TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የተዘጋው የመኪና መንገድ ከ10 ሰዓታት ቆይታ በኋላ ተከፍቷል።

ከውቕሮ ዓዲግራት በሚወስድ ከመቐለ በ40 ኪሎ ሜትር ርቀት በምትገኘው አጉላዕ በምትባለው ከተማ መንገዱ የተዘጋበት ምክንያት ምንድን ነው ?

መንገዱ ከጥዋት እስከ 10:00 ከሰዓት በኋላ የዘጉት በይፋ በዲሞብላይዜሽን (DDR) ወደ ህብረተሰቡ ያልተቀላቀሉ የትግራይ የቀድሞ ተዋጊዎች ናቸው።

የቀድሞ ተዋጊዎቹ ከዲሞብላይዜሽን  (DDR) አጀማመር እና አፈፃፀም ጋር በተያያዘ ፦

1ኛ. የዴሞብላይዜሽን (DDR) አሰራርና መመሪያ ሴት ተዋጊዎች ፣ በጦርነቱ የተጎዱ ታጣቂዎች ቀጥሎ በሙሉ ጤንነት ያሉ እየለ በየደረጃው እንዲፈፀም የሚፈቅድና የሚያዝዝ እያለ በጦርነቱ የተጎዳን ትቶ ጤነኞቹ ለምን አስቀደመ ?

2ኛ. ዴሞብላይዜሽን (DDR) የማይመለከታቸው አንዳንድ ግለሰቦች በወጣው ዝርዝር ስማቸው ተካተዋል ለምን ? ... የሚሉ እና መሰል ጥያቄዎች አንስተዋል።  

ያነሱዋቸው ጥያቄዎች አስመልክተው ከሚመለከታቸው የፀጥታ እና የፓለቲካ አመራሮች ከተወያዩ በኋላ መንገዱ ሊከፈት እንደቻለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል አሳውቆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
ሶሪያ በቀጣይ ወዴት ?

የ24 ዓመታት የበሽር አላሳድ አገዛዝ አክትሟል።

ቤተሰባቸውን ይዘውም ሩስያ ገብተዋል። ጥገኝነትም ተሰጥቷቸዋል።

አሁን ላይ የታጠቁ ተቃዋሚዎች መንበሩን ይዘዋል።

አላሳድን አንባገነን እንደሆኑ የሚገልጹ በርካቶች ክስተቱን ለሶሪያ ዘላቂ ሰላም እድል ያመጣል ይላሉ።

ከዚህ በተቃራኒ በሀገሪቱ ብዙ ታጣቂዎች ነፍጥ ስለያዙ  ለስልጣን ሲባል ወደ 2ኛው ዙር የእርስ በእርስ እልቂት ሊገባ ይችላል የሚሉ ቁጥራቸው ቀላል አይደለም።

ሶሪያ ከፊቷ ተስፋ እና ስጋት ተደቅኗል።

ሶሪያ ውስጥ የሚንቀሳቀሱት እነማን ናቸው ?

እ.ኤ.አ 2011 ነው የሶሪያ እርስ በርስ እልቂት የጀመረው።

የተሳታፊው ብዛት በርካታ ነው። እነዚህ የየራሳቸው ተሳትፎ፣ አመለካከት፣ ዓላማ ያነገቡ ናቸው።

ጉዳዩ ወስብስብ ያለ ነው።

👉 የአሳድ መንግሥት ኃይሎች

የሶሪያ አረብ ጦር (SAA) እና የብሔራዊ መከላከያ ኃይል (NDF) እኚህ የአላሳድ የጀርባ አጥንት ናቸው። SAA ኦፊሴላዊ የሆነው የሶሪያ መከላከያ ነው። NDF በመንግሥት የሚደገፍ ሚሊሻ ነው። SAA በኢራን እና ሩስያ ይደገፋል። በቀጣዩ መንግሥት ምስረታ ዕጣ ፋንታቸው ምን ይሆን ? የሚለው ምናልባትም በነ ሩስያ እና ኢራን ተፅእኖ ስር የወደቀ ሊሆን ይችላል።

👉 ነጻ የሶሪያ ጦር (FSA)

ቡድኑ መጀመሪያ የተቋቋመው ከሶሪያ ጦር ከድተው በወጡ አካላት ነው። ከዛም ወደ ተለያዩ አንጃዎች እና ጥምረት ተለውጣል። ብዙ ጊዜ ከምዕራባውያን እና ከባህረ ሰላጤው ሀገራት ድጋፍ ያገኛል። በብዙ የሶሪያ ክፍሎች ይንቀሳቀሳል ነገር ግን በተለይ በሰሜን የአሳድን ጦር ሲዋጋ ነበር። በኃላም ISISን ሲዋጋ ነበር።

👉 ሀያት ታህሪር አል-ሻም (HTS)

ይህ በመጀመሪያ የሶሪያ የአልቃይዳ ክንፍ ነበር ፤ አልኑስራ በሚል ነበር ይንቀሳቀስ የነበረው። 2017 ላይ ግን በኢድሊብ እና ከፊል አሌፖ ፈርጠም ብሎ ወጥቷል። አላማው እስላማዊ መንግሥት መመስረት እንደሆነ ይነገርለታል። በቅርቡ አሳድን በመገርሰስ ጥቃት ላይ ቁልፍ ሚና ነበረው። በአዲሱ መንግሥት መመስረት ውስጥ የራሱን አላማ ለማስረጽ ግፊት ሊያደርግ ይችላል በዚህም ሴኩላር ከሚባሉት እና መሃከል ላይ ካሉት ጋር ሊጋጭ ይችላል። በኢድሊብ ከነበራቸው የመንግሥት አስተዳደር ጥብቅ የሸሪያ ህግ ለመተግበር ሊሰራ ይችላል።

👉 የሶሪያ ብሔራዊ ጦር (SNA)

እኚህ በቱርክ የሚደገፉ ናቸው። በዋነኝነት በሰሜናዊ ሶሪያ ነው የሚንቀሳቀሱት። የኩርዲሽ ኃይሎችን በመዋጋት የቱርክን ተፅእኖ ለማስረጽ ይንቀሳቀሳሉ ይባላሉ። በአዲሱ መንግሥት የቱርክን ፍላጎት የያዘ ሃሳብ ይዘው ሊቀርቡ ይችላሉ።

👉 የሶሪያ ዴሞክራቲክ ኃይል (SDF)

እኚህ በኩርዲሽ ዋይፒጂ ነው የሚመሩት። በአሜሪካ ድጋፍ ISISን በማሸነፉ ረገድ ትልቁን ሚና ተጫውተዋል። እኚህ ቡድኖች ሰሜናዊ ምስራቅ ሶሪያን ተቆጣጥረው የያዙ ናቸው። ራዕያቸው የፌዴራል፣ ያልተማከለ ሶሪያ እንድትኖር ነው። በማንኛውም አዲስ መንግስት ውስጥ፣ የኩርድ የራስ ገዝ አስተዳደር ወይም ፌደራሊዝም እንዲሰፍን ግፊት ሊያደርጉ ይችላሉ። ይህ ደግሞ እንደ SNA ካሉ ሌሎች ቡድኖች ጋር ሊያጋጫቸው ይችላል።

እንግዴ እኚህ ሁሉ አላማቸው የሚለያይ ነፍጥ ያነገቡ ቡድኖች ናቸው ሶሪያ ውስጥ ያሉት።

ከአሳድ አገዛዝ ወደ አዲስ መንግሥት ለሚደረገው ሽግግር ምናልባትም እጅግ ወሳኝና ጥልቅ ድርድር አልያም የእርስ በእርስ ግጭት በቡድኖቹ መካከል ሊፈጠር ይችላል።

🚨 SAA እና የአሳድ ደጋፊ ሚሊሻዎች ለውጡ ለነሱ ወይም አጋሮቻቸው ምቹ ሁኔታ ካልፈጠረ ሊቃወሙ ይችላሉ።
🚨 HTS ይበልጥ ሃይማኖታዊ የመንግሥት አስታዳደር ለመመስረት ሊንቀሳቀሱ ይችላሉ።
🚨 FSA እና ተመሳሳይ አቋም ያላቸው ቡድኖች ዴሞክራሲያዊ ሂደትን ይደግፋሉ ነገር ግን ጉልህ ተፅእኖ እንዲኖራቸው በአንድ የፖለቲካ ጥላ ስር መጠቃለል አለባቸው።
🚨 SDF ፌዴራሊዝም (ክልላዊ ራስን በራስ የማስተዳደር) እንዲተገበር ግፊት ሊያደርግ ይችላል። ይህን ሞዴል ሌሎች ከተቃወሙት ግጭት መቀጠሉ አይቀሬ ነው።
🚨 ቱርክ በSNA በኩል በምታደርገው ተፅእኖ ጠንካራ ፣ የተማከለ የኩርድ አካል እንዳይፈጠር ለመከላከል በመሆኑ ይህ ወደ ቀጣይ ውጥረት ሊያመራ ይችላል።


በአዲሱ የሶሪያ መንግሥት መስረታ የኃይል መመጣጠን ፣ በቡድኖቹ መካከል ያለው የአስተሳሰብ ልዩነት እና የውጭ ኃይሎች ተፅእኖ ትልቅ ፈታና ይሆናል። የእያንዳንዱ ቡድን ወታደራዊ ጥንካሬ በውጭ ኃይሎች ድጋፍ እና በውስጥ የፖለቲካ እንቅስቃሴ የተቀረጸ በመሆኑ ሰላማዊ  ሽግግር ይኖር ይሆን ? የሚለው አሳሳቢ ነው።

አንዳንዶች ለውጡን በአግባቡ መያዝ ካልተቻለ ሀገሪቱ የመበታተን አደጋ እና ከበፊቱም የባሰ ሰቆቃ ውስጥ ልትገባ የምትችልበት ዕድል ሰፊ እንደሆነ እየገለጹ ነው።

እኚህ ሁሉ ነፍጥ ያነገቡ ቡድኖች ወደ አንድነት መጥተው ጠንካራ ሶሪያን ይመሰርቱ ይሆን ? ወይስ ሁለተኛው ዙር የሶሪያ እርስ በርስ እልቂት ይቀጥላል ? ሁሉንም ጊዜ ይፈታዋል !

🛑 ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህንን ፅሁፍ ለማዘጋጀት በመሰል ጉዳዮች ላይ የሚተነትኑትን ቻክ ፈረን ጨምሮ የተለያዩ ድረገጾችን ተጠቅሟል።

#TikvahEthiopia #ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
#ArbaMinch

🔴 የእሳት አደጋ መድረሱን ተከትሎ የድረሱልን ጥሪ ሲያሰሙ የነበሩ እናት ህይወት አለፈ።

በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ ረፋድ 4 ሠዓት አከባቢ በተለምዶ ' ቡቡ ሜዳ ' ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ በሚገኘዉ አዲሱ ገበያ የእሳት አደጋ ተከስቶ በንብረት ላይ ዉድመት ማድረሱን የከተማው አስተዳደር ፖሊስ አስታውቋል።

በእሳት አደጋዉም የሰዉ ሕይወት መጥፋቱን የሚገልፁ መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ፖሊስን ማብራሪያ ጠይቋል።

የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ም/ኢንስፔክተር ጋፋሮ ቶማስ ፤ በአከባቢው በሚገኝ አንድ የኤሌክትሮንክስ ሱቅ ዉስጥ በኤሌክትሪክ ኮንታክት ምክንያት በተነሳ የእሳት አደጋ 12 ሱቆች መዉደማቸዉን ገልጸዋል።

በአደጋው ወቅት በገበያው ዉስጥ በተለምዶ መንገድ በጩኸት ይድረሱልን ጥሪ ሲያደርጉ ከነበሩ ሴቶች መካከል አንዲት እናት ባለባቸው የጤና እክል ምክንያት ህይወታቸው ማለፉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

እኚህ እናት የልብ ሕመም እንደነበራቸው የገለጹት ም/ኢንስፔክተር ጋፋሮ ፤ በጩኸት የድረሱልን ጥሪ ሲያሰሙ ሳለ በመድከማቸው ወደ ነጭ ሳር ሆስፒታል ቢወሰዱም ሕይወታቸው ማርተፍ አልተቻለም ነው ያሉት።

ሆኖም በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ሕይወቷ ያለፈዉ በእሳት አደጋዉ በደረሰ ጉዳት ተደርጎ የሚሰራጨው መረጃ የተሳሳተ ነዉ ብለዋል።

በገበያዉ ዉስጥ ያለዉ የሱቆች አሰራር እና አጠቃቀም ለእሳት አደጋ አጋላጭ ነዉ ያሉት አዛዡ ፤ ሕይወቷ ያለፈዉ ግለሰብ በገበያው ዉስጥ ሱቅ እንደነበራቸውና ሱቃቸዉም እሳት አደጋዉ እንዳልደረሰበት ገልፀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የእሳት አደጋዉ በተገለፀው አኳሃን መፈጠሩን በገበያው ውስጥ ካሉ ነጋዴዎች የሰማ ሲሆን ሕይወታቸዉ ያለፈዉ ግለሰብም በቀጥታ በእሳት አደጋው በደረሰ ጉዳት አለመሆኑን ነጋዴዎች ተናግረዋል።

" ሞች ወ/ሮ አበባየሁ መንገሻ እንደ እናት ያሳደጉኝ እናቴ ናቸዉ፤ የሞቱት በእሳት አደጋዉ አይደለም " ያሉት አቶ አማኑኤል ሰይፉ የተባሉ ነጋዴ አስቀድመው የልብ ሕመምና የሕክምና ክትትል እንደነበራቸው አስረድተዋል።

አክለው በእሳት አደጋዉ ወቅት መደንገጣቸዉና ከሌሎችም ሴቶች ጋር ሆነዉ ለይድረሱልን ብዙ መጮኻቸዉን ተከትሎ መዳከማቸዉንና ወደ ነጭ ሳር ሆስፒታል ቢወሰዱም ሕይወታቸው ማለፉን ነው የገለጹት።

#TikvahEthiopiaFamilyArbaMinch

@tikvahethiopia
#Berbera

የሶማሌላንድ የገንዘብ እና ልማት ሚኒስቴር ዛሬ በሶማሌላንድ በርበራ ወደብ የኢትዮጵያ ትራንዚት ማሳለጫ ቢሮ ስራ መጀመሩን ገልጿል።

የሶማሌላንድ የንግድና ቱሪዝም ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አብዲረሺድ ኢብራሂም ደግሞ " የሶማሌላንድ መንግሥት በበርበራ ወደብ የኢትዮጵያ ትራንዚት ማሳለጫ ቢሮ ስራ አስጀምሯል " ሲሉ ይፋ አድርገዋል።

" ይህ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ ምዕራፍ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ይህ ውጥን ቀጠናዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስርን ለማጠናከር ሶማሌላንድ ያላትን ቁርጠኝንተ ያሳያል ሲሉ አክለዋል።

ቢሮው በወደቡ የሚራገፉ ጭነቶችን ወደ ኢትዮጵያ የተለያዩ መዳረሻዎች እንዲጓጓዙ የሚያሳልጥ ነው ተብሏል።

በሌላ በኩል ፥ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴሌቪዥን በይፋዊ ማስጀመሪያ ስርዓቱ ላይ ወደቡን የሚያስተዳድረው የተባበሩት አረብ ኤሜሬትሱ DP World በርበራ ዋና ስራ አስፈፃሚ ስፓቺ ዋታንቫራቺ ተገኝተው እንደነበር ገልጿል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው ፤ " ይህ ቢሮ ወደቡ ላይ የሚራገፉ የተለያዩ ጭነቶችን ወደ ኢትዮጵያ እንዲጓጓዙ የሚያሳልጥ ነው " ብለዋል።

የሶማሌላንድ የገንዘብ እና ልማት ሚኒስትሩ ሳድ (ዶ/ር) " ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ ግንኙነታቸው የተጠናከረ ነው ፤ 120 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ አማራጭ ወደቦችን መጠቀም ትችላለች " ማለታቸውን ብሔራዊ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

Photo Credit : #SomalilandFinanceDevelopment

@tikvahethiopia
#TecnoAI

በተለምዶ ረጅም ሰዓታትን አንድ ስራ ላይ ማባከን ታሪክ ሆነ ፤ ቀናት የሚወሰዱ ስራዎችን በሰዓታት ብቻ መፈፅም የአዲሱ ቴክኖ ኤ አይ ዋነኛ መገለጫ ነው፡፡

ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመከተል የቴክኖ ቲክቶክ ገጽ ፎሎው በማድረግ እና Bio ላይ ያለውን ሊንክ ተጭነው በመመዝገብ ታህሳስ 10 በስካይላይት ሆቴል በሚካሄደው የሀገራችን ትልቁ የኤ አይ ሁነት ላይ ይሳተፉ፡፡

https://www.tiktok.com/@tecnoet

@tecno_et @tecno_et
#SafaricomEthiopia

🎉ለወራት የፈለግናቸውን ኳስ ጨዋታዎች ሁሉ ከዳር እስከ ዳር በሚገኘው በሳፋሪኮም ኔትወርክ ላይ በDSTV በቀጥታ እንከታተል! ⚽️

በM-PESA ላይ ስንገዛ የ6ወር 90ጊባ በ6,000 ብር ብቻ! 

🔗የM-PESAን ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቦታችንን https://yangx.top/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይንም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!

የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://yangx.top/Safaricom_Ethiopia_PLC

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም ቻናላችን https://yangx.top/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom #1Wedefit
#Furtheraheadtogether
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia #Somalia " ልዑካኑ የቀጥታ የፊት ለፊት ንግግር / ውይይት አላደረጉም " - የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በቱርክ አሸማጋይነት ትላንት አንካራ ውስጥ ውይይት ማድረጋቸው ተሰምቷል። በቱርክ ጋባዥነት በተደረገው ውይይት የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታየ አጽቀስላሴ እና የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር አህመድ ሞሊም የመሯቸው ልዑካን…
#Ethiopia #Somalia #Turkey

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ልዑካቸው አንካራ ቱርክ ይገኛሉ።

የቱርክ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በጽሕፈት ቤታቸው አቀባበል ያደረጉላቸው ሲሆን ሁለቱ መሪዎች ከልዑካን ቡድናቸው ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።

በሌላ በኩል ፤ የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሼክ መሐመድ አንካራ ይገኛሉ።

እሳቸውም ከኤርዶጋን ጋር ተነጋግረዋል።

መሪዎቹ አንካራ የሄዱበት ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ የገቡበትን ውጥረት ለማርገብ እንዲቻል ኤርዶጋን የንግግር መድረክ አመቻችተውላቸእ ነው።

መሪዎቹ ፊት ለፊት ይነጋገራሉ እየተባለ ይገኛል።

ሮይተርስ የሶማሊያ ዜና አገልግሎት ሶናን ጠቅሶ እንደዘገበው የሁለቱ መሪዎች የፊት ለፊት ንግግር እየተካረረ የሄደውን የሁለቱን ሃገራት ዲፕሎማሲያዊ ቀውስ ለማርገብ ያስችላል ብሏል።

እንደ ተባለው ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ከሀሰን ሼክ መሀመድ ጋር ፊት ለፊት የሚገናኙ ከሆነ ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሌ ላንድ ጋር የወደብ ባለቤት የሚያደርጋትን ስምምነት ከተፈራረሙ ወዲህ ይህ የመጀመሪያዉ ይሆናል።

መረጃው ከጠ/ሚ ፅ/ቤት ፣ ዶቼ ቨለ ፣ ሮይተርስ የተሰባሰበ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የጁባላንድ መንግሥት ከሶማሊያ ፌዴራሉ መንግሥት ጋር ያለውን ግንኙነት ማቋረጡን ይፋ አደረገ። የጁባላንድ ካቢኔ ስብሰባ ካደረገ በኃላ ይፋ እንዳደረገው  " ሙሉ በሙሉና በይፋ ከሶማሊያ የፌዴራል መንግሥት ጋር ያለውን የስራም ሆነ ማንኛውንም ግንኙነት " አቋርጧል። የጁባላድ መንግሥት ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድን ፦ - ኃይላቸውን ያለ አግባብ በመጠቀም - የእርስ በእርስ ጦርነት በማነሳሳት…
#Jubaland #Somlaia

ከሶማሊያ ፌዴራል መንግስት ጋር ሁሉንም ግኑኝነቴን አቋርጫለሁ ፤ ተቆራርጫለሁ ያለው የጁባላንድ አስተዳደር እና የሶማሊያ ፌዴራል መንግሥት ዛሬ ወደ ግጭት ገብተዋል።

ዛሬ ከቀትር ጀምሮ ራስኮምቦኒ ላይ ከፍተኛ ውጊያ መደረጉ ተነግሯል።

ሁለቱም ወገኖች ግጭት መነሳቱን ገልጸው ግጭቱን ማን አስጀመረ በሚለው ላይ እርስ በእርስ እየተወነጃጀሉ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Oromia 🕊 " ሰው በየሄደበት ይገደል ነበር በጣም ትልቅ ችግር ውስጥ ነው ያለፍነው አሁን ከሰላም በላይ ምን ጥቅም አለ ? ሰላምን የሚበልጥ ነገር የለም ! " - ነዋሪዎች 🟢 " ክልሉን ወደ መደበኛ ሁኔታ ለማምጣት እንዲህ ያሉ እምርጃዎች ይበረታታሉ " - አቶ ሽመልስ አብዲሳ " የሰላም ስምምነቱን የተቀበልነው የህዝባችንን ስቃይ ከተመለከትን በኃላ ነው፤... ስምምነቱ ለኦሮሞ ህዝብ ትልቅ እፎይታ…
" በመርሕ ደረጃ መጥፎ ሰላም ጥሩ ጦርነት ባይኖርም የስምምነቶች ግልጽነት ማጣት ውጤቱን የተገላቢጦሽ ሊያደርገው ይችላል ! " - የትብብሩ ፓርቲዎች

መኢአድ፣ ኢሕአፓ፣ ዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄና እናት ፓርቲ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግለጫ ልከዋል።

ፓርቲዎቹ ፤ " አገራችን በሰላም እጦት፣ ሕዝባችን ለዓመታት በዘለቀ ጦርነት ቁምስቅሉን እያየ እንዳለ ምሥክር መቁጠር አይሻም። " ብለዋል።

" በተለይ በብዙ ተስፋና ጉጉት ተጠብቆ የነበረው ' ለውጥ ' የኋልዮሽ መሄድ ከጀመረ ወዲህ ሰላም ማደር ብርቅ፣ ፍጅትና ትርምስ ጌጣችን ከኾነ ሰነበተ " ሲሉ ገልጸዋል።

" ከዚህ ቀደም ኤርትራ በረሃ ከኦነግ ጋር በክልል አመራሮች ደረጃ ግልጽነት የጎደለው ስምምነት ከተደረገ በኋላ ሕዝብ ደስታውን ሳያጣጥም የሰላም ተፈራራሚው ኃይል " ቃል የተገባልኝ አልተፈጸመም " በሚል ሰበብ ተመልሶ ጫካ ከገባ ወዲኽ እንደ አገር ባጠቃላይ በተለይም ደግሞ የኦሮሚያ ክልል ያየው ቁምስቅል ተነግሮ የሚያልቅ አይደለም " ሲሉ ገልጸዋል።

ከሰሞኑ መንግሥት ' ኦነግ ሸኔ ' እያለ የሚጠራው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የተወሰነ ቡድን ሰላም መፈረሙ በመንግሥት የመገናኛ ብዙሃን በስፋት መዘገቡን የገለጹት ፓርቲዎቹ " መጥፎ ሰላም የለም በሚል ጥቂቶች እንኳን የሰላም አካል መኾናቸውን በበጎ የምንመለከተው ነው " ብለውታል።

ከዚኹ ጋር ተያይዞ " የታጣቂ ቡድኑ መሪ ናቸው የተባሉ ግለሰብና የተወሰኑ ወጣቶች ከክልል አመራሮች ጋር ስምምነት ሲፈራረሙ ታይተዋል " ብለዋል።

" ከስምምነቱ ማግስትም አዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች ለሦስት ቀናት በዘለቀ ተኩስ ስትናጥ ከርማለች " ያሉት ፓርቲዎቹ " በተኩሱ እስከ አኹን አንዲት እናት በጥይት ተመትተው ሕይወታቸው ማለፉን አረጋግጠናል " ብለዋል።

ይኸው ድርጊት በተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች እንደተከሰተ ገልጸዋል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ሂደቱ ጥርጣሬን እንዳጫረባቸው ጥርጣሬያቸው የሚነሳውም ከስምምነቱ ግልጸኝነት ማጣት ብቻ ሳይሆን ከእንዲህ ዓይነት ክስተቶች ጭምር መሆኑን ገልጸዋል።

" ስምምነቱ መሣሪያ ማውረድን አይጨምርም ወይ ? " ያሉት ፓርቲዎቹ " የከተማ አስተዳደሩ ርችት እንኳን እንዳይተኮስ ሲከለክል እንዳልከረመ እንዴት ሙሉ ትጥቅ ተይዞ መግባትንና ለቀናት ጭምር የድልነሺነት ብሥራት በሚመስያመስል መልኩ ተኩስን ሊፈቅድ ቻለ ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

በተጨማሪ ፦

° ' ከተማ ውስጥ ኹከት ለመፍጠር የመጡ ' በሚል በመታወቂያ ማንነት በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን ተጉዘው የመጡ ነብሰ ጡሮችና አረጋውያን ጭምር ከአዲስ አበባ መግቢያ ክብረ ነክ በኾነ መንገድ ሲመልስ የነበረ ኃይል አኹን የት ሄዴ ?

° ከዚኹ መሐል ሲገድል ሲቀማ የነበረ በውል ተጣርቶ ተጠያቂነት አይኖርም ወይ ?

° መንግሥት የሰላም ስምምነት ፈጸመ ከተባለው ግለሰብና ቡድን ጋር ከዚኽ ቀደም የነበረው ግንኙነት ምን ነበር ?

° ታንዛኒያ ድረስ ኹለት ጊዜ አድካሚ ሙከራዎች ተደርገው ጫፍ እየደረሱ የተናፈቀው ሰላም ሲጨነግፍ በአቋራጭ አዲስ አበባ እውን የኾነበት ተዓምር ምን ቢኾን ነው ?

° የአዲስ አበባ ከተማ ሕዝብ ሥነልቡናዊ ጫና እንዲደርስበት ታስቦ ተሠርቷል ወይ ? የሚሉ ጥያቄዎችን ፓርቲዎቹ አንስተዋል።

ፓርቲዎቹ ፤ የለአንድም ቀን እንኳን ሰላም መስፈን እጅጉን እንሻለን ብለዋል።

" የአንድም ሰው የሰላምን መንገድ መምረጥ ያስደስተናል " ሲሉ አክበላለዋል።

" በአንጻሩ ደግሞ በሂደቱ ዙሪያ የግልጽነት አለመኖርና የሰላሙ ዘላቂነት እጅግ ስለሚያሳስበን አጠራጣሪ ጉዳዮች ሲኖሩ ማንሳት በጎ ይመስለናል " ብለዋል።

ፓርቲዎቹ፦

➡️ የሰላም መጥፎ የለውምና የተደረሰውን ስምምነት ከነገዘፉ ችግሮቹ በበጎ እናየዋለን ብለዋል።

➡️ መንግሥት የስምምነቱን ሂደትና ዝርዝር ነጥቦች የመከራው ግንባር ቀደም ገፈት ቀማሽ ለሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ ይፋ እንዲያደርግ በአጽንኦት አሳስበዋል።

➡️ በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች ለቀናት የዘለቀው ተኩስ፣ በሰላም ስምምነት የመጣ ሳይኾን ኾን ተብሎ የሕዝብን ሥነ ልቡና ለመስለብና ለማስፈራራት የተደረገ መኾኑን ሕዝባችን እንዲያውቀው እንሻለን ብለዋል።

➡️ በዚኹ የተኩስ እሩምታ ሰበብ መገናኛ አካባቢ ለተገደሉት እናት መንግሥት ሓላፊነት የሚወስድ ኾኖ ቢያንስ ቤተሰባቸውን ይፋዊ ይቅርታ እንዲጠይቅና ተገቢውን ካሳ እንዲከፍል እንጠይቃለን ብለዋል።

➡️ መንግሥት ከሽርፍራፊ ደስታና ማስመሰል ወጥቶ ዘላቂ ሰላምን በሰጥቶ መቀበል መርኅ በገለልተኛ ታዛቢዎች አማካይነት ድርድር ለማድረግ ፈቃደኝነቱን በመግለጽና ለዚህም ተግባራዊ እርምጃ በመውሰድ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ያሉ ደም አፋሳሽ ጦርነቶች ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት እንዲያገኙ፣ በአፋጣኝም ተኩስ አቁም እንዲታወጅ በአጽንዖት አሳስበዋል።

#እናትፓርቲ
#መኢአድ
#ኢሕአፓ
#ዐማራግዮናዊንቅናቄ

@tikvahethiopia