TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ፦ ይህ በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌ የተከሰተ የመሬት መንሸራተት ነው። ትላንት ቀን 10:30 በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ 1 ሰው ሲሞት ፣ 1 ሰው ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል። 8 የአከባቢው ነዋሪዎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል። በተከሰተው ናዳ አደጋ ህይወቷ ያለፈው የ11 ዓመት ሴት ልጅ ናት። አብራት የነበረችው ወላጅ እናቷ ደግሞ ከአደጋው…
#Alert🚨
" እስካሁን የ11 ሰዎች አክስሬን ተገኝቷል " - የካዎ ኮይሻ ወረዳ
በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌ ዛሬ ረፋድ 5 ሠዓት አካባቢ በተከሰተ የመሬት ናዳ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰምቷል፡፡
በተከሰተው አደጋ እስካሁን በተደረገ ፍለጋ የ11 ሰዎች አስከሬን ተገኝቷል።
የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል የካዎ ኮይሻ ወረዳ አስተዳደር አሳውቋል።
ከቀናት በፊት በዚሁ አካባቢ በተከሰተ የመሬት ናዳ 1 ሰው ህይወቱ ማለፉ እና 1 ሰው ከባድ ጉዳት እንደረሰበት ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከወረዳው ኮሚኒኬሽን ነው ያገኘው።
@tikvahethiopia
" እስካሁን የ11 ሰዎች አክስሬን ተገኝቷል " - የካዎ ኮይሻ ወረዳ
በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌ ዛሬ ረፋድ 5 ሠዓት አካባቢ በተከሰተ የመሬት ናዳ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰምቷል፡፡
በተከሰተው አደጋ እስካሁን በተደረገ ፍለጋ የ11 ሰዎች አስከሬን ተገኝቷል።
የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል የካዎ ኮይሻ ወረዳ አስተዳደር አሳውቋል።
ከቀናት በፊት በዚሁ አካባቢ በተከሰተ የመሬት ናዳ 1 ሰው ህይወቱ ማለፉ እና 1 ሰው ከባድ ጉዳት እንደረሰበት ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከወረዳው ኮሚኒኬሽን ነው ያገኘው።
@tikvahethiopia
#Alert🚨
የዝንጀሮ ፈንጣጣ (MPox) የዓለም አቀፍ አሳሳቢ የህዝብ ጤና ደኅንነት ስጋት (PHEIC) እንደሆነ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ወሰኑ።
የዝንጀሮ ፈንጣጣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) እና በአፍሪካ የሥርጭት መጠኑ እየጨመረ መምጣቱን አሳውቀዋል።
ከዚህ ባለፈ፣ የዝንጀሮ ፈንጣጣን የአፍሪካ ሲዲሲ የህብረተሰብ ጤና አህጉራዊ ደህንነት ስጋት እንደሆነ ገልጿል።
በሌላ በኩል ፤ እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ ውስጥ የተያዘ ሰው #አለመኖሩን የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ዛሬ አመልክቷል።
በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት እና ሞያሌን ጨምሮ በሌሎች የመግቢያ ቦታ ላይ የቁጥጥርና ማጣራት ስራ እየተሰራ ነው።
በሽታው እስካሁን በ13 የአፍሪካ ሀገራት መከሰቱን እንዲሁም፣ 2,863 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው እና 517 ለህልፈት መዳረጋቸዉ መረጋገጡን የአፍሪካ ሲዲሲ መረጃ ያሳያል።
@tikvahethmagazine @tikvahethiopia
የዝንጀሮ ፈንጣጣ (MPox) የዓለም አቀፍ አሳሳቢ የህዝብ ጤና ደኅንነት ስጋት (PHEIC) እንደሆነ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ወሰኑ።
የዝንጀሮ ፈንጣጣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) እና በአፍሪካ የሥርጭት መጠኑ እየጨመረ መምጣቱን አሳውቀዋል።
ከዚህ ባለፈ፣ የዝንጀሮ ፈንጣጣን የአፍሪካ ሲዲሲ የህብረተሰብ ጤና አህጉራዊ ደህንነት ስጋት እንደሆነ ገልጿል።
በሌላ በኩል ፤ እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ ውስጥ የተያዘ ሰው #አለመኖሩን የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ዛሬ አመልክቷል።
በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት እና ሞያሌን ጨምሮ በሌሎች የመግቢያ ቦታ ላይ የቁጥጥርና ማጣራት ስራ እየተሰራ ነው።
በሽታው እስካሁን በ13 የአፍሪካ ሀገራት መከሰቱን እንዲሁም፣ 2,863 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው እና 517 ለህልፈት መዳረጋቸዉ መረጋገጡን የአፍሪካ ሲዲሲ መረጃ ያሳያል።
@tikvahethmagazine @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Alert🚨 የዝንጀሮ ፈንጣጣ (MPox) የዓለም አቀፍ አሳሳቢ የህዝብ ጤና ደኅንነት ስጋት (PHEIC) እንደሆነ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ወሰኑ። የዝንጀሮ ፈንጣጣ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) እና በአፍሪካ የሥርጭት መጠኑ እየጨመረ መምጣቱን አሳውቀዋል። ከዚህ ባለፈ፣ የዝንጀሮ ፈንጣጣን የአፍሪካ ሲዲሲ የህብረተሰብ ጤና አህጉራዊ ደህንነት ስጋት እንደሆነ…
#Alert🚨
ከተ.መ.ድ የጤና ኤጀንሲ እንደተገኘው መረጃ በቅርቡ ኤምፖክስ (Mpox) ለመጀመሪያ ጊዜ በ4 የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማለትም ፦
- በጎረቤታችን ኬንያ ፣
- በቡሩንዲ ፣
- በሩዋንዳ
- በኡጋንዳ ተገኝቷል። ሀገራቱም ሪፖርት አድርገዋል። በነዚህ ሀገራት ውስጥ የታየው በሽታ በኮንጎ ካለው ጋር የተገናኘ ነው።
የዝንጀሮ ፈንጣጣ ወይም Mpox በሽታ የሚከሰተው በቫይረስ አማካኝነት ነው።
ከሰው ወደ ሰው ይተላለፋል። በወሲባዊ ግንኙነት ፣ በቆዳ ንክኪ ፣ በቅርብ ርቀት ሆኖ ማውራት/ መተንፈስ ፣ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ባለ የቅርብ ግንኙነት ይተላለፋል።
አሁን ላይ #ዋነኛዎቹ ናቸው የሚባሉት ሁለቱ የቫይረሱ ዝርያዎች Clade 1 - በማእከላዊ አፍሪካ ውስጥ ያለ ፤ Clade 1b - እጅግ በጣም አደገኛ የሆነው አዲስ የቫይረሱ ዝርያ ነው።
@tikvahethiopia
ከተ.መ.ድ የጤና ኤጀንሲ እንደተገኘው መረጃ በቅርቡ ኤምፖክስ (Mpox) ለመጀመሪያ ጊዜ በ4 የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማለትም ፦
- በጎረቤታችን ኬንያ ፣
- በቡሩንዲ ፣
- በሩዋንዳ
- በኡጋንዳ ተገኝቷል። ሀገራቱም ሪፖርት አድርገዋል። በነዚህ ሀገራት ውስጥ የታየው በሽታ በኮንጎ ካለው ጋር የተገናኘ ነው።
የዝንጀሮ ፈንጣጣ ወይም Mpox በሽታ የሚከሰተው በቫይረስ አማካኝነት ነው።
ከሰው ወደ ሰው ይተላለፋል። በወሲባዊ ግንኙነት ፣ በቆዳ ንክኪ ፣ በቅርብ ርቀት ሆኖ ማውራት/ መተንፈስ ፣ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ባለ የቅርብ ግንኙነት ይተላለፋል።
አሁን ላይ #ዋነኛዎቹ ናቸው የሚባሉት ሁለቱ የቫይረሱ ዝርያዎች Clade 1 - በማእከላዊ አፍሪካ ውስጥ ያለ ፤ Clade 1b - እጅግ በጣም አደገኛ የሆነው አዲስ የቫይረሱ ዝርያ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Omo የኦሞ ወንዝ ሙላት ከቁጥጥር ውጭ መሆኑን ተከትሎ የአካባቢው አርሶአደር በ4ቱም አቅጣጫ ንብረቱን ጥሎ መሸሽ ላይ ነው። ችግሩ እንደሚከሰት ታውቆ በርካታ ስራ ሲሰራ ቢቆይም የኦሞ ወንዝ መጠን ከተለመደውና ከታሰበው ውጭ መሆኑን ተከትሎ ግን ለዞኑ መንግስትም ሆነ ለግብረሰናይ ድርጅቶች ሁኔታው ከባድ ሆኖባቸዋል። የወንዙ ሙላት ከባድ መሆኑን በመግለጽ አሁን ላይ አርብቶ አደሩን በአራት ጊዜያዊ…
#ALERT🚨
⚠️ " በውሀ ተውጠን ከማለቃችን በፊት ድረሱልን " - የኦሞራቴ ከተማ ነዋሪዎች
🔴 " የውሀው አመጣጥ እጅግ አስፈሪ ነው ፤ የፌደራል መንግስት ማሽነሪዎች ቶሎ እንዲያቀርብልን እየጠየቅን ነው " - የአካባቢዉ አስተዳደር
የኦሞ ወንዝ መሙላቱን ተከትሎ ሀብት ንብረቴ የሚላቸዉ ከብቶች ማለቁን ያየዉ የደቡብ ኦሞ አርብቶ አደር በአራቱም አቅጣጫ እየተሰደደ መሆኑን ጠቅሰን አካባቢው ትኩረት ይሻል ስንል ከቀናት በፊት መዘገባችን ይታወሳል።
ይሁንና አሁን ላይ የኦሞ ወንዝ ከአቅም በላይ በመሙላቱና የአካባቢዉ መሬት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ መተኛቱን ተከትሎ የወረዳዉ ዋና ከተማ የሆነችዉን ኦሞራቴን ደሴት ሲያደርጋት ህዝቡም መዉጫ በማጣት ጭንቀት ውስጦ መግባቱን ሰምተናል።
የድረሱልን ጥሪያቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያደረሱት የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚገልጹት ለአመታት በወንዙ ሙላት ሲቸገሩ መቆየታቸውንና አሁን ግን ከርቀት ወደምትገኘው ኦሞራቴ ከተማ በእጅጉ መጠጋቱ እንዳስደነገጣቸው በመግለጽ ከመዋጣቸው በፊት የሚመለከተዉ አካል እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል።
በአካባቢው የነበሩት አርብቶ አደሮች በበኩላቸው ሙሉ በሙሉ የግጦሽ መሬቶች በወንዙ ተቆርሶ መወሰዱንና ከብቶቻቸው ማለቃቸውን ገልጸዉ አሁን ላይ የተጠለሉባቸው ጊዜያዊ መጠለያዎች በውሀው እየተጥለቀለቁ በመሆኑ ህይወታቸዉ አደጋ ላይ መውደቁን አስተድተዋል።
ስለሁኔታዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስተያየታቸውን የሰጡን የወረዳዉ አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ " የዉሀዉ አመጣጥ እጅግ አስፈሪ ነው " ብለዋል።
ማህበረሰቡ አፈር በማዳበሪያ እየቋጠረ ግድብ መስራቱ ውሀውን ስላላስቆመው የፌደራል መንግስት ማሽነሪዎች ቶሎ እንዲያቀርብልን እየጠየቅን ብለዋል።
" አሁን ላይ የኦሞራቴ ከተማ ከጊዜያዊ መጠለያዎችም ሆነ ራቅ ካሉ አካባቢዎች ለመገናኘትም ሆነ ለመሸሽ ቱርሚን የሚያገናኘዉ ድልድይ በመሰበሩና ወደኬኒያ የሚወስደዉ ዋና መንገድ በውሀው ክራክ በማድረጉ ደሴት ሆናል " ሲሉ ገልጸዋል።
በመሆኑም " የኦሞራቴ ህዝብ የከፋ ችግር ላይ በመሆኑ የሚመለከተው አካል አፋጣኝ ድጋፍ ሊያደርግለት ይገባል ሲሉ " ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
🔴 " የውሀው አመጣጥ እጅግ አስፈሪ ነው ፤ የፌደራል መንግስት ማሽነሪዎች ቶሎ እንዲያቀርብልን እየጠየቅን ነው " - የአካባቢዉ አስተዳደር
የኦሞ ወንዝ መሙላቱን ተከትሎ ሀብት ንብረቴ የሚላቸዉ ከብቶች ማለቁን ያየዉ የደቡብ ኦሞ አርብቶ አደር በአራቱም አቅጣጫ እየተሰደደ መሆኑን ጠቅሰን አካባቢው ትኩረት ይሻል ስንል ከቀናት በፊት መዘገባችን ይታወሳል።
ይሁንና አሁን ላይ የኦሞ ወንዝ ከአቅም በላይ በመሙላቱና የአካባቢዉ መሬት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ መተኛቱን ተከትሎ የወረዳዉ ዋና ከተማ የሆነችዉን ኦሞራቴን ደሴት ሲያደርጋት ህዝቡም መዉጫ በማጣት ጭንቀት ውስጦ መግባቱን ሰምተናል።
የድረሱልን ጥሪያቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያደረሱት የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚገልጹት ለአመታት በወንዙ ሙላት ሲቸገሩ መቆየታቸውንና አሁን ግን ከርቀት ወደምትገኘው ኦሞራቴ ከተማ በእጅጉ መጠጋቱ እንዳስደነገጣቸው በመግለጽ ከመዋጣቸው በፊት የሚመለከተዉ አካል እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል።
በአካባቢው የነበሩት አርብቶ አደሮች በበኩላቸው ሙሉ በሙሉ የግጦሽ መሬቶች በወንዙ ተቆርሶ መወሰዱንና ከብቶቻቸው ማለቃቸውን ገልጸዉ አሁን ላይ የተጠለሉባቸው ጊዜያዊ መጠለያዎች በውሀው እየተጥለቀለቁ በመሆኑ ህይወታቸዉ አደጋ ላይ መውደቁን አስተድተዋል።
ስለሁኔታዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስተያየታቸውን የሰጡን የወረዳዉ አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ " የዉሀዉ አመጣጥ እጅግ አስፈሪ ነው " ብለዋል።
ማህበረሰቡ አፈር በማዳበሪያ እየቋጠረ ግድብ መስራቱ ውሀውን ስላላስቆመው የፌደራል መንግስት ማሽነሪዎች ቶሎ እንዲያቀርብልን እየጠየቅን ብለዋል።
" አሁን ላይ የኦሞራቴ ከተማ ከጊዜያዊ መጠለያዎችም ሆነ ራቅ ካሉ አካባቢዎች ለመገናኘትም ሆነ ለመሸሽ ቱርሚን የሚያገናኘዉ ድልድይ በመሰበሩና ወደኬኒያ የሚወስደዉ ዋና መንገድ በውሀው ክራክ በማድረጉ ደሴት ሆናል " ሲሉ ገልጸዋል።
በመሆኑም " የኦሞራቴ ህዝብ የከፋ ችግር ላይ በመሆኑ የሚመለከተው አካል አፋጣኝ ድጋፍ ሊያደርግለት ይገባል ሲሉ " ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#ALERT🚨 ⚠️ " በውሀ ተውጠን ከማለቃችን በፊት ድረሱልን " - የኦሞራቴ ከተማ ነዋሪዎች 🔴 " የውሀው አመጣጥ እጅግ አስፈሪ ነው ፤ የፌደራል መንግስት ማሽነሪዎች ቶሎ እንዲያቀርብልን እየጠየቅን ነው " - የአካባቢዉ አስተዳደር የኦሞ ወንዝ መሙላቱን ተከትሎ ሀብት ንብረቴ የሚላቸዉ ከብቶች ማለቁን ያየዉ የደቡብ ኦሞ አርብቶ አደር በአራቱም አቅጣጫ እየተሰደደ መሆኑን ጠቅሰን አካባቢው ትኩረት ይሻል…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Alert🚨
ኦሞ ወንዝ በከፍተኛ ሁኔታ በመሙላቱ የወንዙ ውሃ እና የቱርካና ሀይቅ ይዞታውን እያሰፋ በመሆኑ በኦሞራቴ ከተማ በ1.9 ኪ/ሜ ርቀት አከባቢ በተለያዩ ቦታዎች የመሬት መሰንጠቅ እዲሁም ውሃው ውስጥ ለውስጥ እየሄደ በመሆኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopia
ኦሞ ወንዝ በከፍተኛ ሁኔታ በመሙላቱ የወንዙ ውሃ እና የቱርካና ሀይቅ ይዞታውን እያሰፋ በመሆኑ በኦሞራቴ ከተማ በ1.9 ኪ/ሜ ርቀት አከባቢ በተለያዩ ቦታዎች የመሬት መሰንጠቅ እዲሁም ውሃው ውስጥ ለውስጥ እየሄደ በመሆኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ለመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት የሆነው ቅልጥ አለት መሬት ውስጥ መምጣቱ ነው " - ኤልያስ ሌዊ (ዶ/ር) ዛሬ ጠዋት 1 ሰዓት ከ37 ደቂቃ ከ50 ሴኮንድ ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። ቦታው ባለፈው በተከሰተበት አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ ሲሆን በሬክተር ስኬል 4.6 አካባቢ እነደሆነ ተገልጿል። የዛሬው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት አዲስ አበባ ድረስ በደንብ ተሰምቷል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስና…
#Alert🚨
ከደቂቃዎች በፊት በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች የመሬት መንቀጥቀጥ ንዘረት እንደሰሙ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ጠቁመዋል።
" በተለይም ፎቅ ላይ በደንብ ይታወቅ ነበር " ብለዋል።
ጎተራ፣ አያት ፣ ባልደራስ ፣ ሰሚት ፣ መካኒሳ ፣ ጀሞ ፣ ኮዬ ፣ ጣፎ ፣ ቱሉ ዲምቱ ፣ ጦር ኃይሎች ፣ ቀጨኔ፣ ጎፋ ... እንዲሁም ከሌሎች በርካታ አካባቢዎች ቲክቫህ ኢትዮጵያ ንዝረቱ መሰማቱን የሚመለከቱ መልዕክቶችን ተቀብሏል።
ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት በቀናት ውስጥ ለሶስተኛ ጊዜ ነው።
ሰሞኑን በአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ እየተከሰተ መሆኑ ይታወቃል።
ይህም የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ አዲስ አበባ እና ሌሎች ከተሞች ድረስ እየተሰማ ነው።
@tikvahethiopia
ከደቂቃዎች በፊት በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች የመሬት መንቀጥቀጥ ንዘረት እንደሰሙ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ጠቁመዋል።
" በተለይም ፎቅ ላይ በደንብ ይታወቅ ነበር " ብለዋል።
ጎተራ፣ አያት ፣ ባልደራስ ፣ ሰሚት ፣ መካኒሳ ፣ ጀሞ ፣ ኮዬ ፣ ጣፎ ፣ ቱሉ ዲምቱ ፣ ጦር ኃይሎች ፣ ቀጨኔ፣ ጎፋ ... እንዲሁም ከሌሎች በርካታ አካባቢዎች ቲክቫህ ኢትዮጵያ ንዝረቱ መሰማቱን የሚመለከቱ መልዕክቶችን ተቀብሏል።
ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት በቀናት ውስጥ ለሶስተኛ ጊዜ ነው።
ሰሞኑን በአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ እየተከሰተ መሆኑ ይታወቃል።
ይህም የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ አዲስ አበባ እና ሌሎች ከተሞች ድረስ እየተሰማ ነው።
@tikvahethiopia
#Alert🚨
ከመቐለ ወደ ዓዲግራት የሚወሰደው ዋና የመኪና መንገድ አጉላዕ በተባለ ቦታ መዘጋቱ ተጓዦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" መንገዱ ከዲሞብላይዜሽን (DDR) ጋር በተያያዘ ጥያቄ ባነሱ የቀድሞ የትግራይ ታዋጊ አባላት ነው የተዘጋው " ብለዋል።
ጥያቄው በዝርዝር ምን እንደሆነ የሚታወቅ ነገር የለም።
መንገዱ ከዛሬ ታህሳስ 1/2017 ዓ.ም ጠዋት ጀምሮ ይህ መረጃ እስከወጣበት ከቀኑ 7:00 ድረስ ተዘግቷል።
መንገዱ በመዘጋቱ ምክንያት ከመቐለ የተነሱ መኪኖች 40 ኪሎ ሜትር ከተጓዙ በኋላ አጉላዕ ከተማ ደርሰው ወደ ውቕሮ ዓዲግራት እና ሌሎች ቦታዎች ማለፍ አይችሉም።
ከዓዲግራት ፣ ወቕሮ እና ሌሎች ከተሞች የመጡት ደግሞ አጉላዕ ደርሰው ወደ መቐለ ከተማ ማለፍ አይችሉም ብለዋል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ መንገደኞች።
ተጓዦች መንገዱ በመዘጋቱ ምክንያት ለከፍተኛ እንግልት መጋለጣቸው ገልፀው ፤ እስካሁን መንገዱን የዘጉትን የቀድሞ ተዋጊዎች አባላትን ጥያቄ ሰምቶ መልስ የሰጣቸው የለም ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ጉዳዩ ተከታትሎ ያለውን መረጃ እንደሚያቀርብ ከወዲሁ ይጠቁማል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
ከመቐለ ወደ ዓዲግራት የሚወሰደው ዋና የመኪና መንገድ አጉላዕ በተባለ ቦታ መዘጋቱ ተጓዦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" መንገዱ ከዲሞብላይዜሽን (DDR) ጋር በተያያዘ ጥያቄ ባነሱ የቀድሞ የትግራይ ታዋጊ አባላት ነው የተዘጋው " ብለዋል።
ጥያቄው በዝርዝር ምን እንደሆነ የሚታወቅ ነገር የለም።
መንገዱ ከዛሬ ታህሳስ 1/2017 ዓ.ም ጠዋት ጀምሮ ይህ መረጃ እስከወጣበት ከቀኑ 7:00 ድረስ ተዘግቷል።
መንገዱ በመዘጋቱ ምክንያት ከመቐለ የተነሱ መኪኖች 40 ኪሎ ሜትር ከተጓዙ በኋላ አጉላዕ ከተማ ደርሰው ወደ ውቕሮ ዓዲግራት እና ሌሎች ቦታዎች ማለፍ አይችሉም።
ከዓዲግራት ፣ ወቕሮ እና ሌሎች ከተሞች የመጡት ደግሞ አጉላዕ ደርሰው ወደ መቐለ ከተማ ማለፍ አይችሉም ብለዋል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ መንገደኞች።
ተጓዦች መንገዱ በመዘጋቱ ምክንያት ለከፍተኛ እንግልት መጋለጣቸው ገልፀው ፤ እስካሁን መንገዱን የዘጉትን የቀድሞ ተዋጊዎች አባላትን ጥያቄ ሰምቶ መልስ የሰጣቸው የለም ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ጉዳዩ ተከታትሎ ያለውን መረጃ እንደሚያቀርብ ከወዲሁ ይጠቁማል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Earthquake : ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ የተሰማ የመሬት መንቀጥቀጥ አዋሽ አካባቢ ተከስቶ ነበር። በርካታ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት መንቀጥቀጡ እና ንዝረቱ ከእንቅልፋቸው እንደቀሰቀሳቸውና ጠንክሮ እንደተሰማቸው መልዕክት ልከዋል። በተለይ አዲስ አበባ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ላይ ጠንከር ብሎ ንዝረቱ ተሰምቷል። ከንዝረቱ ጋር በተያያዘ መልዕክት የላከ የቤተሰባችን አባል ፥…
🚨 #Alert
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ተከስቶ የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ ከአዋሽ 23 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ሲሆን የጀርመኑ የጂኦሳይንስ ሪሰርች ማዕከል መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 5.0 መመዝገቡን አሳውቋል።
የአሜሪካ ጃኦሎጂካል ሰርቬይ ደግሞ በሬክተር ስኬል 4.9 መለካቱን አመላክቷል።
ንዝረቱ አዲስ አበባ የተለያዩ ሰፈሮች ተሰምቷል።
@tikvahethiopia
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ተከስቶ የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ ከአዋሽ 23 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ሲሆን የጀርመኑ የጂኦሳይንስ ሪሰርች ማዕከል መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 5.0 መመዝገቡን አሳውቋል።
የአሜሪካ ጃኦሎጂካል ሰርቬይ ደግሞ በሬክተር ስኬል 4.9 መለካቱን አመላክቷል።
ንዝረቱ አዲስ አበባ የተለያዩ ሰፈሮች ተሰምቷል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የትግራይ ጉዳይ ወዴት ? በትግራይ ክልል ያሉ የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች እንደሆኑ የገለጹ መኮንኖች ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር። በዚህም ' የተዳከመ ' ያሉት በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ተነስቶ በሌላ እንዲዋቀር መወሰናቸውን ገልጸዋል። " የጊዜያዊ አስተዳደሩ እንደ አዲስ እንዲዋቀር ውሳኔ አሳልፈናል " ብለዋል። " በፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት የተቋቋመው የትግራይ…
🚨#Alert
" የወጣው መግለጫ ግልፅ የሆነ መፈንቀለ መንግስት ያወጀ እና የፕሪቶሪያውን ውል ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው ! " - የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር
" ህጋዊ ያልሆነ ቡድን ደግፎ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለማፍረስ ፤ ስርዓት አልበኝነት ለማስፈን እና ሰራዊቱን ለመበተን መንቀሳቀስ ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ " የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አስታወቀ።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ ዛሬ ጥር 15/2017 ዓ.ም በትግራይ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮች ስም የወጣው መግለጫ አላማውን የሳተ እና ሰራዊቱ ከተሰጠው ተልእኮ ውጭ ነው ብሏል።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ ፤ " በሰራዊት ከፍተኛ አዣዦች ስም የወጣው መግለጫ እንደማያውቀው በማንኛውም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው ያልተለመደ ተግባር ነው " ብሎታል።
የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ " ያልተለመደ ተግባር " ሲል የገለፀውን ውሳኔ አስመልክቶ ለመወያየት አስቸኳይ ስብሰባ መጥራቱን እና ሁኔታውን መርምሮ ዝርዝር ማብራርያ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።
" በከፍተኛ የሰራዊት አዛዦች ስም የወጣው መግለጫ ግልፅ የሆነ መፈንቀለ መንግስት ያወጀ እና የፕሪቶሪያውን ውል ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው " ብሏል ጊዚያዊ አስተዳደሩ።
" ሃላፊነት የጎደለውን ውሳኔው ወደ ታች ለማውረድ ጥድፍያ የተሞላበት እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ መሆኑ ደርሼቤታለሁ " ያለው የጊዚያዊ አስተዳደሩ " የሚያስከትለው አደጋው እጅግ ከፍተኛ መሆኑ በመረዳት ተግባሩ በአስቸኳይ መቆም አለበት " ሲል አስጠንቅቋል።
" መላው የፀጥታ አካላት ህገ-ወጥ ውሳኔው የህዝቡን ችግር የሚያባብስ የጦርነት አዋጅ እና ስርዓት አልበኝነት የሚያስከትል መሆኑ በመገንዘብ በፅናት እንድትቃወሙት ትእዛዙን ተግባራዊ እንዳታደርጉ አስታውቃለሁ " ሲልም አክሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" የወጣው መግለጫ ግልፅ የሆነ መፈንቀለ መንግስት ያወጀ እና የፕሪቶሪያውን ውል ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው ! " - የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር
" ህጋዊ ያልሆነ ቡድን ደግፎ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለማፍረስ ፤ ስርዓት አልበኝነት ለማስፈን እና ሰራዊቱን ለመበተን መንቀሳቀስ ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ " የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አስታወቀ።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ ዛሬ ጥር 15/2017 ዓ.ም በትግራይ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮች ስም የወጣው መግለጫ አላማውን የሳተ እና ሰራዊቱ ከተሰጠው ተልእኮ ውጭ ነው ብሏል።
ጊዚያዊ አስተዳደሩ ፤ " በሰራዊት ከፍተኛ አዣዦች ስም የወጣው መግለጫ እንደማያውቀው በማንኛውም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው ያልተለመደ ተግባር ነው " ብሎታል።
የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ " ያልተለመደ ተግባር " ሲል የገለፀውን ውሳኔ አስመልክቶ ለመወያየት አስቸኳይ ስብሰባ መጥራቱን እና ሁኔታውን መርምሮ ዝርዝር ማብራርያ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።
" በከፍተኛ የሰራዊት አዛዦች ስም የወጣው መግለጫ ግልፅ የሆነ መፈንቀለ መንግስት ያወጀ እና የፕሪቶሪያውን ውል ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው " ብሏል ጊዚያዊ አስተዳደሩ።
" ሃላፊነት የጎደለውን ውሳኔው ወደ ታች ለማውረድ ጥድፍያ የተሞላበት እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ መሆኑ ደርሼቤታለሁ " ያለው የጊዚያዊ አስተዳደሩ " የሚያስከትለው አደጋው እጅግ ከፍተኛ መሆኑ በመረዳት ተግባሩ በአስቸኳይ መቆም አለበት " ሲል አስጠንቅቋል።
" መላው የፀጥታ አካላት ህገ-ወጥ ውሳኔው የህዝቡን ችግር የሚያባብስ የጦርነት አዋጅ እና ስርዓት አልበኝነት የሚያስከትል መሆኑ በመገንዘብ በፅናት እንድትቃወሙት ትእዛዙን ተግባራዊ እንዳታደርጉ አስታውቃለሁ " ሲልም አክሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
🚨#Alert
ከደቂቃዎች በፊት ከፍ ያለ የመሬት መንቀጥቀጥ አዋሽ አካባቢ ተከስቷል።
ንዝሩት በአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች ተሰምቷል።
ቃላቸውን የላኩልን የቤተሰባች አባላት " ዛሬ በጣም የሚያስፈራ ነበር። ሰሞኑን ድግግሞሹ ቀንሶ ነበር። ዛሬ በድንገት በሚያስፈራ ሁኔታ ነው የተሰማን " ብለዋል።
@tikvahethiopia
ከደቂቃዎች በፊት ከፍ ያለ የመሬት መንቀጥቀጥ አዋሽ አካባቢ ተከስቷል።
ንዝሩት በአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች ተሰምቷል።
ቃላቸውን የላኩልን የቤተሰባች አባላት " ዛሬ በጣም የሚያስፈራ ነበር። ሰሞኑን ድግግሞሹ ቀንሶ ነበር። ዛሬ በድንገት በሚያስፈራ ሁኔታ ነው የተሰማን " ብለዋል።
@tikvahethiopia
🚨 #ALERT
አሁን ከደቂቃዎች በፊት በርካቶችን ከተኙበት የቀሰቀሰቀሰ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል።
ንዝረቱ በአዲስ አበባ እና የተለያዩ ከተሞች ከፍ ብሎ ተሰምቷል።
መልዕክታቸውን የላኩ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት " የዛሬው ንዝረት ከእስካሁኑ የተለየና የሚያስደነግጥ ነበር " ሲሉ ገልጸዋል።
በርካቶችም በንዝረቱ ምክንያት ከእንቅልፍ መባነናቸውን ጠቁመዋል።
@tikvahethiopia
አሁን ከደቂቃዎች በፊት በርካቶችን ከተኙበት የቀሰቀሰቀሰ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል።
ንዝረቱ በአዲስ አበባ እና የተለያዩ ከተሞች ከፍ ብሎ ተሰምቷል።
መልዕክታቸውን የላኩ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት " የዛሬው ንዝረት ከእስካሁኑ የተለየና የሚያስደነግጥ ነበር " ሲሉ ገልጸዋል።
በርካቶችም በንዝረቱ ምክንያት ከእንቅልፍ መባነናቸውን ጠቁመዋል።
@tikvahethiopia