ ቀደም/ሀምሌ 18/ ዋዜማ ራድዮን ጨምሮ የተለያዩ አክቲቪስቶችና የፌስቡክ ገፆች የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ቴዎድሮስ ገቢባ ታሰሩ ብለው ያሰራጩት መረጃ ሀሰተኛ ነበር። በወቅቱ የትኛውም የመንግስት አካል ስለመታሰራቸው በይፋ አላረጋገጠም። ዋዜማ ሬድዮም #የሲአንን የፌስቡክ ገፅ ጠቅሶ ያሰራጨው መረጃ ከሀሰተኛ ገፅ የተወሰደ ነበር። አቶ ቴዎድሮስ በቁጥጥር ስር የዋሉት #ትላንት ነው።
ከሀሰተኛ የፌስቡክ ገፆች እንጠንቀቅ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከዚህ ቀደም/ሀምሌ 18/ ዋዜማ ራድዮን ጨምሮ የተለያዩ አክቲቪስቶችና የፌስቡክ ገፆች የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ቴዎድሮስ ገቢባ ታሰሩ ብለው ያሰራጩት መረጃ ሀሰተኛ ነበር። በወቅቱ የትኛውም የመንግስት አካል ስለመታሰራቸው በይፋ አላረጋገጠም። ዋዜማ ሬድዮም #የሲአንን የፌስቡክ ገፅ ጠቅሶ ያሰራጨው መረጃ ከሀሰተኛ ገፅ የተወሰደ ነበር። አቶ ቴዎድሮስ በቁጥጥር ስር የዋሉት #ትላንት ነው።
ከሀሰተኛ የፌስቡክ ገፆች እንጠንቀቅ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የኒውዚላንድ አፈ ጉባኤ በፓርላማ ክርክር ወቅት ለህፃን ጡጦ አጠቡ!
ትሪቮር ማላርድ የተባሉት የኒውዚላንድ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ በምክር ቤቱ እየተካሄደ በነበረ ክርክር ወቅት የአንድን የፓርላማ አባል ልጅ በማቀፍና ጡጦ በማጥባት አግራሞትን ፈጥረዋል፡፡ ዘጋርዲያን #በተንቀሳቃሽ ምስል ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያሳየው አፈ ጉባኤው ልጁን ያጠቡት ታማቲ ኮፊ የተባለችው የምክር ቤት አባል ክርክር እያደረገች በነበረበት ወቅት ነው፡፡
Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትሪቮር ማላርድ የተባሉት የኒውዚላንድ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ በምክር ቤቱ እየተካሄደ በነበረ ክርክር ወቅት የአንድን የፓርላማ አባል ልጅ በማቀፍና ጡጦ በማጥባት አግራሞትን ፈጥረዋል፡፡ ዘጋርዲያን #በተንቀሳቃሽ ምስል ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያሳየው አፈ ጉባኤው ልጁን ያጠቡት ታማቲ ኮፊ የተባለችው የምክር ቤት አባል ክርክር እያደረገች በነበረበት ወቅት ነው፡፡
Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"የአፋን ኦሮሞ ትምህርት #ለድርድር የሚቀርብ አይደለም" – የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ
የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የአፋን ኦሮሞ ትምህርት ለድርድር የማይቀርብና ለቋንቋው እድገት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያን ስርዓተ ትምህርት አስመልክቶ በትምህርት ሚኒስቴር የተሰጠው መግለጫ የአፋን ኦሮሞን ተጨባጭ ሁኔታ የማይገልጽ መሆኑንና የክልሉ መንግስት በቋንቋ ጉዳይ ላይ የማያወላዳ አቋም እንዳለው ህዝቡ ሊረዳ እንደሚገባም ተናግረዋል።
የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤትን የማስተዳደር፣ የትምህርት ስርዓትን ማዘጋጀት፣ የስምንተኛ ክፍል ፈተና ማዘጋጀትና አርሞ ውጤት መወሰን ለክልል የተሰጠ ስልጣን በመሆኑ በዚህ ላይ ጫና የሚያሳድር ማንም ሊኖር እንደማይገባ ገልጸው፤ እንደ ከዚህ በፊቱ ሁሉ በአፋን ኦሮሞ የሚሰጥ ትምህር እንደሚቀጥልም ነው ያሳወቁት።
የክልሉ መንግስት የአፋን ኦሮሞ ቋንቋን ለማሳደግ ከዚህ በፊት በቋንቋው ትምህርት በማይሰጥባቸው አካባቢዎች ጭምር መማሪያ እንዲሆን እየሰራ በመሆኑ ሁሉም ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ነው አቶ ሽመልስ የገለጹት።
በተጨማሪም በክልሉ ውስጥ ከክልሉ ስርዓተ ትምህርት ውጪ የሚያስተምሩ የግል ትምህርት ቤቶች ላይም በዚህ ዓመት የማስተካከያ እርምጃ እንደሚወሰድ ተጠቅሷል።
Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የአፋን ኦሮሞ ትምህርት ለድርድር የማይቀርብና ለቋንቋው እድገት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያን ስርዓተ ትምህርት አስመልክቶ በትምህርት ሚኒስቴር የተሰጠው መግለጫ የአፋን ኦሮሞን ተጨባጭ ሁኔታ የማይገልጽ መሆኑንና የክልሉ መንግስት በቋንቋ ጉዳይ ላይ የማያወላዳ አቋም እንዳለው ህዝቡ ሊረዳ እንደሚገባም ተናግረዋል።
የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤትን የማስተዳደር፣ የትምህርት ስርዓትን ማዘጋጀት፣ የስምንተኛ ክፍል ፈተና ማዘጋጀትና አርሞ ውጤት መወሰን ለክልል የተሰጠ ስልጣን በመሆኑ በዚህ ላይ ጫና የሚያሳድር ማንም ሊኖር እንደማይገባ ገልጸው፤ እንደ ከዚህ በፊቱ ሁሉ በአፋን ኦሮሞ የሚሰጥ ትምህር እንደሚቀጥልም ነው ያሳወቁት።
የክልሉ መንግስት የአፋን ኦሮሞ ቋንቋን ለማሳደግ ከዚህ በፊት በቋንቋው ትምህርት በማይሰጥባቸው አካባቢዎች ጭምር መማሪያ እንዲሆን እየሰራ በመሆኑ ሁሉም ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ነው አቶ ሽመልስ የገለጹት።
በተጨማሪም በክልሉ ውስጥ ከክልሉ ስርዓተ ትምህርት ውጪ የሚያስተምሩ የግል ትምህርት ቤቶች ላይም በዚህ ዓመት የማስተካከያ እርምጃ እንደሚወሰድ ተጠቅሷል።
Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ!
የቁልቢ ገብርኤል ገዳም አስተዳዳሪ መልዓከኃይል ቆሞስ አባ እንቁስላሴ ድንገተኛ ህልፈተ ሕይወት ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 11 ሰዎችን በመያዝ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ። የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ድቪዝን ኃላፊ ኮማንደር ስዩም ደገፋ ለኢዜአ እንደገለጹት የገዳሙን አስተዳዳሪ የአሟሟት ሁኔታ ለማጣራት ከዞንና ከሜታ ወረዳ አቃቤ ህግና ፖሊስ የተውጣጣ ቡድን ተቋቁሞ ምርመራ በመደረግ ላይ ነው።
በዚህም እስካሁን የተጠረጠሩ 11 ሰዎችን በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሆነም አመልክተዋል። መርማሪ ቡድኑም ወደዳግማዊ ምኒሊክ ሆስፒታል የተላከውን የአስክሬን ምርመራ ውጤት በመጠባበቅ ላይ መሆኑን ገልጸዋል።
የገዳሙ አስተዳዳሪ ህይወታቸው ባለፈ በበነገታው የአካባቢው ነዋሪዎች ከወረዳው አስተዳዳሪ፣ ከአገር ሽማግሌዎችና ሃይማኖት አባቶች ጋር ውይይት ከዳረጉና የጋራ መግባባት ላይ ከተደረሰ በኋላ ከህግ አግባብነት ውጭ መንገድ መዝጋታቸውን ኮማንደር ስዩም አያይዘው ተናግረዋል።
ከእዚህ በተጨማሪ ሌሎች የጸጥታ ችግሮችን በመፈጸም ከጸጥታ ኃይሉ ጋር በተፈጠረው ግጭት አንድ የስምንት ዓመት ታዳጊ ሕጻን ሕይወቱ ማለፉንና በአራት ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን አመልክተዋል። ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በአሁኑ ወቅት በድሬዳዋ ህክምናቸውን እየተከታተሉ መሆኑንም ገልጸዋል።
የገዳሙ አስተዳዳሪ መልዓከ ኃይል ቆሞስ አባ እንቁስላሴ ባለፈው ነሐሴ 12 ቀን 2011 ዓ.ም በገዳሙ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ድንገት ሕይወታቸው አልፎ መገኘቱ ይታወሳል። የቀብር ሥነስርአታቸውም ባለፈው ማክሰኞ በትውልድ ስፍራቸው መፈጸሙ ታውቋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የቁልቢ ገብርኤል ገዳም አስተዳዳሪ መልዓከኃይል ቆሞስ አባ እንቁስላሴ ድንገተኛ ህልፈተ ሕይወት ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 11 ሰዎችን በመያዝ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ። የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ድቪዝን ኃላፊ ኮማንደር ስዩም ደገፋ ለኢዜአ እንደገለጹት የገዳሙን አስተዳዳሪ የአሟሟት ሁኔታ ለማጣራት ከዞንና ከሜታ ወረዳ አቃቤ ህግና ፖሊስ የተውጣጣ ቡድን ተቋቁሞ ምርመራ በመደረግ ላይ ነው።
በዚህም እስካሁን የተጠረጠሩ 11 ሰዎችን በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሆነም አመልክተዋል። መርማሪ ቡድኑም ወደዳግማዊ ምኒሊክ ሆስፒታል የተላከውን የአስክሬን ምርመራ ውጤት በመጠባበቅ ላይ መሆኑን ገልጸዋል።
የገዳሙ አስተዳዳሪ ህይወታቸው ባለፈ በበነገታው የአካባቢው ነዋሪዎች ከወረዳው አስተዳዳሪ፣ ከአገር ሽማግሌዎችና ሃይማኖት አባቶች ጋር ውይይት ከዳረጉና የጋራ መግባባት ላይ ከተደረሰ በኋላ ከህግ አግባብነት ውጭ መንገድ መዝጋታቸውን ኮማንደር ስዩም አያይዘው ተናግረዋል።
ከእዚህ በተጨማሪ ሌሎች የጸጥታ ችግሮችን በመፈጸም ከጸጥታ ኃይሉ ጋር በተፈጠረው ግጭት አንድ የስምንት ዓመት ታዳጊ ሕጻን ሕይወቱ ማለፉንና በአራት ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን አመልክተዋል። ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በአሁኑ ወቅት በድሬዳዋ ህክምናቸውን እየተከታተሉ መሆኑንም ገልጸዋል።
የገዳሙ አስተዳዳሪ መልዓከ ኃይል ቆሞስ አባ እንቁስላሴ ባለፈው ነሐሴ 12 ቀን 2011 ዓ.ም በገዳሙ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ድንገት ሕይወታቸው አልፎ መገኘቱ ይታወሳል። የቀብር ሥነስርአታቸውም ባለፈው ማክሰኞ በትውልድ ስፍራቸው መፈጸሙ ታውቋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከመልዓከኃይል ቆሞስ አባ እንቁስላሴ ድንገተኛ ህልፈተ ሕይወት ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 11 ሰዎችን በመያዝ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ-ካርታ!
አክቲቪስት #ጃዋር_መሐመድ የኢትዮጵያ የትምህርትና ሥልጠና ፍኖተ-ካርታ «ግልፅ ያልሆነ፣ በቂ ጥናትና በቂ ውይይት ያልተካሔደበት» ነው ሲል ተቸ። በ2013 ዓ.ም. ሥራ ላይ ይውላል ተብሎ የሚጠበቀው ፍኖተ-ካርታ «ተድበስብሶና ተምታቶ የቀረበ» ነው ሲል ወርፎታል።
ለኦኤምኤን በሰጠው ማብራሪያ «የትምህርት ፍኖተ-ካርታ ከሀገር ግንባታ ጋር የተያያዘ ነው። የሀገር ግንባታ ደግሞ ፖለቲካዊ ፕሮጀክት ነው። ስለዚህ የትምህርት ፍኖተ-ካርታው ካገሪቷ የፖለቲካ ፍኖተ-ካርታ ጋ መዋሐድ መቻል አለበት» ብሏል
አዘጋጆች «ብቃት ያላቸው ባለሙያዎች መሆን ነበረባቸው፤ በሀገሪቷ ያሉ ብሔር ብሔረሰቦችን የተለያዩ ባለድርሻዎችን ያሳተፈ ሊሆን ይገባዋል» ያለው ጃዋር «ሀገሪቷ ከምትፈልገው የፖለቲካ ፍኖተ-ካርታ የሚጻረር» ነው የሚል ዕምነት እንዳለው ተናግሯል።
ጃዋር «እኔ እንደማስበው የታሪክ መፃህፍቶች ውስጥ ያለው ይዘት በምሁራን በደንብ ተገምግሞ ለሕዝብ ቀርቦ ውይይት እና ክርክር ሳይደረግበት ወደ መተግበር እንገባለን ካሉ ይኸቺን ሀገር ወደ መበታተን ለማቃረብ የሚደረግ ነው» ሲል አስጠንቅቋል።
Via #EsheteBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አክቲቪስት #ጃዋር_መሐመድ የኢትዮጵያ የትምህርትና ሥልጠና ፍኖተ-ካርታ «ግልፅ ያልሆነ፣ በቂ ጥናትና በቂ ውይይት ያልተካሔደበት» ነው ሲል ተቸ። በ2013 ዓ.ም. ሥራ ላይ ይውላል ተብሎ የሚጠበቀው ፍኖተ-ካርታ «ተድበስብሶና ተምታቶ የቀረበ» ነው ሲል ወርፎታል።
ለኦኤምኤን በሰጠው ማብራሪያ «የትምህርት ፍኖተ-ካርታ ከሀገር ግንባታ ጋር የተያያዘ ነው። የሀገር ግንባታ ደግሞ ፖለቲካዊ ፕሮጀክት ነው። ስለዚህ የትምህርት ፍኖተ-ካርታው ካገሪቷ የፖለቲካ ፍኖተ-ካርታ ጋ መዋሐድ መቻል አለበት» ብሏል
አዘጋጆች «ብቃት ያላቸው ባለሙያዎች መሆን ነበረባቸው፤ በሀገሪቷ ያሉ ብሔር ብሔረሰቦችን የተለያዩ ባለድርሻዎችን ያሳተፈ ሊሆን ይገባዋል» ያለው ጃዋር «ሀገሪቷ ከምትፈልገው የፖለቲካ ፍኖተ-ካርታ የሚጻረር» ነው የሚል ዕምነት እንዳለው ተናግሯል።
ጃዋር «እኔ እንደማስበው የታሪክ መፃህፍቶች ውስጥ ያለው ይዘት በምሁራን በደንብ ተገምግሞ ለሕዝብ ቀርቦ ውይይት እና ክርክር ሳይደረግበት ወደ መተግበር እንገባለን ካሉ ይኸቺን ሀገር ወደ መበታተን ለማቃረብ የሚደረግ ነው» ሲል አስጠንቅቋል።
Via #EsheteBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
24 ሺህ የሚጠጋ ህዝብ ከቀዬው ተፈናቅሏል!
በክረምቱ ወራት በአንዳንድ የኢትዮጵያ ክፍሎች በደረሰ የጎርፍ አዳጋ 24 ሺህ የሚጠጋ ህዝብ ከቀዬው መፈናቀሉን የአደጋ ስጋትና ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ። በቀሪው የክረምት ወቅትም በአንዳንድ አካባቢዎች ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊከሰት ስለሚችል ህዝቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ የብሔራዊ ሚቲዎሮሎጂ ኤጀንሲ በበኩሉ አሳስቧል።
Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በክረምቱ ወራት በአንዳንድ የኢትዮጵያ ክፍሎች በደረሰ የጎርፍ አዳጋ 24 ሺህ የሚጠጋ ህዝብ ከቀዬው መፈናቀሉን የአደጋ ስጋትና ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ። በቀሪው የክረምት ወቅትም በአንዳንድ አካባቢዎች ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊከሰት ስለሚችል ህዝቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ የብሔራዊ ሚቲዎሮሎጂ ኤጀንሲ በበኩሉ አሳስቧል።
Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሼር #share
የንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ነሃሴ 18 አገልግሎት አይሰጡም!!
"...ባንካችን የቴክኖሎጂ አቅሙን በማሳደግ ረገድ ፕሮጀክት ቀርፆ የድርጊት መርሃ ግብር በመንደፍ የፊታችን ነሀሴ 18 ቀን 2011 ዓ/ም ተግባራዊ ስለሚያደርግ ሁሉም የባንካችን ቅርንጫፎች አገልግሎት የማይሰጡ መሆናቸውን በታላቅ አክብሮት እየገለፅን፣ የኤቲ ኤም ማሽኖቻችንና የሲ.ቢ.ኢ ብር በዕለቱ የተለመደውን የባንክ አገልግሎት የሚሰጡ መሆኑን እናሳውቃለን።" የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ነሃሴ 18 አገልግሎት አይሰጡም!!
"...ባንካችን የቴክኖሎጂ አቅሙን በማሳደግ ረገድ ፕሮጀክት ቀርፆ የድርጊት መርሃ ግብር በመንደፍ የፊታችን ነሀሴ 18 ቀን 2011 ዓ/ም ተግባራዊ ስለሚያደርግ ሁሉም የባንካችን ቅርንጫፎች አገልግሎት የማይሰጡ መሆናቸውን በታላቅ አክብሮት እየገለፅን፣ የኤቲ ኤም ማሽኖቻችንና የሲ.ቢ.ኢ ብር በዕለቱ የተለመደውን የባንክ አገልግሎት የሚሰጡ መሆኑን እናሳውቃለን።" የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Photoshop
ከሰሞኑን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች #ISIS የለቀቀው ተብሎ እየተሰራጨ የሚገኘው #የኢትዮጵያ ስም ያለበት ፎቶ #ሀሰተኛና በphotoshop የተሰራ ነው።
NB. በፎቶው ላይ የምትመለከቷቸው ታጣቂዎች #የISIS ሳይሆኑ #የአልሸባብ ታጣቂዎች ናቸው። #TIKVAH_ETH
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከሰሞኑን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች #ISIS የለቀቀው ተብሎ እየተሰራጨ የሚገኘው #የኢትዮጵያ ስም ያለበት ፎቶ #ሀሰተኛና በphotoshop የተሰራ ነው።
NB. በፎቶው ላይ የምትመለከቷቸው ታጣቂዎች #የISIS ሳይሆኑ #የአልሸባብ ታጣቂዎች ናቸው። #TIKVAH_ETH
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በድሬዳዋ የተከሰተውን የቹኩን- ጉንያ የትኩሳት ህመም ወረርሽኝን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያግዝ የጽዳት ዘመቻ ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ። ከተያዘው ወር ጀምሮ በተከሰተው የቹኩን- ጉንያ ቫይረስ ወረርሽኝ ህመም ከ7ሺህ በላይ ሰዎች መጠቃታቸው ታውቋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አከራካሪው የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ ካርታ!
ዶክተር ገረመው ሁሉቃ(ከትምህርት ሚኒስቴር)፦
"ከቋንቋ ጋር በተያያዘ የፌደራል እና የክልል መንግስታት ስልጣንን በሚመለከት አሁንም መጣራት ያሉባቸው ነገሮች እንዳሉ እያየን ነው። ፍኖተ ካርታው ገና እየተሰራበት ያለ ሰነድ ነው። የፌደራል መንግስት የስራ ቋንቋ ከ3ኛ ክፍል ጀምሮ ይሰጣል ይላል፤ የ8ኛ ክፍል ፈተናም ብሄራዊ ፈተና ሆኖ ግን ተተርጉሞ ለክልሎች ይሰጣል ይላል እነዚህ ሁለቱ ጉዳዮች የክልል መንግስታትን ስልጣን ይነካሉ ህገመንግስቱ እንደሚለው ከ1ኛ ክፍል - 8ኛ ክፍል ያለውን የትምህርት መስጫ ቋንቋ የሚወስነው የክልሉ መንግስት ነው። ይህ መታየት ያለበት ጉዳይ ስለሆነ ትምህርት ሚኒስቴር እየሰራበት ይገኛል።"
▫️ጉዶዮቹ የመጨረሻ ውሳኔ ያልተላለፈባቸው ከሆኑ ትላንት በትምህርት ሚኒስትሩ የተሰጠው መግለጫስ ተብለው ከቢቢሲ የተጠየቁት ዶክተር ገረመው ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል፦
"የትላንቱ መግለጫ በ2012 ዓ/ም ፍኖተ ካርታው ተግባራዊ እንደሚሆን ለማስተዋወቅ እንጂ ስሱ ተብለው የተያዙና ውሳኔ ያልተሰጠባቸው ጉዳዮች አሉ። ፍኖተ ካርታው ገና እየተጠና ያለ ነገር ነው #የመጨረሻ አይደለም። በቀጣዩ ሳምንት በጅግጅጋ በሚደረገው የትምህርት ኮንፈረንስ ውይይት ይደረግበታል። ክልሎችም ስለሚሳተፉ እነዚህ ጉዳዮች #መፍትሄ ያገኛሉ።"
#BBCአማርኛ
#TIKVAH_ETH
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶክተር ገረመው ሁሉቃ(ከትምህርት ሚኒስቴር)፦
"ከቋንቋ ጋር በተያያዘ የፌደራል እና የክልል መንግስታት ስልጣንን በሚመለከት አሁንም መጣራት ያሉባቸው ነገሮች እንዳሉ እያየን ነው። ፍኖተ ካርታው ገና እየተሰራበት ያለ ሰነድ ነው። የፌደራል መንግስት የስራ ቋንቋ ከ3ኛ ክፍል ጀምሮ ይሰጣል ይላል፤ የ8ኛ ክፍል ፈተናም ብሄራዊ ፈተና ሆኖ ግን ተተርጉሞ ለክልሎች ይሰጣል ይላል እነዚህ ሁለቱ ጉዳዮች የክልል መንግስታትን ስልጣን ይነካሉ ህገመንግስቱ እንደሚለው ከ1ኛ ክፍል - 8ኛ ክፍል ያለውን የትምህርት መስጫ ቋንቋ የሚወስነው የክልሉ መንግስት ነው። ይህ መታየት ያለበት ጉዳይ ስለሆነ ትምህርት ሚኒስቴር እየሰራበት ይገኛል።"
▫️ጉዶዮቹ የመጨረሻ ውሳኔ ያልተላለፈባቸው ከሆኑ ትላንት በትምህርት ሚኒስትሩ የተሰጠው መግለጫስ ተብለው ከቢቢሲ የተጠየቁት ዶክተር ገረመው ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል፦
"የትላንቱ መግለጫ በ2012 ዓ/ም ፍኖተ ካርታው ተግባራዊ እንደሚሆን ለማስተዋወቅ እንጂ ስሱ ተብለው የተያዙና ውሳኔ ያልተሰጠባቸው ጉዳዮች አሉ። ፍኖተ ካርታው ገና እየተጠና ያለ ነገር ነው #የመጨረሻ አይደለም። በቀጣዩ ሳምንት በጅግጅጋ በሚደረገው የትምህርት ኮንፈረንስ ውይይት ይደረግበታል። ክልሎችም ስለሚሳተፉ እነዚህ ጉዳዮች #መፍትሄ ያገኛሉ።"
#BBCአማርኛ
#TIKVAH_ETH
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በአስቸኳይ እረፍታቸውን አቋርጠው እንዲመጡ ተጠሩ። የምክር ቤቱ አባላት ሰኔ 30 ቀን 2011 ዓ.ም ነበር ስራቸውን አጠናቀው ለእረፍት የተበኑት።
ይሁንና የምክር ቤቱ አባላት ነገ ለአስቸኳይ ስብሰባ እረፍታቸውን አቋርጠው እንደተጠሩ የምክር ቤቱ ህዝብ ግንኙነት ስራ ክፍል ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታውቋል። የምክር ቤቱ አባላት ነገ ሐሴ 18 ቀን 2011 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በሚያካሂደው 3ኛ አስቸኳይ ስብሰባው እንዲገኙ ተጠርተዋል።
ምክር ቤቱ በነገው ውሎውም የምርጫና የፖለቲካ ፓርቲዎች ረቂቅ አዋጅን መርምሮ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡ በዚህ አዋጆች ላይ ከዚህ በፊት የተለያዩ ውይይቶች የተካሄዱ ሲሆን የተወሰኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች አዋጁን እንደማይቀበሉት ማሳወቃቸው ይታወሳል።
ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ይሁንና የምክር ቤቱ አባላት ነገ ለአስቸኳይ ስብሰባ እረፍታቸውን አቋርጠው እንደተጠሩ የምክር ቤቱ ህዝብ ግንኙነት ስራ ክፍል ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታውቋል። የምክር ቤቱ አባላት ነገ ሐሴ 18 ቀን 2011 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በሚያካሂደው 3ኛ አስቸኳይ ስብሰባው እንዲገኙ ተጠርተዋል።
ምክር ቤቱ በነገው ውሎውም የምርጫና የፖለቲካ ፓርቲዎች ረቂቅ አዋጅን መርምሮ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡ በዚህ አዋጆች ላይ ከዚህ በፊት የተለያዩ ውይይቶች የተካሄዱ ሲሆን የተወሰኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች አዋጁን እንደማይቀበሉት ማሳወቃቸው ይታወሳል።
ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአሸንድዬ ጨዋታ አከባበር በላልይበላ!
በአሸንድዬ በዓል #የሀገር ውስጥ እና #የውጭ ሀገራት ጎብኝዎች እየታደሙ ነው። የአሸንድዬ በዓል "የባህል እሴቶቻችን የአብሮነታችን መሠረት ናቸው" በሚል መሪ ሀሳብ እየተከበረ ነው።
የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የላልይበላና አካባቢው ነዋሪዎች በበዓሉ እየታደሙ ነው። የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገራት ጎብኝዎችም ተገኝተዋል። ይህም በዓሉን በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ለማስተዋዎቅ እና ተጠቃሚ ለመሆን ያስችላል።
Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአሸንድዬ በዓል #የሀገር ውስጥ እና #የውጭ ሀገራት ጎብኝዎች እየታደሙ ነው። የአሸንድዬ በዓል "የባህል እሴቶቻችን የአብሮነታችን መሠረት ናቸው" በሚል መሪ ሀሳብ እየተከበረ ነው።
የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የላልይበላና አካባቢው ነዋሪዎች በበዓሉ እየታደሙ ነው። የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገራት ጎብኝዎችም ተገኝተዋል። ይህም በዓሉን በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ለማስተዋዎቅ እና ተጠቃሚ ለመሆን ያስችላል።
Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#update ከተሰጣቸዉ እዉቅናና ፍቃድ ዉጪ የትምህርት አገልግሎት የሚሰጡ የግልና የመንግስት ኮሌጆችና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከድርጊታቸዉ እንዲቆጠቡ የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ አሳሰበ፡፡ ኤጀንሲዉ ከእዉቅናዉ ዉጪ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የትምህርት ተቋማት ላይ እርምጃ ወስዷል፡፡
በአዲስ አበባና አካባቢዋ 18 የግል ኮሌጆችና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ካምፓሶችን መዝጋቱን አስተዉቋል፡፡ እንዲሁም 4 የመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከእዉቅናዉ ዉጪ ከግል የትምህርት ተቋማት ጋር በትብብር ሲሰጡ የነበረዉን አገልግሎት እንዲቋረጥ መደረጉን የኤንጀንሲዉ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ታምራት ሞታ ተናግረዋል፡።
በተለይም በግል ዘርፍ የትምህርት አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት አብዛኞቹ ደረጃቸዉን ባለጠበቁ የትምህረት ቅጥር ግቢ ዉስጥ እንደነበር ጠቁመው የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ኤጀንሲዉ ቁርጠኛ አቋም መያዙንም ምክትል ዳሬክተሩ አስታዉቀዋል።
Via #AMN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአዲስ አበባና አካባቢዋ 18 የግል ኮሌጆችና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ካምፓሶችን መዝጋቱን አስተዉቋል፡፡ እንዲሁም 4 የመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከእዉቅናዉ ዉጪ ከግል የትምህርት ተቋማት ጋር በትብብር ሲሰጡ የነበረዉን አገልግሎት እንዲቋረጥ መደረጉን የኤንጀንሲዉ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ታምራት ሞታ ተናግረዋል፡።
በተለይም በግል ዘርፍ የትምህርት አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት አብዛኞቹ ደረጃቸዉን ባለጠበቁ የትምህረት ቅጥር ግቢ ዉስጥ እንደነበር ጠቁመው የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ኤጀንሲዉ ቁርጠኛ አቋም መያዙንም ምክትል ዳሬክተሩ አስታዉቀዋል።
Via #AMN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ📸አትሌት ኃይሌ ገብረ ስላሴ ያስገነባውን ትምህርት ቤት ለማስመረቅ ዋግ ኽምራ ገብቷል። ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረ ስላሴ ሚያዝያ 27ቀን 2011 ዓመተ ምህረት ነበር በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ፃግብጂ ወረዳ የሚገኘውን የገልኩ የዳስ ትምህርት ቤት ሙሉ በሙሉ ደረጃውን የጠበቀ አድርጎ ለማስገንባት የመሠረት ድንጋይ ያስቀመጠው፡፡
በወቅቱ “ትምህርት ቤቱን ለ2012 የትምህርት ዘመን ሙሉ በሙሉ ከዳስ ለማላቀቅ ጥረት አደርጋለሁ” ሲል ቃል ገብቶ እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡ በዚህም ግንባታው አራት ወራት ባልሞላ ጊዜ ተጠናቅቆ ለምረቃም ለማስተማርም ተዘጋጅቷል።
ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረ ስላሴ ትናንት ማታ በሰቆጣ፣ ዛሬ ደግሞ ፃግብጂ ወረዳ ገልኩ ትምህርት ቤት ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል ፡፡ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ በሦስት ወራት ውስጥ በሁለት ሕንፃዎች የተከፈሉ ስምንት ክፍሎችን ማስገንባቱ ነው የተገለጸው፡፡
በትምህርት ቤቱ ምርቃ ስነ ስርዓት ላይም የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ይልቃል ከፋለ እና የሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረ ስላሴ ባለቤት እንደሚገኙም አመብድ ዘግቧል፡፡
Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በወቅቱ “ትምህርት ቤቱን ለ2012 የትምህርት ዘመን ሙሉ በሙሉ ከዳስ ለማላቀቅ ጥረት አደርጋለሁ” ሲል ቃል ገብቶ እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡ በዚህም ግንባታው አራት ወራት ባልሞላ ጊዜ ተጠናቅቆ ለምረቃም ለማስተማርም ተዘጋጅቷል።
ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረ ስላሴ ትናንት ማታ በሰቆጣ፣ ዛሬ ደግሞ ፃግብጂ ወረዳ ገልኩ ትምህርት ቤት ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል ፡፡ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ በሦስት ወራት ውስጥ በሁለት ሕንፃዎች የተከፈሉ ስምንት ክፍሎችን ማስገንባቱ ነው የተገለጸው፡፡
በትምህርት ቤቱ ምርቃ ስነ ስርዓት ላይም የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ይልቃል ከፋለ እና የሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረ ስላሴ ባለቤት እንደሚገኙም አመብድ ዘግቧል፡፡
Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia