TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.13K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
“ የአንድ አዞ ቆዳ አንድ ሴንቲሜትር 5 ዶላር ነው የሚሸጠው ” - የጋሞ ልማት ማኀበር

በተለይ የውጪ አገር የገበያ ትስስር ባለመኖሩ ኢትዮጵያ ከአዞ ሽያጭ እስከ 60 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ገቢ እያጣች መሆኑን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባምንጭ የጋሞ ልማት ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።

ከሦስት ዓመታት በፊት ትንሽ የአዞ ስጋና ቆዳ ለውጪ አገራት ይሸጥ እንደነበር፣ ከዚያ በኋላ በገበያ ትስስር ክፍተት ገቢው በመቀዛቀዙ እንደ አዲስ ለማንሰራራት እየተሰራ መሆኑን ማኀበሩ አስረድቷል።

ስለአዞ ሽያጭ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ የጠየቃቸው የማህበሩ አርባምንጭ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳዊት ዳኘ፣ “ ከ3 አመታት በፊት 10፣ 15 ነበር የሚሸጠው። ከ3000 እስከ 5000 አዞዎች ሲሸጡ የነበረው ከ10 ዓመት በፊት ነው። እየቀሰ መጥቷል ” ብለዋል።

የማኀበሩ ሥራ የአርባምንጭ አስኪያጅ አቶ ዲዊት ዳኘ ምን አሉ ?

“ የአዞ ቆዳ የሽያጭ ሂደቱ ተቀዛቅዞ ቆይቶ አሁን ሽያጭ አልተጀመረም። አሁን በማኀበሩ ተወስዶ እየተሰራ ነው። ቆዳቸው ለሽያጭ የደረሱ ከ2500  በላይ አዞዎች አሉን። እንዴት እንደሚቀጥል ከአገር ውስጥ ካምፓኒዎች ጋር እያወራን ነው።

አሁን ተነጋግረን የውል ሂደት ላይ ነው ያለነው እሱን ጨርሰን ሽያጩ ይካሄዳል ብለን እናስባለን። በፊት ሲሸጥ የነበረው ቆዳው ብቻ ነው። ግን የአዞ ስጋው፣ ጥርሱ፣ ይፈለጋል። ስጋው በሌሎች አገራት በጣም ይፈለጋል።

አሁን 4,000 የአዞ ጫጩቶችን ለመሰብሰብ እንቁላል ዝግጁ ሆኖ ነው ያለው። ከሦስት ወራት በኋላ ጫጩት ከተፈለፈለ በኋላ ከሀይቁ ወደ ማኀበር ይመጣሉ።

የአዞ ቆዳና ስጋ በጣም ዋጋው ውድ ነው። ስለዚህ ትክክለኛ ማርኬት ሊንኬጅ ተፈጥሮ ስርዓቱ ቢዘረጋ እንደ አገር ትልቅ ገቢ እናገኛለን። በተለይ በዘርፉ የሚሰሩ የውጪ አገር ካምፓኒዎችን እያነጋነርን ነው ” ብለዋል።

ከ2,500 በላይ አዞዎች ለሽያጭ ቢቀርቡ ምን ያክል ገቢ ማግኘት ይቻላል ? ስንል የጠየቅናቸው አቶ ዳዊት፣ የአንድ አዞ ቆዳ አንድ ሴንቲሜትር 5 ዶላር እንደሚሸጥ፣ የአንድ አዞ ቆዳ እስከ 45 ሴንቲሜትር እንደሚሆን፣ አንድ አዞ በትንሹ እስከ 22 ሺሕ ብር እንደሚሸጥ፣ በጠቅላላ ከ55 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ሊገኝ እንደሚችል አስረድተዋል።

በማኀበሩ ስንት ሠራተኞች አሉ ? የአዞ ስጋ ምግብነት ላይ ይውላል ወይ ? ለሚለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ አቶ ዳዊት፣ “ የአዞ ስጋ ይበላል። በኛ አልተለመደም። ግን የኛ ሰዎች የ40 ዓመት ልምድ አላቸው። ብራንቹ ተቋቁሞ 41 ዓመቱ ነው። ረጅም ልምድ ያላቸው ሰዎች አዞ የመመገብ ልምድ አላቸው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

አቶ ዳዊትና አንድ የማኀበሩ አስጎብኝ በኢትዮጵያ ብዙ እንዳልተለመደ፣ ኬኒያን ጨምር በሌሎች አካባቢዎች አዞ ለምግብነት እንደሚውል ተናግረዋል።

አቶ ዳዊት፣ “ የአዞ ሬስቶራንት ለመክፈት ” እንዳሰቡ ገልጸው፣ “ ፈረንጆች ይመጣሉ እዚህ ይመገባሉ፤ ቀስ በቀስ የኛ ሰዎችም እያዩ እየተመገቡ ይሄዳሉ ” ነው ያሉት።

አክለው፣ በማኀበሩ ወደ 35 ገደማ ሠራተኞች እንዳሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጹ ሲሆን፣ የማኀበሩ አስጎብኝ በሰጡት ገለጻ ደግሞ፣ “60 በመቶ የሚሆኑት ሰራተኞች የአዞ ስጋ ይመገባሉ” ብለዋል።

አንድ አዞ ለሽያጭ ለመቅረብ ብቁ እስከሚሆን ድረስ 62 ኪሎ ግራም ስጋ እንደሚመገብ፣ አዞ የሚመገበው የአሳ፣ የአዞ ስጋ እንደሆነ፣ አሳማ ሌሎች የእንስሳት ዝርያዎች እንዳሉ፣ የህክምናና ሌሎችን ጨምሮ በአጠቃላይ ማኀበሩ በአመት እስከ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ እንደሚደረግ ተመልክቷል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት #AddisAbaba

ከዛሬ ለሊት 6:00 ሠዓት ጀምሮ እስከ ነገ 7:00 ሠዓት ድረስ መንገዶች ይዘጋሉ።

129ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ነገ ፒያሳ በሚገኘው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ይከበራል።

ይህን ተከትሎ ፦

- በቸርችል ጎዳና በቴዎድሮስ አደባባይ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ባንኮ ዲሮማ መብራት
- ከአራት ኪሎ በራስ መኮንን ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ራስ መኮንን ድልድይ
- ከመነን አካባቢ እና የካቲት 12 ሆስፒታል በአፍንጮ በር ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ አፍንጮ በር
- ከእሪ በከንቱ በኤሌክትሪክ ህንፃ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ደጎል አደባባይ
- ከአዲሱ ገበያ በሰሜን ሆቴል ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ሰሜን መብራት
- ከመርካቶ በአቡነ ጴጥሮስ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ደጃዝማች ሀብተጊዮርጊስ ድልድይ
- ከእንቁላል ፋብሪካ በቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ዮሐንስ መብራት የሚወስዱት መንገዶች ከዛሬ የካቲት 22 ቀን 2017 ዓ/ም ከለሊቱ 6፡00 ሠዓት ጀምሮ እስከ የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 7፡00 ሠዓት ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።

አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።

ህብረተሰቡም ማንኛውም አጠራጣሪ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ በ 011-1-11-01-11 ወይም በነፃ ስልክ መስመር 991 መጠቀም የሚቻል መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

በአዲስ አበባ የተሰማው ከፍተኛ ድምጽ የ129ኛው ዓድዋ ድል በዓልን ምክንያት በማድረግ የተተከሰ የመድፍ ድምፅ ነው።

@tikvahethiopia
#ዓድዋ

እንኳን ለ129ኛው የዓድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ !

" ዓድዋ ዛሬ ናት ዓድዋ ትናንት
መቼ ተነሱና የወዳደቁት
ምስጋና ለእነርሱ ለዓድዋ ጀግኖች
ለዛሬ ነፃነት ላበቁኝ ወገኖች
የጥቁር ድል አምባ ዓድዋ
አፍሪካ እምዬ #ኢትዮጵያ
ተናገሪ
የድል ታሪክሽን አውሪ !!  " - ጂጂ

መልካም የድል በዓል ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ !!

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ዓድዋ እንኳን ለ129ኛው የዓድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ ! " ዓድዋ ዛሬ ናት ዓድዋ ትናንት መቼ ተነሱና የወዳደቁት ምስጋና ለእነርሱ ለዓድዋ ጀግኖች ለዛሬ ነፃነት ላበቁኝ ወገኖች የጥቁር ድል አምባ ዓድዋ አፍሪካ እምዬ #ኢትዮጵያ ተናገሪ የድል ታሪክሽን አውሪ !!  " - ጂጂ መልካም የድል በዓል ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ !! @tikvahethiopia
#ዓድዋ129

ዛሬ የካቲት 23 መላ የኢትዮጵያ ህዝብና ጀግኖች አርበኞች በአንድነት የኢጣሊያንን ቅኝ ገዢ ጦር ዓድዋ ላይ ድል ያደረጉበት በዓል እየተከበረ ይገኛል።

ንጉሰ ነገስት አፄ ሚኒልክ የመሯቸዉ ኢትዮጵያዉን ጀግኖች ኢትዮጵያን የወረረ ጠላታቸዉን ዓድዋ ላይ መትተዉ አሳፍረዉ፣ አዋርደው ፣ አንገት አስደፍተው የመለሱት ልክ በዛሬው ዕለት ከ129 ዓመታት በፊት ነበር።

#ዓድዋ
#የመላአፍሪካውያንድል
#Ethiopia

@tikvahethiopia
#SafaricomEthiopia

ዝግጁ ነሽሽሽሽሽ?? የሳፋሪኮም ቅድሜያ ለሴቶች 5ኬሜ ሩጫ ምዝገባ ጀምሯል M-PESAን ተጠቅመሽ 540 ብር የነበረውን ቲሸርት
በ 389 ብር ብቻ አግኚ!!!
ከM-Pesa ጋር አብረን እንፍጠን። #Andegna #WomensRun #MPESASafaricom
#Earthquake

ዛሬ የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ.ም በዓዲግራት ፣ በዓድዋ፣ ፣ ወቕሮ ፣ መቐለ ጨምሮ በበርካታ የትግራይ አከባቢዎች ከቀኑ 5:30 ጀምሮ ለሰከንዶች የቆየ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዘርት ተከሰተዋል።

የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ድረገጽ ከዓዲግራት 46 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሬክተር ስኬል 5.2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ እንደነበር አመልክቷል።

የመሬት መንቀጥቀጡ ከኢትዮጵያ እና ኤርትራ ድንባር ላይ መከሰቱ ተነግሯል።

@tikvahethiopia
#MoE

" በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ዕጩ ተመራቂዎች የፋይዳ መታወቂያ ሊያወጡ ይገባል " - ትምህርት ሚኒስቴር

የካቲት 21/2017 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተፈርሞ ለሁሉም የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተላከ ሰርኩላር፤ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪ እና የሠራተኞችን መረጃ በተደራጀ መልኩ ለመያዝ ጠቀሜታ እንዳለው ይገልጻል።

የሀገር አቀፍ ፈተናዎችን ደህንነት ለማስጠበቅ አስፈላጊ መሆኑንም ያትታል።

በዚህም በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ዕጩ ተመራቂዎች ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ ሊያወጡ እንደሚገባ / እንደ ቅደመ ሁኔታ መቀመጡን አሳስቧል።

Via
@tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#ነዳጅ የነዳጅ ምርቶች ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል። የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል። አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97…
#ነዳጅ

የነዳጅ ምርቶች ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል።

የመጋቢት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።


አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር

አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር

አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር

የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር

አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97 ብር

አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ 108.30 ብር

#ነዳጅ #ኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ብርሃን_ባንክ
የብርሃን ጉዞጎ ተጠቃሚዎች ብቻ የሚያገኙትን ልዩ ቅናሾች እና ጥቅሞች ያግኙ፣ ይህም ጉዞዎን የበለጠ ተመጣጣኝ እና አስደሳች ያደርገዋል።
👉ደንበኞች በአካል መሄድ ሳያስፈልጋቸው ከ10 በላይ አለም አቀፍ የአየር መንገዶች የበረራ ትኬቶችን ዋጋ ማወዳደር ያስችላል።
👉ደንበኞች በሚመርጡት አየር መንገድ የበረራ ትኬቶች ላይ ቅናሽ ዋጋዎች እንዲያገኙ ያስችላል።
👉ደንበኞች በሚመርጡት ሰዓት እና ዋጋ አስተማማኝ የበረራ ቡኪንግ ለመያዝ ያስችላል።
👉በሁሉም የባንካችን ቅርንጫፎች፣ በሞባይል ወይንም በኢንተርኔት ባንኪንግ ክፍያዎችን መፈጸም ያስችላል፡፡
👉ያለ ተጨማሪ ክፍያ ሳምንቱን ሙሉ ለ 24 ሰዓታት የባለሙያ ምክር እና እርዳታ እንዲያገኙ ያስችላል።
ስለ ብርሃን ጉዞጎ (GuzoGo) አገልግሎት ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት በ0116506355 /0116507425 ወይም በነፃ የጥሪ ማዕከል ቁጥር 8292 ላይ ይደውሉ፤
እንደስማችን ብርሃን ነው ስራችን
#eticket #guzogo #internetbanking #mobilebankingbanking #berhanbank #bank #finance #Stressfreebanking #bankinethiopia
#SafaricomEthiopia

🗺 ሃይኪንግ ላይ ሆናችሁ ዳታ መጠቀም ፈልጋችሁ ታውቃላችሁ? እነሆ አዲስ ቅመም!
💨 የትም ይዛችሁት መሄድ የሚያስችላችሁ እስከ 6 ሰዓት የሚቆይ የባትሪ አቅም ያለውና አዳዲስ የቴክኖሎጂ ትሩፋቶችን ይዞ በአንዴ እስከ 8 ሰው ድረስ የሚያስጠቅመውን ልዩ ቅመም MIFIን ገዝተን ፈጣን 4G ኢንተርኔት እንጠቀም! ለ30 ቀን ከሚቆይ ነጻ 30ጊባ ዳታ ጉርሻ ጋር 😋

ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት
  
🔗 የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

#MPESASafaricom #1Wedefit #Furtheraheadtogether