TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.13K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#ዓድዋ

እንኳን ለ129ኛው የዓድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ !

" ዓድዋ ዛሬ ናት ዓድዋ ትናንት
መቼ ተነሱና የወዳደቁት
ምስጋና ለእነርሱ ለዓድዋ ጀግኖች
ለዛሬ ነፃነት ላበቁኝ ወገኖች
የጥቁር ድል አምባ ዓድዋ
አፍሪካ እምዬ #ኢትዮጵያ
ተናገሪ
የድል ታሪክሽን አውሪ !!  " - ጂጂ

መልካም የድል በዓል ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ !!

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ዓድዋ እንኳን ለ129ኛው የዓድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ ! " ዓድዋ ዛሬ ናት ዓድዋ ትናንት መቼ ተነሱና የወዳደቁት ምስጋና ለእነርሱ ለዓድዋ ጀግኖች ለዛሬ ነፃነት ላበቁኝ ወገኖች የጥቁር ድል አምባ ዓድዋ አፍሪካ እምዬ #ኢትዮጵያ ተናገሪ የድል ታሪክሽን አውሪ !!  " - ጂጂ መልካም የድል በዓል ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ !! @tikvahethiopia
#ዓድዋ129

ዛሬ የካቲት 23 መላ የኢትዮጵያ ህዝብና ጀግኖች አርበኞች በአንድነት የኢጣሊያንን ቅኝ ገዢ ጦር ዓድዋ ላይ ድል ያደረጉበት በዓል እየተከበረ ይገኛል።

ንጉሰ ነገስት አፄ ሚኒልክ የመሯቸዉ ኢትዮጵያዉን ጀግኖች ኢትዮጵያን የወረረ ጠላታቸዉን ዓድዋ ላይ መትተዉ አሳፍረዉ፣ አዋርደው ፣ አንገት አስደፍተው የመለሱት ልክ በዛሬው ዕለት ከ129 ዓመታት በፊት ነበር።

#ዓድዋ
#የመላአፍሪካውያንድል
#Ethiopia

@tikvahethiopia
#SafaricomEthiopia

ዝግጁ ነሽሽሽሽሽ?? የሳፋሪኮም ቅድሜያ ለሴቶች 5ኬሜ ሩጫ ምዝገባ ጀምሯል M-PESAን ተጠቅመሽ 540 ብር የነበረውን ቲሸርት
በ 389 ብር ብቻ አግኚ!!!
ከM-Pesa ጋር አብረን እንፍጠን። #Andegna #WomensRun #MPESASafaricom
#Earthquake

ዛሬ የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ.ም በዓዲግራት ፣ በዓድዋ፣ ፣ ወቕሮ ፣ መቐለ ጨምሮ በበርካታ የትግራይ አከባቢዎች ከቀኑ 5:30 ጀምሮ ለሰከንዶች የቆየ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዘርት ተከሰተዋል።

የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ድረገጽ ከዓዲግራት 46 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሬክተር ስኬል 5.2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ እንደነበር አመልክቷል።

የመሬት መንቀጥቀጡ ከኢትዮጵያ እና ኤርትራ ድንባር ላይ መከሰቱ ተነግሯል።

@tikvahethiopia
#MoE

" በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ዕጩ ተመራቂዎች የፋይዳ መታወቂያ ሊያወጡ ይገባል " - ትምህርት ሚኒስቴር

የካቲት 21/2017 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተፈርሞ ለሁሉም የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተላከ ሰርኩላር፤ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪ እና የሠራተኞችን መረጃ በተደራጀ መልኩ ለመያዝ ጠቀሜታ እንዳለው ይገልጻል።

የሀገር አቀፍ ፈተናዎችን ደህንነት ለማስጠበቅ አስፈላጊ መሆኑንም ያትታል።

በዚህም በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ዕጩ ተመራቂዎች ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ ሊያወጡ እንደሚገባ / እንደ ቅደመ ሁኔታ መቀመጡን አሳስቧል።

Via
@tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#ነዳጅ የነዳጅ ምርቶች ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል። የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል። አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97…
#ነዳጅ

የነዳጅ ምርቶች ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል።

የመጋቢት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።


አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር

አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር

አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር

የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር

አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97 ብር

አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ 108.30 ብር

#ነዳጅ #ኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ብርሃን_ባንክ
የብርሃን ጉዞጎ ተጠቃሚዎች ብቻ የሚያገኙትን ልዩ ቅናሾች እና ጥቅሞች ያግኙ፣ ይህም ጉዞዎን የበለጠ ተመጣጣኝ እና አስደሳች ያደርገዋል።
👉ደንበኞች በአካል መሄድ ሳያስፈልጋቸው ከ10 በላይ አለም አቀፍ የአየር መንገዶች የበረራ ትኬቶችን ዋጋ ማወዳደር ያስችላል።
👉ደንበኞች በሚመርጡት አየር መንገድ የበረራ ትኬቶች ላይ ቅናሽ ዋጋዎች እንዲያገኙ ያስችላል።
👉ደንበኞች በሚመርጡት ሰዓት እና ዋጋ አስተማማኝ የበረራ ቡኪንግ ለመያዝ ያስችላል።
👉በሁሉም የባንካችን ቅርንጫፎች፣ በሞባይል ወይንም በኢንተርኔት ባንኪንግ ክፍያዎችን መፈጸም ያስችላል፡፡
👉ያለ ተጨማሪ ክፍያ ሳምንቱን ሙሉ ለ 24 ሰዓታት የባለሙያ ምክር እና እርዳታ እንዲያገኙ ያስችላል።
ስለ ብርሃን ጉዞጎ (GuzoGo) አገልግሎት ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት በ0116506355 /0116507425 ወይም በነፃ የጥሪ ማዕከል ቁጥር 8292 ላይ ይደውሉ፤
እንደስማችን ብርሃን ነው ስራችን
#eticket #guzogo #internetbanking #mobilebankingbanking #berhanbank #bank #finance #Stressfreebanking #bankinethiopia
#SafaricomEthiopia

🗺 ሃይኪንግ ላይ ሆናችሁ ዳታ መጠቀም ፈልጋችሁ ታውቃላችሁ? እነሆ አዲስ ቅመም!
💨 የትም ይዛችሁት መሄድ የሚያስችላችሁ እስከ 6 ሰዓት የሚቆይ የባትሪ አቅም ያለውና አዳዲስ የቴክኖሎጂ ትሩፋቶችን ይዞ በአንዴ እስከ 8 ሰው ድረስ የሚያስጠቅመውን ልዩ ቅመም MIFIን ገዝተን ፈጣን 4G ኢንተርኔት እንጠቀም! ለ30 ቀን ከሚቆይ ነጻ 30ጊባ ዳታ ጉርሻ ጋር 😋

ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት
  
🔗 የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

#MPESASafaricom #1Wedefit #Furtheraheadtogether
" እገዳው ተነስቷል " - ኢሰመኮ

የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን በኅዳር ወር 2017 ዓ.ም. ፦
- የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል፣
- የሕግ ባለሙያዎች ለሰብአዊ መብቶች
- ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ የተባሉ 3 በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ የሚሠሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ ጥሎት የነበረውን እገዳ ካነሳ በኋላ በታኅሣሥ ወር 2017 ዓ.ም. የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል እና የሕግ ባለሙያዎች ለሰብአዊ መብቶችን በድጋሚ እንዲሁም የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ እና የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማእከልን ማገዱ ይታወሳል።

ኢሰመኮ ታኅሣሥ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ የሚተላለፉ እገዳዎች በሲቪል ምኅዳሩ እና በማኅበር የመደራጀት መብቶች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንዳይፈጥሩ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስቧል።

በተጨማሪም ኢሰመኮ በድርጅቶቹ እገዳ ላይ ሰፊ የሰብአዊ መብቶች ምርመራ ያከናወነ ሲሆን የደረሰባቸውን ግኝቶች እና ምክረ ሐሳቦች ለሚመለከታቸው አካላት ማጋራቱን አመልክቷል።

ኢሰመኮ በተለይ አዲስ በተሾሙት ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ በኩል ጉዳዩን በልዩ ትኩረት በመከታተል ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን እና እገዳ ከተጣለባቸው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን በማድረግ ለጉዳዩ መፍትሔ ለማስገኘት ሢሠራ እንደቆየ ጠቁሟል።

ይህ የኢሰመኮ ጥረት ውጤት በማስገኘቱ በ4ቱ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ ተጥሎ የነበረው እገዳ ከዛሬ የካቲት 24 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ የተነሳ በመሆኑን ኢሰመኮ አሳውቋል።


@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ፐርፐዝብላክ ° " ሥራ ላይ የነበሩ ሱቆችም የቤት ኪራይ መክፈል ስላልተቻለ ሊዘጉ ነው " - የፐርፐዝ ብላክ ባለአክሲዮኖች ° " በፍርድ ቤት የተያዘ ጉዳይ ስላለ ምንም  አይነት መግለጫ አንሰጥም " - ድርጅቱ የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ባለአክሲዮኖች፣ የድርጅቱ አካላት መታሰራቸውን ተከትሎ ድርጅቱ ላይ ባላቸው ሼር ላይ ሥጋትና ቅሬታ እንዳደረባቸው፣ ለቅሬታቸው አፋጣኝ ምላሽ  እንዲሰጣቸው በቲክቫህ…
“ ድርጅቱ ለኪራይ፣ ደመወዝና ለሌሎች ወጪዎች ክፍያ ባለመፈጸሙ ሠራተኛው ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቋል ” - የፐርፐዝ ብላክ ባለአክሲዮኖች

ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ሕብረት ባንክ ካለው ገንዘብ ውጪ በሌሎች ባንኮች ያለውን ገንዘብ እንዲያንቀሳቅስ ፍርድ ቤት ውሳኔ ቢሰጥም በዐቃቢ ህግ ይጎባኝ ውሳኔው መታገዱን የፍርድ ቤት ሰነድና ባለአክሲዮኖች አመለከቱ።

ሁነቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያስረዱት ባለአክሲዮኖች የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ አካውንት ለሰባት ወራት ተዘግቶ መቆየቱን፣ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለደመወዝና ሥራ ማስኬጃ ክርክር ሲካሄድ ቆይቶ እንደነበር ገልጸዋል።

በክርክር ሂደቱም፣ ፍርድ ቤት ሕብረት ባንክ ከተቀመጠው ገንዘቡ ውጪ በሌሎች ባንኮች ያለው የፐርፐዝ ብላክ ገንዘብ እንዲንቀሳቀስ፣ ለማንቀሳቀስ አስተዳዳሪ እንዲሾም ወስኖ እንደነበር አስረድተዋል።

“ነገር ግን ዐቃቤ ሕግ ውሳኔውን በመቃወም ይግባኝ ጠይቆ የስር ፍርድ ቤቱ የሰጠውን ውሳኔ አሳግዶታል” ብለዋል።

“ድርጅቱ ለኪራይ፣ ደመወዝና ለሌሎች ወጪዎች ክፍያ ባለመፈጸሙ ሠራተኛው ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቋል” ያሉት ባለክሲዮኖቹ፣ “ድርጅቱ የሚፈርስ እንኳን ከሆነ አግባብ ባለው መንገድ መፍረስ ነበረበት እጅግ ከባድ ሁኔታ ተፈጥሯል” ሲሉ አማረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ሰነድ፣ “መዝገቡ ከቀጠሮ በፊት የቀረበው ይግባኝ ባይ በቀን 10/6/2017 ዓ/ም በተፃፈ አቤቱታ ያቀረዝነው ይግባኝ ታይቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ የፌ/ከፍ/ፍርድ ቤት በወ/መ/ቁ 326384 የሰጠው ውሳኔ ታግዶ እንዲቆይ እንዲታዘዝልን በሚል ባቀረበው አቤቱታ ነው” ይላል።

አክሎም፣ ይግባኝ ቅሬታ ለመስማት ለ20/06/2017 ዓ/ም የተያዘው ቀጠሮ ተሰብሮ የእግድ አቤቱታውን በመመርመር ዝርዝር ትዕዛዝ መስጠቱን ያስረዳል።

የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ አካውንቶች መዘጋታቸው፣ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍስሃ እሸቱ (ዶ/ር) አገር መውጣታቸው አይዘነጋም።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia