TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" የተማሪዎች ዕለታዊ የምግብ ተመን ወጪ 100 በሆነበት ማግስት አንድ ዳቦ ለቁርስ ማቅረብ ማሻሻል አይደለም " -የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች
በትላንትናው ዕለት በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ከተሻሻለው የምግብ ሜኑ ጋር በተያያዘ በዩኒቨርሲቲው የተፈጠረ ግርግር ለተማሪዎች መጎዳት እና ለንብረት ውድመት ምክንያት መሆኑ ተሰምቷል።
ለአለመግባባቱ መነሻ የሆነው በትምህርት ሚኒስቴር በተሻሻለው እና በሁሉም የዩኒቨርሲቲዎች ወጥነት ያለው የምግብ ሜኑ እንዲኖር የሚያዘውን መመሪያ ተከትሎ " ዩኒቨርሲቲው አግባብ ባልሆነ መንገድ ተግባራዊ እያደረገው ነው " በሚል ነው።
ዩኒቨርስቲው ከቅዳሜ 12/04/2017 ዓ/ም ጀምሮ አንድ ዳቦ ለቁርስ እየቀረበ እንደሚገኝ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" ከዚህ በፊት ለዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ዕለታዊ ለቁርስ ይቀርብልን የነበረው ዳቦ ምንም እንኳን መጠኑ በጣም አነስተኛ ቢሆንም ሁለት ነበር አሁን ግን የተማሪዎች ዕለታዊ የምግብ ተመን ወጪ 100 በሆነበት ማግስት አንድ ዳቦ ለቁርስ ማቅረብ ማሻሻል አይደለም " ሲሉ ወቅሰዋል።
በዚህ የምግብ አቅርቦት ደስተኛ ያልሆኑ የዋና ግቢ እና የዓዲ ሓቂ ግቢ ተማሪዎች ድርጊቱን በመቃወማቸው ለድብደባ እና ለእስር መዳረጋቸውን ገልጸዋል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ በመቐለ ዩኒቨርስቲ የአሪድ የተማሪዎች ምግብ ቤት ሰራተኛን አነጋግሯል።
እኚሁ ሰራተኛ ፤ " ግርግሩ በቁርስ ሰዓት ነበር የጀመረው ተማሪዎቹ በቁርስ ሰዓት ሲቅርብላቸው የነበረው ሁለት ዳቦ ግራሙ ጨምሯል በማለት አንድ ዳቦ እንዲሰጣቸው ተደረገ ተማሪዎቹ ዳቦው አንድ መሆኑን እና የተጨመረ ግራም እንደሌለ ተናግረው የዩኒቨርስቲው አመራሮች እንዲያነጋግሩዋቸው ጠየቁ " በማለት የጉዳዩን መነሻ አብራርተዋል።
" ይሁን እንጂ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት መልስ ባለመስጠታቸው የተቆጡ ተማሪዎች የምግብ ጠረጴዛዎችን ፣ የምግብ ቁሳቁሶችን ፣ መስታወቶችን እና ሌሎች ነገሮች ወደ መስበር ተሸጋግረዋል በምግብ ቤቱ ሰራተኞች ላይ ግን ያደረሱት ጉዳት የለም " ብለዋል።
በቁርስ ሰዓት በአሪድ ካምፓስ የጀመረው ግርግር ወደ ዓዲ ሓቂ ካምፓስ በመዝለቅ እስከ እራት ሰዓት ድረስ በዩኒቨርስቲ ንብረቶች ላይ ውድመት መድረሱን ተገልጿል።
የክልሉ ፓሊስ ኮሚሽን ወደ ካምፓሶቹ የፀጥታ አካላት መላኩ ተነግሯል።
በዚህም ሳቢያ በፓሊስ እና በተማሪዎቹ መካከል በተፈጠረ ግጭት ተማሪዎች የድብደባ ጥቃት እንደደረሰባቸው ተነግሯል።
በሁለቱ ካምፓሶች ግን ለጊዜው ግምቱ ያልተጣራ ንብረት መውደሙን ለመረዳት ተችሏል።
በመቐለ ዩኒቨርስቲ አሪድ እና ዓዲ ሓቂ ካምፓሶች የተፈጠረው ግርግር በአሁኑ ሰዓት ሙሉ በሙሉ ቆሟል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የዩኒቨርስቲውን የኮሙኒኬሽን ኮርፓሬት ስለ ተፈጠረው ግርግር ማብራርያ እንዲስጥ ያቀረበው ጥያቄ " የጉዳዩ መነሻ እና መድረሻ የሚመለከት ይፋዊ መግለጫ በሚድያ እስከሚሰጥ ጠብቁ የሚል " ምላሽ ተሰጥቶታል።
በኃላም ተቋሙ ማብራሪያ አውጥቷል።
በዚህም ፦
- በሃገር ደረጃ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሃገራዊ የምግብ ሜኑ በትምህርት ሚኒስቴር ጸድቆ ለትግበራ መላኩን ገልጿል።
- ዩኒቨርሲቲው ከተማሪዎች ህብረት ጋር በመነጋገር የመቐለ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች የምግብ ሜኑን አዘጋጅቶ ወደ ትግበራ መግባቱን አመልክቷል።
- በሜኑው ላይ የሚስተካከሉ ነገሮች ካሉ ብሄራዊ ሜኑ በይዘት እና በጀት ደረጃ እስካልተለየ ድረስ ጥያቄዎች በተማሪዎች ህብረት በኩል ቀርበው ማስተካከል እንደሚቻል አመልክቷል።
- በሃገር ደረጃ ተግባራዊ የሆነውን የምግብ ሜኑ ተቃውሞ የዩኒቨርሲቲውን መሰረተልማት ማጥፋት እና የካፊተርያ እና የጥበቃ ሰራተኞች ላይ ጉዳት ማድረስ ተማሪዎችን እንዲሁም ማህበረሰቡን እና ሃገሪቱን የሚጎዳና ተግባር እንደሆነ ገልጿል።
- ተማሪዎች ቅሬታቸውን በሰላማዊ መንገድ መግለጽ እንዳለባቸው አሳስቧል።
ጉዳዩን በተመለከተ የመቐለ ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች ህብረት የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ያቀረቧቸው ጥያቄዎች ትክክለኛ ስለመሆናቸው የሚገልጽ የአቋም መግለጫ አውጥቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው የአቋም መግለጫ ከሚመለከታቸው የማኔጅመንት አካላት ጋር በተደረገ ውይይት ያለኣግባብ የታሰሩ ተማሪዎች እንዲፈቱ እና ያለ መረጃ በተማሪዎች ላይ እርምጃ እንዳይወሰድ መወያየታቸውን ይገልጻል።
በተጨማሪም አዲሱ ሜኑ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ እስከሚሆን ድረስ በነባሩ ሜኑ እንዲቀጥል ከመግባባት ላይ መደረሱን ገልጿል።
ህብረቱ ለተማሪዎች ሰላማዊ ጥያቄ ከተማሪዎች ጎን እንደሚቆም ይሁን እንጂ በዋና ግቢ ካፍቴሪያ እና በኣዲ ሓቂ ተማሪዎች ላይ የደረሰው ጉዳት እና ስህተት ፈጽሞ መደገም የለበትም ብሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
በትላንትናው ዕለት በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ከተሻሻለው የምግብ ሜኑ ጋር በተያያዘ በዩኒቨርሲቲው የተፈጠረ ግርግር ለተማሪዎች መጎዳት እና ለንብረት ውድመት ምክንያት መሆኑ ተሰምቷል።
ለአለመግባባቱ መነሻ የሆነው በትምህርት ሚኒስቴር በተሻሻለው እና በሁሉም የዩኒቨርሲቲዎች ወጥነት ያለው የምግብ ሜኑ እንዲኖር የሚያዘውን መመሪያ ተከትሎ " ዩኒቨርሲቲው አግባብ ባልሆነ መንገድ ተግባራዊ እያደረገው ነው " በሚል ነው።
ዩኒቨርስቲው ከቅዳሜ 12/04/2017 ዓ/ም ጀምሮ አንድ ዳቦ ለቁርስ እየቀረበ እንደሚገኝ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" ከዚህ በፊት ለዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ዕለታዊ ለቁርስ ይቀርብልን የነበረው ዳቦ ምንም እንኳን መጠኑ በጣም አነስተኛ ቢሆንም ሁለት ነበር አሁን ግን የተማሪዎች ዕለታዊ የምግብ ተመን ወጪ 100 በሆነበት ማግስት አንድ ዳቦ ለቁርስ ማቅረብ ማሻሻል አይደለም " ሲሉ ወቅሰዋል።
በዚህ የምግብ አቅርቦት ደስተኛ ያልሆኑ የዋና ግቢ እና የዓዲ ሓቂ ግቢ ተማሪዎች ድርጊቱን በመቃወማቸው ለድብደባ እና ለእስር መዳረጋቸውን ገልጸዋል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ በመቐለ ዩኒቨርስቲ የአሪድ የተማሪዎች ምግብ ቤት ሰራተኛን አነጋግሯል።
እኚሁ ሰራተኛ ፤ " ግርግሩ በቁርስ ሰዓት ነበር የጀመረው ተማሪዎቹ በቁርስ ሰዓት ሲቅርብላቸው የነበረው ሁለት ዳቦ ግራሙ ጨምሯል በማለት አንድ ዳቦ እንዲሰጣቸው ተደረገ ተማሪዎቹ ዳቦው አንድ መሆኑን እና የተጨመረ ግራም እንደሌለ ተናግረው የዩኒቨርስቲው አመራሮች እንዲያነጋግሩዋቸው ጠየቁ " በማለት የጉዳዩን መነሻ አብራርተዋል።
" ይሁን እንጂ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት መልስ ባለመስጠታቸው የተቆጡ ተማሪዎች የምግብ ጠረጴዛዎችን ፣ የምግብ ቁሳቁሶችን ፣ መስታወቶችን እና ሌሎች ነገሮች ወደ መስበር ተሸጋግረዋል በምግብ ቤቱ ሰራተኞች ላይ ግን ያደረሱት ጉዳት የለም " ብለዋል።
በቁርስ ሰዓት በአሪድ ካምፓስ የጀመረው ግርግር ወደ ዓዲ ሓቂ ካምፓስ በመዝለቅ እስከ እራት ሰዓት ድረስ በዩኒቨርስቲ ንብረቶች ላይ ውድመት መድረሱን ተገልጿል።
የክልሉ ፓሊስ ኮሚሽን ወደ ካምፓሶቹ የፀጥታ አካላት መላኩ ተነግሯል።
በዚህም ሳቢያ በፓሊስ እና በተማሪዎቹ መካከል በተፈጠረ ግጭት ተማሪዎች የድብደባ ጥቃት እንደደረሰባቸው ተነግሯል።
በሁለቱ ካምፓሶች ግን ለጊዜው ግምቱ ያልተጣራ ንብረት መውደሙን ለመረዳት ተችሏል።
በመቐለ ዩኒቨርስቲ አሪድ እና ዓዲ ሓቂ ካምፓሶች የተፈጠረው ግርግር በአሁኑ ሰዓት ሙሉ በሙሉ ቆሟል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የዩኒቨርስቲውን የኮሙኒኬሽን ኮርፓሬት ስለ ተፈጠረው ግርግር ማብራርያ እንዲስጥ ያቀረበው ጥያቄ " የጉዳዩ መነሻ እና መድረሻ የሚመለከት ይፋዊ መግለጫ በሚድያ እስከሚሰጥ ጠብቁ የሚል " ምላሽ ተሰጥቶታል።
በኃላም ተቋሙ ማብራሪያ አውጥቷል።
በዚህም ፦
- በሃገር ደረጃ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሃገራዊ የምግብ ሜኑ በትምህርት ሚኒስቴር ጸድቆ ለትግበራ መላኩን ገልጿል።
- ዩኒቨርሲቲው ከተማሪዎች ህብረት ጋር በመነጋገር የመቐለ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች የምግብ ሜኑን አዘጋጅቶ ወደ ትግበራ መግባቱን አመልክቷል።
- በሜኑው ላይ የሚስተካከሉ ነገሮች ካሉ ብሄራዊ ሜኑ በይዘት እና በጀት ደረጃ እስካልተለየ ድረስ ጥያቄዎች በተማሪዎች ህብረት በኩል ቀርበው ማስተካከል እንደሚቻል አመልክቷል።
- በሃገር ደረጃ ተግባራዊ የሆነውን የምግብ ሜኑ ተቃውሞ የዩኒቨርሲቲውን መሰረተልማት ማጥፋት እና የካፊተርያ እና የጥበቃ ሰራተኞች ላይ ጉዳት ማድረስ ተማሪዎችን እንዲሁም ማህበረሰቡን እና ሃገሪቱን የሚጎዳና ተግባር እንደሆነ ገልጿል።
- ተማሪዎች ቅሬታቸውን በሰላማዊ መንገድ መግለጽ እንዳለባቸው አሳስቧል።
ጉዳዩን በተመለከተ የመቐለ ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች ህብረት የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ያቀረቧቸው ጥያቄዎች ትክክለኛ ስለመሆናቸው የሚገልጽ የአቋም መግለጫ አውጥቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው የአቋም መግለጫ ከሚመለከታቸው የማኔጅመንት አካላት ጋር በተደረገ ውይይት ያለኣግባብ የታሰሩ ተማሪዎች እንዲፈቱ እና ያለ መረጃ በተማሪዎች ላይ እርምጃ እንዳይወሰድ መወያየታቸውን ይገልጻል።
በተጨማሪም አዲሱ ሜኑ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ እስከሚሆን ድረስ በነባሩ ሜኑ እንዲቀጥል ከመግባባት ላይ መደረሱን ገልጿል።
ህብረቱ ለተማሪዎች ሰላማዊ ጥያቄ ከተማሪዎች ጎን እንደሚቆም ይሁን እንጂ በዋና ግቢ ካፍቴሪያ እና በኣዲ ሓቂ ተማሪዎች ላይ የደረሰው ጉዳት እና ስህተት ፈጽሞ መደገም የለበትም ብሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🚨“ አቶ ክርስቲያን ታደለና ዮሐንስ ቧያለው ዛሬ የሐኪም ቀጠሮ ነበራቸው ማረሚያ ቤቱ አልወሰዳቸውም ” - ቤተሰቦቻቸው 🔴 “ በሕይወት የመኖር መብታቸውን ነው ያሳጧቸው። የእስረኛ ዝውውር ወይስ በሕይወት የመኖር መብት ነው የሚቀድመው ? ” - ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ አዋሽ አርባ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት ባደረባቸው የጤና እክል በወቅቱ ባለመታከማቸው ለአንጀት ድርቀት ህመም የተዳረጉት አቶ…
“ አቶ ዮሐንስን ቧያለውን ለይተው ‘ዞን አምስት’ የሚባል ቦታ አስገብተውታል። ያ ቦታ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሰው ከባድ ጥፋት ሲያጠፋ መቅጫ ነው ” - ጉዳዩን የሚከታተሉ አካል
ለ1 ዓመት ከ5 ወር በእስራት ላይ የሚገኙት የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ዮሐንስ ቧያለው አብረዋቸው ከነበሩት 41 እስረኞች ተለይተው “ ለሕይወታቸው አስጊ ወደሆነ ቦታ ” ለማዘወር ተገደዋል ይህ ደግሞ ጭንቀት ፈጥሮብናል ሲሉ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ አካል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ሰኞ ታኀሳስ 14 ቀን 2017 ዓ/ም 41 እስረኞች ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ወደ ቂሊንጦ እንደተዘዋወሩ ገልጸው፣ አቶ ዮሐንስን ለይተው “ በ‘ሸኔ ተጠርጥረው’ ካሉ ሰዎች " ጋር ወስደዋቸዋል ሲሉ ጠቁመዋል።
በመሆኑም የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ያሉበትን ቦታ ጎብኝተው የአቶ ዮሐንስን ሕይወት ደህንነት እንዲያረጋግጡ ጠይቀዋል።
ስለአቶ ዮሐንስ ቧያለው በዝርዝር የተባለው ምንድን ነው ?
“ ትላንት እስረኞቹን ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ወደ ቂሊንጦ አዘዋውረዋል። 41 እስረኞችን ነው ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የወሰዱት።
ከዚያ በኋላ አቶ ዮሐንስን ቧያለውን ለይተው አስቀርተው ‘ዞን አምስት’ የሚባል ቦታ አስገብተውታል። ያ ቦታ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሰው ከባድ ጥፋት ሲያጠፋ መቅጫ ነው።
እዛ ውስጥ ያሉት በ'ሸኔ' ተጠርጥረው ያሉ ሰዎች ናቸው። ለይተው ከእነርሱ ጋር ነው ያስቀመጡት። ‘ሸኔ ናችሁ’ ተብለው የታሰሩ፣ ‘ሸኔ’ የተባሉ ልጆች ናቸው እዛ ያሉት።
ይሄ ሁኔታውን ያከብደዋል። በዛ ላይ ደግሞ ኦፕራሲዮን ከተሰራ ሁለት ሳምንቱ ነው። አሁን ካስገቡት ቦታ አልጋ የሚባል ነገር የለም። ባዶ መሬት ላይ ነው እየተኛ ያለው።
አቶ ዮሐንስ አሁን የገባበት ቦታ በጣም የሚያሰጋ፣ እንኳን ኦፕራሲዮን የተደረገ ጤነኛ ሰውም የሚታመምበት ክፍል ነው። ቤቱ በጣም ቅዝቃዜ ስላለው እያነከሰ ነው። ” ሲሉ ገልጸዋል።
አቶ ዮሐንስ ከ41 እስረኞች ተለይተው የተወሰዱት ምክንያት በግልጽ ሳይታወቅና ከአቶ ክርስቲያን ታደለ ጋር ኦፕራሲዮን ተሰርተው የነበረ ቢሆንም በቀጠሯቸው ቀን ሀኪም ቤት ሳይሄዱ በቀሩበት ሁኔታ መሆኑ ተገልጿል።
አሁንም የጤናቸው ጉዳይ አሳሳቢ እንደሆነ፣ ለአቶ ዮሐንስ ማስታገሻ መድኃኒት እንኳ ለመውሰድ ፈቃድ እንዳልተገኘ፣ ቁስላቸውን መመርመር ባለመቻላቸው በጠና እየታመሙ መሆናቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ አካላት ጠቁመዋል።
አቶ ዮሐንስ ቧያለው እና ክርስቲያን ታደለ በአዋሽ አርባ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት በጠና ታመው በጊዜው ባለመታከማቸው ለአንጀት ድርቀት በሽታ ተጋልጠው ከቆዩ በኋላ ከሳምንታት በፊት ቀዶ ጥገና ቢደረግላቸውም በቀጠሯቸው ቀን ወደ ህክምና ለመሄድ መከልከላቸውን መነገሩ ይታወሳል።
(የአቶ ዮሐንስን የቦታ ለውጥ እንዲገመግሙ መልክዕት የተላለፈላቸው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ድርጊቱን ገምግመው ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆኑ ማብራሪያቸው በቀጣይ ይቀርባል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ለ1 ዓመት ከ5 ወር በእስራት ላይ የሚገኙት የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ዮሐንስ ቧያለው አብረዋቸው ከነበሩት 41 እስረኞች ተለይተው “ ለሕይወታቸው አስጊ ወደሆነ ቦታ ” ለማዘወር ተገደዋል ይህ ደግሞ ጭንቀት ፈጥሮብናል ሲሉ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ አካል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ሰኞ ታኀሳስ 14 ቀን 2017 ዓ/ም 41 እስረኞች ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ወደ ቂሊንጦ እንደተዘዋወሩ ገልጸው፣ አቶ ዮሐንስን ለይተው “ በ‘ሸኔ ተጠርጥረው’ ካሉ ሰዎች " ጋር ወስደዋቸዋል ሲሉ ጠቁመዋል።
በመሆኑም የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ያሉበትን ቦታ ጎብኝተው የአቶ ዮሐንስን ሕይወት ደህንነት እንዲያረጋግጡ ጠይቀዋል።
ስለአቶ ዮሐንስ ቧያለው በዝርዝር የተባለው ምንድን ነው ?
“ ትላንት እስረኞቹን ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ወደ ቂሊንጦ አዘዋውረዋል። 41 እስረኞችን ነው ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የወሰዱት።
ከዚያ በኋላ አቶ ዮሐንስን ቧያለውን ለይተው አስቀርተው ‘ዞን አምስት’ የሚባል ቦታ አስገብተውታል። ያ ቦታ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሰው ከባድ ጥፋት ሲያጠፋ መቅጫ ነው።
እዛ ውስጥ ያሉት በ'ሸኔ' ተጠርጥረው ያሉ ሰዎች ናቸው። ለይተው ከእነርሱ ጋር ነው ያስቀመጡት። ‘ሸኔ ናችሁ’ ተብለው የታሰሩ፣ ‘ሸኔ’ የተባሉ ልጆች ናቸው እዛ ያሉት።
ይሄ ሁኔታውን ያከብደዋል። በዛ ላይ ደግሞ ኦፕራሲዮን ከተሰራ ሁለት ሳምንቱ ነው። አሁን ካስገቡት ቦታ አልጋ የሚባል ነገር የለም። ባዶ መሬት ላይ ነው እየተኛ ያለው።
አቶ ዮሐንስ አሁን የገባበት ቦታ በጣም የሚያሰጋ፣ እንኳን ኦፕራሲዮን የተደረገ ጤነኛ ሰውም የሚታመምበት ክፍል ነው። ቤቱ በጣም ቅዝቃዜ ስላለው እያነከሰ ነው። ” ሲሉ ገልጸዋል።
አቶ ዮሐንስ ከ41 እስረኞች ተለይተው የተወሰዱት ምክንያት በግልጽ ሳይታወቅና ከአቶ ክርስቲያን ታደለ ጋር ኦፕራሲዮን ተሰርተው የነበረ ቢሆንም በቀጠሯቸው ቀን ሀኪም ቤት ሳይሄዱ በቀሩበት ሁኔታ መሆኑ ተገልጿል።
አሁንም የጤናቸው ጉዳይ አሳሳቢ እንደሆነ፣ ለአቶ ዮሐንስ ማስታገሻ መድኃኒት እንኳ ለመውሰድ ፈቃድ እንዳልተገኘ፣ ቁስላቸውን መመርመር ባለመቻላቸው በጠና እየታመሙ መሆናቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ አካላት ጠቁመዋል።
አቶ ዮሐንስ ቧያለው እና ክርስቲያን ታደለ በአዋሽ አርባ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት በጠና ታመው በጊዜው ባለመታከማቸው ለአንጀት ድርቀት በሽታ ተጋልጠው ከቆዩ በኋላ ከሳምንታት በፊት ቀዶ ጥገና ቢደረግላቸውም በቀጠሯቸው ቀን ወደ ህክምና ለመሄድ መከልከላቸውን መነገሩ ይታወሳል።
(የአቶ ዮሐንስን የቦታ ለውጥ እንዲገመግሙ መልክዕት የተላለፈላቸው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ድርጊቱን ገምግመው ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆኑ ማብራሪያቸው በቀጣይ ይቀርባል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ከከባዱ አደጋ አንዲትም ጭረት ሰውነታችንን ሳይነካን ነው የወጣነው። ይህን ማድረግ የሚችለው አላህ (ሱወ) ብቻና ብቻ ነው !! " - ሳቢር ይርጉ
ኡስታዝ ሀሺም ሽፋ እና ሳቢር ይርጉ አስከፊ ከሆነ የመኪና አደጋ አንድም ነገር ሳይሆኑ በህይወት ተረፉ።
ዛሬ ምሽት ከሱሉልታ አቅጣጫ አጣና ጭኖ ቁልቁለቱን ሲምዘገዘግ የነበረ ኤኔትሬ ከባድ መኪና ከነጭነቱ እነ ኡስታዝ ሲጓዙበት በነበረችው መኪና ላይ ከባዱ አደጋ አድርሷል።
ሳቢር ይርጉ ፤ " እንሆ የአላህን ኒዕማ አውጀናል። በአላህ ፈቃድ ሁለታችንም ከከባዱ አደጋ ምንም ሳንሆን ተርፈናል። ሁለታችንም አንዲትም ጭረት ሰውነታችን ላይ ሳይደርስ በሰላም ወጥተናል አልሀምዱሊላህ !! ወደ የቤታችንም ገብተናል " ሲሉ ገልጸዋል።
" በህይወት ስንተርፍ ሞትን አንዘንጋው። ይህን ማድረግ የሚችለው አላህ (ሱወ) ብቻና ብቻ ነው። አልሀምዱሊላህ ጀዛኩሙላሁ ኸይር ! " ሲሉ አክለዋል።
አደጋው የደረሰባቸው ዛሬ ምሽት ለጥቂት ቀናት የሊደርሺፕ ስልጠና ለመካፈል እየተጓዙ በነበረበት ወቅት ነው።
መኪናዋን ሲያሽከረክሩ የነበሩት ኡስታዝ ሀሺም ሽፋ ሲሆኑ ሁለቱም ከከባዱ አደጋ አንድም ጭረት ሰይነካቸው በህይወት ተርፈው ወደ ቤት ገብተዋል።
መረጃውን ያካፈሉን በ ' ድምጻችን ይሰማ ' የሰላማዊ እንቅስቃሴና ትግል ወቅት በእጅጉ የሚታወቁት ሳቢር ይርጉ ናቸው።
@tikvahethiopia
ኡስታዝ ሀሺም ሽፋ እና ሳቢር ይርጉ አስከፊ ከሆነ የመኪና አደጋ አንድም ነገር ሳይሆኑ በህይወት ተረፉ።
ዛሬ ምሽት ከሱሉልታ አቅጣጫ አጣና ጭኖ ቁልቁለቱን ሲምዘገዘግ የነበረ ኤኔትሬ ከባድ መኪና ከነጭነቱ እነ ኡስታዝ ሲጓዙበት በነበረችው መኪና ላይ ከባዱ አደጋ አድርሷል።
ሳቢር ይርጉ ፤ " እንሆ የአላህን ኒዕማ አውጀናል። በአላህ ፈቃድ ሁለታችንም ከከባዱ አደጋ ምንም ሳንሆን ተርፈናል። ሁለታችንም አንዲትም ጭረት ሰውነታችን ላይ ሳይደርስ በሰላም ወጥተናል አልሀምዱሊላህ !! ወደ የቤታችንም ገብተናል " ሲሉ ገልጸዋል።
" በህይወት ስንተርፍ ሞትን አንዘንጋው። ይህን ማድረግ የሚችለው አላህ (ሱወ) ብቻና ብቻ ነው። አልሀምዱሊላህ ጀዛኩሙላሁ ኸይር ! " ሲሉ አክለዋል።
አደጋው የደረሰባቸው ዛሬ ምሽት ለጥቂት ቀናት የሊደርሺፕ ስልጠና ለመካፈል እየተጓዙ በነበረበት ወቅት ነው።
መኪናዋን ሲያሽከረክሩ የነበሩት ኡስታዝ ሀሺም ሽፋ ሲሆኑ ሁለቱም ከከባዱ አደጋ አንድም ጭረት ሰይነካቸው በህይወት ተርፈው ወደ ቤት ገብተዋል።
መረጃውን ያካፈሉን በ ' ድምጻችን ይሰማ ' የሰላማዊ እንቅስቃሴና ትግል ወቅት በእጅጉ የሚታወቁት ሳቢር ይርጉ ናቸው።
@tikvahethiopia
🤙🏽ከሳፋሪኮም ወደ የቴሌ የሚያስደውሉ የድምፅ ጥቅሎች በመጠቀም ከ07 ➡️ 09 መስመር በሽ በሽ ብለን እንደዋወል! ከሳፋሪኮም ጋር በአብሮነት አንድ ወደፊት⚡️
🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ:
https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
#MPESASafaricom
#SafaricomEthiopia
#1Wedefit
#Furtheraheadtogether
🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ:
https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
#MPESASafaricom
#SafaricomEthiopia
#1Wedefit
#Furtheraheadtogether
#Somalia #Eritrea
የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ኤርትራ ናቸው።
ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ኤርትራ ፣ አስመራ መግባታቸው ተነግሯል።
አስመራ ሲደርሱ ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ነው ኤርፖርት ተገኝተው የተቀበሏቸው።
የኤርትራው የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገ/መስቀል ሁለቱ መሪዎች በሁለትዮሽ ፣በቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ብለዋል።
ፕሬዜዳንቱ በቱርክ፣ አንካራ ከኢትዮጵያ ጋር ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር በኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቃሚነት ጉዳይ ላይ ስምምነት ከፈረሙ በኃላ ነው ኤርትራ የሄዱት።
አንደንድ ዘገባዎች የኤርትራው እና የሱማሊያው መሪ የአንካራውን ስምምነት አጀንዳቸው ሊያደርጉት እንደሚችሉ አሳይተዋል።
የሶማሊያው መሪ ከዚህ ቀደም ወደ ኤርትራ በመመላለስ የሚታወቁ ሲሆን በተለይ ግን ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ የመግባቢያ ስምምነት ከፈረሙ በኃላ እንዲሁም ኢትዮጵያ ለህዝቦቼ የባህር በር ያስፈልጋቸዋል ይህ የህልውና ጉዳይ ጭምር ነው በማለት አቋማን ይፋ ካደረገችና ዓለም አቀፍ አጀንዳ ካደረገችው በኃላ ደጋግመው ኤርትራ ፣ አስመራ ኢሳያስ ጋር ተመላልሰዋል።
የኤርትራው መሪ በነዚህ ወቅቶች አንድም ጊዜ ሶማሊያ፣ ሙቃዲሾ ለጉብኝት ብለው ሄደው አያውቁም።
ባለፈው ጥቅምት ወር ላይ የግብፅ፣ የኤርትራ እና የሶማሊያ መሪዎች በአስመራ የሶስትዮሽ ጉባኤ አካሂደው የሶማሊያ ተቋማት እና ጦር ድንበሯን ለመጠበቅ እና የግዛት አንድነቷን ለማስጠበቅ የሚያስችል ስምምነት ላይ መድረሳቸው የሚዘነጋ አይደለም።
#Somlaia #Eritrea
@tikvahethiopia
የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ኤርትራ ናቸው።
ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ኤርትራ ፣ አስመራ መግባታቸው ተነግሯል።
አስመራ ሲደርሱ ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ነው ኤርፖርት ተገኝተው የተቀበሏቸው።
የኤርትራው የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገ/መስቀል ሁለቱ መሪዎች በሁለትዮሽ ፣በቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ብለዋል።
ፕሬዜዳንቱ በቱርክ፣ አንካራ ከኢትዮጵያ ጋር ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር በኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቃሚነት ጉዳይ ላይ ስምምነት ከፈረሙ በኃላ ነው ኤርትራ የሄዱት።
አንደንድ ዘገባዎች የኤርትራው እና የሱማሊያው መሪ የአንካራውን ስምምነት አጀንዳቸው ሊያደርጉት እንደሚችሉ አሳይተዋል።
የሶማሊያው መሪ ከዚህ ቀደም ወደ ኤርትራ በመመላለስ የሚታወቁ ሲሆን በተለይ ግን ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ የመግባቢያ ስምምነት ከፈረሙ በኃላ እንዲሁም ኢትዮጵያ ለህዝቦቼ የባህር በር ያስፈልጋቸዋል ይህ የህልውና ጉዳይ ጭምር ነው በማለት አቋማን ይፋ ካደረገችና ዓለም አቀፍ አጀንዳ ካደረገችው በኃላ ደጋግመው ኤርትራ ፣ አስመራ ኢሳያስ ጋር ተመላልሰዋል።
የኤርትራው መሪ በነዚህ ወቅቶች አንድም ጊዜ ሶማሊያ፣ ሙቃዲሾ ለጉብኝት ብለው ሄደው አያውቁም።
ባለፈው ጥቅምት ወር ላይ የግብፅ፣ የኤርትራ እና የሶማሊያ መሪዎች በአስመራ የሶስትዮሽ ጉባኤ አካሂደው የሶማሊያ ተቋማት እና ጦር ድንበሯን ለመጠበቅ እና የግዛት አንድነቷን ለማስጠበቅ የሚያስችል ስምምነት ላይ መድረሳቸው የሚዘነጋ አይደለም።
#Somlaia #Eritrea
@tikvahethiopia
#ፓስፖርት
🚨 " በምሽት ጊዜ ለጾታዊ ጥቃት ጭምር የተዳረጉ ሴቶች እንዳሉ ሰምተናል " - የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም
🔴 " ሁኔታዎቹ ከመንገድ መዘጋጋት ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ ናቸው " -ኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት
" በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሚጠበቅብንን ክፍያዎችን እና መረጃዎች አሟልተን በቀጠሮአችን መሰረት በመገኘት ፓስፖርት እንዲሰጠን ለብዙ ጊዜ ብንመላለስም አገልግሎቱን ማግኘት አልቻልንም " ያሉ ተገልጋዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አቀረቡ።
" ከምልልሱም በላይ ያለምንም ህጋዊ ምክንያት ከ2000 እስከ 5000 ብር ከፍለን ቀጠሮ አስይዘን በቀጠሮአችንም ተገኝተን እያለ የቀጠሮ ቀን ተቃጥሏል አዲስ ቀጠሮ መያዝ አለባችሁ በመባላችን ላልተገባ ወጭ እና እንግልት ተዳርገናል " ነው ያሉት።
ተገልጋዮቹ አስተዳደራዊ እና ተቋማዊ በደል ደርሶብናል ሲሉ አቤቱታቸውን ለኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አቅርበዋል።
የእንባ ጠባቂ ተቋምም በቁጥር 127 የሚሆኑት እነዚህ ቅሬታ አቅራቢ ተገልጋዮች ለተቋሙ ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት ጉዳያቸውን በመመልከት ምላሽ እንዲሰጡበት ለኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በደብዳቤ ጠይቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው " አመልካቾች የሚጠበቅባቸውን ክፍያ እንዲሁም መረጃዎችን አሟልተው በተገኙበት እና የቀጠሮ ቀናቸው በምን ህጋዊ ምክንያት እንደተቃጠለ የሚገልጽ መልስ እና ማስረጃ ይህ ደብዳቤ በደረሳችሁ በ05 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ እንድትልኩ እንጠይቃለን " ይላል፡፡
እንባ ጠባቂ ተቋሙ ደብዳቤውን የጻፈው 01/04/17 ዓ/ም ሲሆን በአምስት የስራ ቀናት ምላሽ እንዲሰጠው ጠይቆ ነበር።
ነገር ግን ከተቋሙ ምንም አይነት ምላሽ አለማግኘቱን በኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የመንግስት ተቋማት አስተዳደር በደል መርማሪ ባለሞያ የሆኑት አቶ እንዳየሁ ውቤ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
መርማሪው በዝርዝር ምን አሉ ?
" ቅሬታቸውን ይዘው ወደ ተቋማችን የመጡ ተገልጋዮች በመጀመሪያ 127 የነበሩ ቢሆንም በኋላ ቀስ በቀስ 205 በላይ ደርሰዋል።
በቦታው ተገኝተን ባደረግነው ምልከታ ተመሳሳይ የሆነ መጉላላት ያጋጠማቸው ዜጎች ግን ከ5 ሺ በላይ እንደሚገመቱ ታዝበናል።
ተገልጋዮቹ ከደሴ እና የተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ፓስፖርት ለማውጣት በቀጠሮአቸው መሰረት የመጡ ቢሆንም ነገር ግን አገልግሎቱን በጊዜ ባለማግኘታቸው እና እዛው ለማደር በመገደዳቸው ምክንያት በምሽት ጊዜ ለጾታዊ ጥቃት ጭምር የተዳረጉ ሴቶች እንዳሉ ሰምተናል።
አብዛኞቹ ከደሴ፣ ወሎ ፣ከጎንደር እና ሎሎችም ሩቅ አካባቢዎች ወደ ባህር ዳር መጥተው ለሶስት እና አራት ቀናት ለማደር እየተገደዱ ነው የሚበላው አጥቶ የሚለምንም አለ ተርበናል እያሉ የሚያለቅሱም አሉ " ብለዋል።
ከ6 ወር እስከ አንድ አመት ለሚጠጋ ጊዜ እየተጉላሉ ያሉት እኚህ ተገልጋዮች አብዛኞቹ ጉዳያቸው ከአሻራ ጋር የተገናኘ ነው።
መርማሪው ደብዳቤውን ለባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ ለአቶ አስማረ ጫኔ በአካል በመገኘት የሰጡ ሲሆን በወቅቱ ለሃላፊው ቀጠሮአችውን ሳያጠፉ ተቃጥሎባቸዋል ብላችሁ በአዲስ ተመዝገቡ ያላችኋቸው ለምንድነው ? የሚል ጥያቄ ማንሳታቸውን ነግረውናል።
ሃላፊው በምላሻቸው ከታህሳስ 1 ጀምሮ አዲስ መመሪያ በመምጣቱ ቀጠሮ ያለፋቸው ተገልጋዮች እንደ አዲስ ተመዝግበው ብቻ አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችሉ ነግረውናል ብለዋል።
ነገር ግን ቅሬታ አቅራቢ ተገልጋዮቹ በቀጠሮአቸው የተገኙ በመሆናቸው አዲስ የተባለው መመሪያ የማይመለከታቸው እና ከቅሬታ አቅራቢዎቹ ጋር የማይገናኝ በመሆኑ ምላሽ የሚሉትን ነገር በደብዳቤ እንዲያሳውቁ በመንገር እንደተመለሱ አስታውሰዋል።
ይሁን እንጂ እስካሁን ምንም አይነት ምላሽ ተቋሙ አለመስጠቱን ገልጸው በድጋሚ ደብዳቤ ለመጻፍ እየተዘጋጀን ነው ብለዋል።
ነገር ግን የአሁኑ ደብዳቤ ለሃላፊው በስሙ እንዲጻፍ የሚደረግ መሆኑን ጠቅሰው በድጋሚ ምላሽ የማይሰጡ ከሆነ ጉዳዩ ወደ ክስ እንደሚያመራ አቶ እንዳየሁ ተናግረዋል።
ቲክቫህ የቅሬታ አቅራቢዎቹን እና የዕንባ ጠባቂ ተቋምን ቅሬታ በመያዝ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑትን አቶ አስማረ ጫኔን ምላሽ ጠይቋል።
ሃላፊው በምላሻቸው ምን አሉ ?
" ሁኔታዎቹ ከመንገድ መዘጋጋት ጋር በተያያዘ ምክንያት በቀጠሮ ስለማይመጡ የቀጠሮ መደራረብ ጋር የተያያዙ ችግሮች ናቸው።
ይህንን ችግር ለመቅረፍ ምሽትን ጨምሮ ቅዳሜ እና እሁድም ያለምንም ቅጣት አገልግሎት ስንሰጥ ቆይተናል " ብለዋል።
ስለ ዝርዝር ነገሮች ግን ምላሽ የሚሰጠው በዋና መስሪያ ቤት ደረጃ መሆኑን በመግለጽ ተጨማሪ ማብራሪያ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።
@tikvahethiopia
🚨 " በምሽት ጊዜ ለጾታዊ ጥቃት ጭምር የተዳረጉ ሴቶች እንዳሉ ሰምተናል " - የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም
🔴 " ሁኔታዎቹ ከመንገድ መዘጋጋት ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ ናቸው " -ኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት
" በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሚጠበቅብንን ክፍያዎችን እና መረጃዎች አሟልተን በቀጠሮአችን መሰረት በመገኘት ፓስፖርት እንዲሰጠን ለብዙ ጊዜ ብንመላለስም አገልግሎቱን ማግኘት አልቻልንም " ያሉ ተገልጋዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አቀረቡ።
" ከምልልሱም በላይ ያለምንም ህጋዊ ምክንያት ከ2000 እስከ 5000 ብር ከፍለን ቀጠሮ አስይዘን በቀጠሮአችንም ተገኝተን እያለ የቀጠሮ ቀን ተቃጥሏል አዲስ ቀጠሮ መያዝ አለባችሁ በመባላችን ላልተገባ ወጭ እና እንግልት ተዳርገናል " ነው ያሉት።
ተገልጋዮቹ አስተዳደራዊ እና ተቋማዊ በደል ደርሶብናል ሲሉ አቤቱታቸውን ለኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አቅርበዋል።
የእንባ ጠባቂ ተቋምም በቁጥር 127 የሚሆኑት እነዚህ ቅሬታ አቅራቢ ተገልጋዮች ለተቋሙ ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት ጉዳያቸውን በመመልከት ምላሽ እንዲሰጡበት ለኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በደብዳቤ ጠይቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው " አመልካቾች የሚጠበቅባቸውን ክፍያ እንዲሁም መረጃዎችን አሟልተው በተገኙበት እና የቀጠሮ ቀናቸው በምን ህጋዊ ምክንያት እንደተቃጠለ የሚገልጽ መልስ እና ማስረጃ ይህ ደብዳቤ በደረሳችሁ በ05 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ እንድትልኩ እንጠይቃለን " ይላል፡፡
እንባ ጠባቂ ተቋሙ ደብዳቤውን የጻፈው 01/04/17 ዓ/ም ሲሆን በአምስት የስራ ቀናት ምላሽ እንዲሰጠው ጠይቆ ነበር።
ነገር ግን ከተቋሙ ምንም አይነት ምላሽ አለማግኘቱን በኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የመንግስት ተቋማት አስተዳደር በደል መርማሪ ባለሞያ የሆኑት አቶ እንዳየሁ ውቤ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
መርማሪው በዝርዝር ምን አሉ ?
" ቅሬታቸውን ይዘው ወደ ተቋማችን የመጡ ተገልጋዮች በመጀመሪያ 127 የነበሩ ቢሆንም በኋላ ቀስ በቀስ 205 በላይ ደርሰዋል።
በቦታው ተገኝተን ባደረግነው ምልከታ ተመሳሳይ የሆነ መጉላላት ያጋጠማቸው ዜጎች ግን ከ5 ሺ በላይ እንደሚገመቱ ታዝበናል።
ተገልጋዮቹ ከደሴ እና የተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ፓስፖርት ለማውጣት በቀጠሮአቸው መሰረት የመጡ ቢሆንም ነገር ግን አገልግሎቱን በጊዜ ባለማግኘታቸው እና እዛው ለማደር በመገደዳቸው ምክንያት በምሽት ጊዜ ለጾታዊ ጥቃት ጭምር የተዳረጉ ሴቶች እንዳሉ ሰምተናል።
አብዛኞቹ ከደሴ፣ ወሎ ፣ከጎንደር እና ሎሎችም ሩቅ አካባቢዎች ወደ ባህር ዳር መጥተው ለሶስት እና አራት ቀናት ለማደር እየተገደዱ ነው የሚበላው አጥቶ የሚለምንም አለ ተርበናል እያሉ የሚያለቅሱም አሉ " ብለዋል።
ከ6 ወር እስከ አንድ አመት ለሚጠጋ ጊዜ እየተጉላሉ ያሉት እኚህ ተገልጋዮች አብዛኞቹ ጉዳያቸው ከአሻራ ጋር የተገናኘ ነው።
መርማሪው ደብዳቤውን ለባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ ለአቶ አስማረ ጫኔ በአካል በመገኘት የሰጡ ሲሆን በወቅቱ ለሃላፊው ቀጠሮአችውን ሳያጠፉ ተቃጥሎባቸዋል ብላችሁ በአዲስ ተመዝገቡ ያላችኋቸው ለምንድነው ? የሚል ጥያቄ ማንሳታቸውን ነግረውናል።
ሃላፊው በምላሻቸው ከታህሳስ 1 ጀምሮ አዲስ መመሪያ በመምጣቱ ቀጠሮ ያለፋቸው ተገልጋዮች እንደ አዲስ ተመዝግበው ብቻ አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችሉ ነግረውናል ብለዋል።
ነገር ግን ቅሬታ አቅራቢ ተገልጋዮቹ በቀጠሮአቸው የተገኙ በመሆናቸው አዲስ የተባለው መመሪያ የማይመለከታቸው እና ከቅሬታ አቅራቢዎቹ ጋር የማይገናኝ በመሆኑ ምላሽ የሚሉትን ነገር በደብዳቤ እንዲያሳውቁ በመንገር እንደተመለሱ አስታውሰዋል።
ይሁን እንጂ እስካሁን ምንም አይነት ምላሽ ተቋሙ አለመስጠቱን ገልጸው በድጋሚ ደብዳቤ ለመጻፍ እየተዘጋጀን ነው ብለዋል።
ነገር ግን የአሁኑ ደብዳቤ ለሃላፊው በስሙ እንዲጻፍ የሚደረግ መሆኑን ጠቅሰው በድጋሚ ምላሽ የማይሰጡ ከሆነ ጉዳዩ ወደ ክስ እንደሚያመራ አቶ እንዳየሁ ተናግረዋል።
ቲክቫህ የቅሬታ አቅራቢዎቹን እና የዕንባ ጠባቂ ተቋምን ቅሬታ በመያዝ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የባህር ዳር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑትን አቶ አስማረ ጫኔን ምላሽ ጠይቋል።
ሃላፊው በምላሻቸው ምን አሉ ?
" ሁኔታዎቹ ከመንገድ መዘጋጋት ጋር በተያያዘ ምክንያት በቀጠሮ ስለማይመጡ የቀጠሮ መደራረብ ጋር የተያያዙ ችግሮች ናቸው።
ይህንን ችግር ለመቅረፍ ምሽትን ጨምሮ ቅዳሜ እና እሁድም ያለምንም ቅጣት አገልግሎት ስንሰጥ ቆይተናል " ብለዋል።
ስለ ዝርዝር ነገሮች ግን ምላሽ የሚሰጠው በዋና መስሪያ ቤት ደረጃ መሆኑን በመግለጽ ተጨማሪ ማብራሪያ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የተማሪዎች ዕለታዊ የምግብ ተመን ወጪ 100 በሆነበት ማግስት አንድ ዳቦ ለቁርስ ማቅረብ ማሻሻል አይደለም " -የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በትላንትናው ዕለት በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ከተሻሻለው የምግብ ሜኑ ጋር በተያያዘ በዩኒቨርሲቲው የተፈጠረ ግርግር ለተማሪዎች መጎዳት እና ለንብረት ውድመት ምክንያት መሆኑ ተሰምቷል። ለአለመግባባቱ መነሻ የሆነው በትምህርት ሚኒስቴር በተሻሻለው እና በሁሉም የዩኒቨርሲቲዎች…
#Update
“ መቐለ ብቻ አይደለም። ትላንት ደብረ ብርሃንም ፣ ደባርቅም ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም ተነስቷል ቅሬታው ” - የኢትዮጵያ ተማሪዎች ኀብረት
🚨 " የታሰሩ ተማሪዎች ተፈተዋል !! "
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምግብ ሜኑ ተመሳሳይ እንዲሆን የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን የምግብ በጀት ላይ ትምህርት ሚኒስቴር ማስተካከያ ማድረጉ ይታወቃል።
በዚህም ትምህርት ሚኒስቴር አጠናሁት ባለው ወቅታዊ የምግብ ዋጋ ጥናት መሠረት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን የምግብ በጀት ከታኀሳስ 1 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ በቀን 100 ብር እንዲሆን መወሰኑ አይዘነጋም።
ውሳኔው ተግባራዊ መሆኑን ተከትሎ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በአዲሱ የምግብ ሜኑ ቅሬታ እንዳላቸው እየገለጹ ይገኛሉ።
በመቐለ ፣ ደብረ ብርሃን፣ ደባርቅና ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች የሚገኙ ተማሪዎች ትላንት ቅሬታቸውን በአደባባይ መግለጻቸውን የኢትዮጵያ ተማሪዎች ኀብረት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
በመቐለ ዩኒቨርሲቲ በነበረው በዚሁ ሂደት በተማሪዎቹ ድብደባ እስራት እንደደረሰ፣ ንብረት እንወደመም ተመልክቷል።
በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ትላንት በተፈጠረው ግርግር የታሰሩ ተማሪዎች ተፈቱ ? ምን ያህል ተማሪዎች ናቸው የታሰሩት ? ስንል የጠየቅነው ኀብረቱ፣ “ 27 አካባቢ ተማሪዎች ነበሩ የታሰሩት ” ሲል መልሷል።
ኀብረቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል፣“ ታስረው የነበሩት ሁሉም የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተፈተትተዋል። አሁን እዛ እየወጣን ነው ” ሲል አረጋግጧል።
“ ሁሉም ነገር ተረጋግቷል። ተቋሙ የራሳቸው በመሆኑ ተማሪዎች መጠበቅ እንዳለባቸው፣ የወደመው ንብረትም በጋራ መስተካከል ያለበት እንዲስተካከል ማሰሰቢያ ተሰጥቶ ሁሉንም አስፈትተናቸዋል ” ነው ያለው።
“ ተማሪዎቹ ታስረው የነበረው ቀዳማዊ ወያኔ እና ኣደ ሓቂ ነበር። ግማሾቹ ከቁኑ ስምንት ሰዓት ገደማ፣ ቀሪዎቹ ደግሞ ከምሽቱ 12 ሰዓት ተኩል ነው የፈቱት ” ብሏል።
በተማሪዎች ላይ ድብደባ ደርሷል የተባለውን በተመለከተ ማብራሪያ እንዲሰጥ ጠይቀነው በሰጠን ምላሽ ደግሞ፣ “ ተማሪ ላይ ድብደባ ደርሷል። ጉዳትም ደርሷል ” ነው ያለው።
የአዲሱ የምግብ ሜኑ ውሳኔ ቅሬታ ያሳደረው በመቐለ ዩኒቨርሲቲ በሚገኙ ተማሪዎች ብቻ እንዳልሆነ ኅብረቱ ገልጿል።
ኅብረቱ “ መቐለ ብቻ አይደለም። ትላንት ደብረ ብርሃን፣ ደባርቅም በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም ተነስቷል ” ሲል ነው ያስረዳው።
“ በይበልጥ የመቐለው ፓለቲሳይዝ ስለሆነ ነው እንጂ በሌሎችም እኮ አለ ሰላማዊ ሰልፍ የወጡበት በዚሁ በሜኑ ጉዳይ። ጉዳዩ አገራዊ ነው እየሆነ ያለው ” ሲልም አክሏል።
የሰላማዊ ሰልፉን ምክንያት በተመለከተ በሰጠን ማብራሪያ ኀብረቱ፣ “ አዲስ የወጣውን የምግብ ፓሊሲ እንቀበላለን አንቀበልም በሚል ነው ” ብሏል።
ቅሬታ የተነሳበትን የምግብ ሜኑውን በተመለከተ ከትምህር ሚኒስቴር ጋር በጉዳዩ ዙሪያ ለመወያዬት ቀጠሮ እንደያዘም ኅብረቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
“ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲው፣ የመቐለው አሁን ተረጋግቷል። ኮንሰርኑ ግን የ100 ብሯ ጉዳይ ነው ” ሲልም ገልጿል።
ቅሬታው በሌሎችም ዩኒቨርቲዎች መሆኑን ኀብረቱ በገለጸው መሠረት ቅሬታ አለበት የተባለውን ደባርቅ ዩኒቨርሲቲን የጠየቅን ሲሆን፣ የአዲሱ ሜኑ ጉዳይ ለእርሱም ጥያቄ እንደሆነበት ገልጿል።
(አዱሱን የምግብ ሜኑ የተመለከተው የተማሪዎቹ ቅሬታና የደባርቅ ዩኒቨርሲቲዝርዝር ማብራሪያ በቀጣይ ይቀርባል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ መቐለ ብቻ አይደለም። ትላንት ደብረ ብርሃንም ፣ ደባርቅም ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም ተነስቷል ቅሬታው ” - የኢትዮጵያ ተማሪዎች ኀብረት
🚨 " የታሰሩ ተማሪዎች ተፈተዋል !! "
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምግብ ሜኑ ተመሳሳይ እንዲሆን የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን የምግብ በጀት ላይ ትምህርት ሚኒስቴር ማስተካከያ ማድረጉ ይታወቃል።
በዚህም ትምህርት ሚኒስቴር አጠናሁት ባለው ወቅታዊ የምግብ ዋጋ ጥናት መሠረት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን የምግብ በጀት ከታኀሳስ 1 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ በቀን 100 ብር እንዲሆን መወሰኑ አይዘነጋም።
ውሳኔው ተግባራዊ መሆኑን ተከትሎ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በአዲሱ የምግብ ሜኑ ቅሬታ እንዳላቸው እየገለጹ ይገኛሉ።
በመቐለ ፣ ደብረ ብርሃን፣ ደባርቅና ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች የሚገኙ ተማሪዎች ትላንት ቅሬታቸውን በአደባባይ መግለጻቸውን የኢትዮጵያ ተማሪዎች ኀብረት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
በመቐለ ዩኒቨርሲቲ በነበረው በዚሁ ሂደት በተማሪዎቹ ድብደባ እስራት እንደደረሰ፣ ንብረት እንወደመም ተመልክቷል።
በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ትላንት በተፈጠረው ግርግር የታሰሩ ተማሪዎች ተፈቱ ? ምን ያህል ተማሪዎች ናቸው የታሰሩት ? ስንል የጠየቅነው ኀብረቱ፣ “ 27 አካባቢ ተማሪዎች ነበሩ የታሰሩት ” ሲል መልሷል።
ኀብረቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል፣“ ታስረው የነበሩት ሁሉም የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተፈተትተዋል። አሁን እዛ እየወጣን ነው ” ሲል አረጋግጧል።
“ ሁሉም ነገር ተረጋግቷል። ተቋሙ የራሳቸው በመሆኑ ተማሪዎች መጠበቅ እንዳለባቸው፣ የወደመው ንብረትም በጋራ መስተካከል ያለበት እንዲስተካከል ማሰሰቢያ ተሰጥቶ ሁሉንም አስፈትተናቸዋል ” ነው ያለው።
“ ተማሪዎቹ ታስረው የነበረው ቀዳማዊ ወያኔ እና ኣደ ሓቂ ነበር። ግማሾቹ ከቁኑ ስምንት ሰዓት ገደማ፣ ቀሪዎቹ ደግሞ ከምሽቱ 12 ሰዓት ተኩል ነው የፈቱት ” ብሏል።
በተማሪዎች ላይ ድብደባ ደርሷል የተባለውን በተመለከተ ማብራሪያ እንዲሰጥ ጠይቀነው በሰጠን ምላሽ ደግሞ፣ “ ተማሪ ላይ ድብደባ ደርሷል። ጉዳትም ደርሷል ” ነው ያለው።
የአዲሱ የምግብ ሜኑ ውሳኔ ቅሬታ ያሳደረው በመቐለ ዩኒቨርሲቲ በሚገኙ ተማሪዎች ብቻ እንዳልሆነ ኅብረቱ ገልጿል።
ኅብረቱ “ መቐለ ብቻ አይደለም። ትላንት ደብረ ብርሃን፣ ደባርቅም በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም ተነስቷል ” ሲል ነው ያስረዳው።
“ በይበልጥ የመቐለው ፓለቲሳይዝ ስለሆነ ነው እንጂ በሌሎችም እኮ አለ ሰላማዊ ሰልፍ የወጡበት በዚሁ በሜኑ ጉዳይ። ጉዳዩ አገራዊ ነው እየሆነ ያለው ” ሲልም አክሏል።
የሰላማዊ ሰልፉን ምክንያት በተመለከተ በሰጠን ማብራሪያ ኀብረቱ፣ “ አዲስ የወጣውን የምግብ ፓሊሲ እንቀበላለን አንቀበልም በሚል ነው ” ብሏል።
ቅሬታ የተነሳበትን የምግብ ሜኑውን በተመለከተ ከትምህር ሚኒስቴር ጋር በጉዳዩ ዙሪያ ለመወያዬት ቀጠሮ እንደያዘም ኅብረቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
“ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲው፣ የመቐለው አሁን ተረጋግቷል። ኮንሰርኑ ግን የ100 ብሯ ጉዳይ ነው ” ሲልም ገልጿል።
ቅሬታው በሌሎችም ዩኒቨርቲዎች መሆኑን ኀብረቱ በገለጸው መሠረት ቅሬታ አለበት የተባለውን ደባርቅ ዩኒቨርሲቲን የጠየቅን ሲሆን፣ የአዲሱ ሜኑ ጉዳይ ለእርሱም ጥያቄ እንደሆነበት ገልጿል።
(አዱሱን የምግብ ሜኑ የተመለከተው የተማሪዎቹ ቅሬታና የደባርቅ ዩኒቨርሲቲዝርዝር ማብራሪያ በቀጣይ ይቀርባል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ለሰላም የሚከፈል ማንኛውም ዋጋ በመንግሰት በኩል ይከፈላል " - አቶ መሀመድ እድሪስ ዛሬ የሰላም ሚኒስትር ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ጋር ተገናኝተው በመንበረ ፓትርያርክ መወያየታቸው ተሰምቷል። በቅርቡ የተሾሙት የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መሀመድ እድሪስ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ጋር የትውውቅ ፕሮግራም…
" የሐይማኖት ሐገር የሆነችውና በርካታ የችግር መፍቻ ባህልና ልምድ ያላት ሀገር ላይ ዜጎች በሰላም እጦት ምክንያት መቸገር የለባቸውም ! " - የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ
የኢፌዴሪ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መሐመድ እድሪስ ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራሮችና የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ጋር ትውውቅ ማድረጋቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
ሚኒስትሩ በሰላም ግንባታና በሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ጋር ትብብራቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ምን አሉ ?
- መጅሊሱን ለመጎብኘት ሚኒስትሩ መምጣታቸው በራሳቸው እና በጠቅላይ ምክር ቤቱ ስም አመስግነዋል።
- የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሙስሊሙን አንድነትና የሐገራችንን ሰላም ለማጠናከር የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ ጅምሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
- ጠቅላይ ምክር ቤቱ በቀጣይ በሚያካሄደው የመጅሊስ ምርጫ መንግስት በተለይ የሰላም ሚኒስቴር አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል።
የሰላም ሚኒስትር አቶ መሐመድ እድሪስ ምን አሉ ?
° በዓለም መድረክ ላይ የሃገራችንን ኢትዮጵያን ስም ከፍ ለማድረግ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚዳንት ሼይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ እየሰሩ ያሉትን ስራ አድንቀዋል።
- በአፋርና በሱማሌ ወንድም ሕዝቦች መካከል የነበረውን የቆየ አለመግባባትና ግጭት ለመፍታት ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለሰራው ስራ ምስጋና አቅርበዋል። በቀጣይ ሁሉ አቀፍ የሰላምና የልማት ስራዎችን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
° የሐይማኖት ሐገር የሆነችውና በርካታ የችግር መፍቻ ባህልና ልምድ ያላት ሀገር ላይ ዜጎች በሰላም እጦት ምክንያት መቸገር እንደሌለባቸው ተናግረዋል።
° ጠቅላይ ምክር ቤቱ አሁን ያለው ሰላም እንዲጎለብት ፣እየታዩ ያሉ የሰላም ፈተናዎች እንዲፈቱና ዘላቂ መፍትሄ እንዲመጣ ሀገራዊ የሰላም ጥሪና ዱዓ በጁምዓ ሰላት ላይ የሰላም ጥሪ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
° መንግስት ግጭቶች በንግግር እንዲፈቱ ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ያቀረበ እና ለዚህም ቁርጠኝነቱ ያለው መሆኑን ገልጸው የሰላም ሚኒስቴርም ከሁሉም የእምነት አባቶችና ተቋማት ጋር በትብብር እንደሚሰራ አመልክተዋል።
° መጭው የመጅሊስ ምርጫ በሰላማዊ ሁኔታ እንዲካሄድ መንግስት አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ አሳውቀዋል።
#MinistryofPeace
@tikvahethiopia
የኢፌዴሪ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መሐመድ እድሪስ ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራሮችና የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ጋር ትውውቅ ማድረጋቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
ሚኒስትሩ በሰላም ግንባታና በሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ጋር ትብብራቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ምን አሉ ?
- መጅሊሱን ለመጎብኘት ሚኒስትሩ መምጣታቸው በራሳቸው እና በጠቅላይ ምክር ቤቱ ስም አመስግነዋል።
- የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሙስሊሙን አንድነትና የሐገራችንን ሰላም ለማጠናከር የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ ጅምሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
- ጠቅላይ ምክር ቤቱ በቀጣይ በሚያካሄደው የመጅሊስ ምርጫ መንግስት በተለይ የሰላም ሚኒስቴር አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል።
የሰላም ሚኒስትር አቶ መሐመድ እድሪስ ምን አሉ ?
° በዓለም መድረክ ላይ የሃገራችንን ኢትዮጵያን ስም ከፍ ለማድረግ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚዳንት ሼይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ እየሰሩ ያሉትን ስራ አድንቀዋል።
- በአፋርና በሱማሌ ወንድም ሕዝቦች መካከል የነበረውን የቆየ አለመግባባትና ግጭት ለመፍታት ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለሰራው ስራ ምስጋና አቅርበዋል። በቀጣይ ሁሉ አቀፍ የሰላምና የልማት ስራዎችን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
° የሐይማኖት ሐገር የሆነችውና በርካታ የችግር መፍቻ ባህልና ልምድ ያላት ሀገር ላይ ዜጎች በሰላም እጦት ምክንያት መቸገር እንደሌለባቸው ተናግረዋል።
° ጠቅላይ ምክር ቤቱ አሁን ያለው ሰላም እንዲጎለብት ፣እየታዩ ያሉ የሰላም ፈተናዎች እንዲፈቱና ዘላቂ መፍትሄ እንዲመጣ ሀገራዊ የሰላም ጥሪና ዱዓ በጁምዓ ሰላት ላይ የሰላም ጥሪ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
° መንግስት ግጭቶች በንግግር እንዲፈቱ ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ያቀረበ እና ለዚህም ቁርጠኝነቱ ያለው መሆኑን ገልጸው የሰላም ሚኒስቴርም ከሁሉም የእምነት አባቶችና ተቋማት ጋር በትብብር እንደሚሰራ አመልክተዋል።
° መጭው የመጅሊስ ምርጫ በሰላማዊ ሁኔታ እንዲካሄድ መንግስት አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ አሳውቀዋል።
#MinistryofPeace
@tikvahethiopia