TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba " አሁንም አንዳንድ የቤት ባለቤቶች ወደ ቤታቸው ለመግባት ምንም እንቅስቃሴ እያደረጉ አይደለም ፤ ይህ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ነው " - ኮርፖሬሽኑ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በተለያዩ ጊዜያት በእጣ እና በጨረታ ተላልፈው ነዋሪ ያልገባባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች አስመልክቶ እስከ ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም ድረስ የቤት ባለቤቶቹ ወደ ቤታቸው የማይገቡ ከሆነ በህግ አግባብ ውል…
#የጋራመኖሪያቤቶች
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በተለያዩ ጊዜያት በእጣ እና በጨረታ ተላልፈው ነዋሪ ያልገባባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች የቤት ባለቤቶቹ እንዲገቡባቸው የሰጠው የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ነገ ህዳር 30/2017 ዓ/ም ያበቃል።
ኮርፖሬሽኑ በሰጠው የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የቤት ባለቤቶቹ ወደ ቤታቸው የማይገቡ ከሆነ በህግ አግባብ ውል የሚቋረጥ መሆኑን መግለጹ ይታወሳል።
ቀደም ብሎ የተሰጠው ገደብ ጥምቅት 30 የነበረ ቢሆንም ቤታቸውን አድሰው ለመግባት የጊዜ እጥረት ላጋጠማቸው የቤት ባለቤቶች ተብሎ እስከ ህዳር 30 ተራዝሞ ነበር።
ይህ ለመጨረሻ ጊዜ የተሰጠ የጊዜ ገደብ መሆኑን ኮርፖሬሽኑ ገልጾ ነበር።
ቀኑ ነገ ሰኞ ያበቃል።
በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ የማይገቡ ነዋሪዎች የሽያጭ ውላቸው የሚቋረጥ እና በቤታቸው ውስጥ ለሚፈጸም ማንኛውም ህገወጥ ድርጊት ተጠያቂ እንደሚሆኑ መግለጹ ይታወሳል።
ከዘህ ቀደም ኮርፖሬሽኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥቶት በነበረው ማብራሪያ ምን ነበር ያለው ?
- ማስታወቂያው የወጣበት ዋናው ምክንያት ሰዎች ‘ ተቸገርን፣ ክፍት በሆኑ ቤቶች ወንጀል እየተሰራ ነው፣ እየተዘረፍን ነው፣ ሴቶች እየተደፈሩብን ነው፣ የጸጥታ ስጋትም እየሆኑብን ’ ብለው ቅሬታ ስላቀረቡ እንደሆነ፤
- ቤቶቹ ቼክ ሲደረጉ እጣ የወጣባቸው ፤ ውል የተፈጸመባቸው፣ በጨረታ የተላለፉ ነገር ግን ሰው ያልገባባቸው እንደሆኑ፤
- ነዋሪው በከፍተኛ ሁኔታ እየተቸገረ ፤ የጸጥታ ኃይሉም ጥያቄ እያነሳ እንደሆነ ፤
- " የቤት ባለቤቶች ቤታችሁን አድሳችሁ ግቡ " የተባለውም የግድ እራሳቸውን እንዳይደለ ፤ ቢፈልጉ አድሶ ማከራየት መብታቸው እንደሆነ፤
- የራሳቸው ቤት እስከሆነ ድረስ አድሰው ማከራት ከፈለጉ ደግሞ እራሳቸው መግባት መብታቸው እንደሆነ ዞሮ ዞሮ ሰው በቤቱ ሊኖርበት እንደሚገባ ማብራራቱ ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በተለያዩ ጊዜያት በእጣ እና በጨረታ ተላልፈው ነዋሪ ያልገባባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች የቤት ባለቤቶቹ እንዲገቡባቸው የሰጠው የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ነገ ህዳር 30/2017 ዓ/ም ያበቃል።
ኮርፖሬሽኑ በሰጠው የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የቤት ባለቤቶቹ ወደ ቤታቸው የማይገቡ ከሆነ በህግ አግባብ ውል የሚቋረጥ መሆኑን መግለጹ ይታወሳል።
ቀደም ብሎ የተሰጠው ገደብ ጥምቅት 30 የነበረ ቢሆንም ቤታቸውን አድሰው ለመግባት የጊዜ እጥረት ላጋጠማቸው የቤት ባለቤቶች ተብሎ እስከ ህዳር 30 ተራዝሞ ነበር።
ይህ ለመጨረሻ ጊዜ የተሰጠ የጊዜ ገደብ መሆኑን ኮርፖሬሽኑ ገልጾ ነበር።
ቀኑ ነገ ሰኞ ያበቃል።
በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ የማይገቡ ነዋሪዎች የሽያጭ ውላቸው የሚቋረጥ እና በቤታቸው ውስጥ ለሚፈጸም ማንኛውም ህገወጥ ድርጊት ተጠያቂ እንደሚሆኑ መግለጹ ይታወሳል።
ከዘህ ቀደም ኮርፖሬሽኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥቶት በነበረው ማብራሪያ ምን ነበር ያለው ?
- ማስታወቂያው የወጣበት ዋናው ምክንያት ሰዎች ‘ ተቸገርን፣ ክፍት በሆኑ ቤቶች ወንጀል እየተሰራ ነው፣ እየተዘረፍን ነው፣ ሴቶች እየተደፈሩብን ነው፣ የጸጥታ ስጋትም እየሆኑብን ’ ብለው ቅሬታ ስላቀረቡ እንደሆነ፤
- ቤቶቹ ቼክ ሲደረጉ እጣ የወጣባቸው ፤ ውል የተፈጸመባቸው፣ በጨረታ የተላለፉ ነገር ግን ሰው ያልገባባቸው እንደሆኑ፤
- ነዋሪው በከፍተኛ ሁኔታ እየተቸገረ ፤ የጸጥታ ኃይሉም ጥያቄ እያነሳ እንደሆነ ፤
- " የቤት ባለቤቶች ቤታችሁን አድሳችሁ ግቡ " የተባለውም የግድ እራሳቸውን እንዳይደለ ፤ ቢፈልጉ አድሶ ማከራየት መብታቸው እንደሆነ፤
- የራሳቸው ቤት እስከሆነ ድረስ አድሰው ማከራት ከፈለጉ ደግሞ እራሳቸው መግባት መብታቸው እንደሆነ ዞሮ ዞሮ ሰው በቤቱ ሊኖርበት እንደሚገባ ማብራራቱ ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia