TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
" ከእንግዲህ በሽፍትነት / rebel በመሆን መንግሥትን መጣል አይደለም ፤ መነቅነቅ አይቻልም " - ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ " ከእንግዲህ በኃላ በሽፍትነት / rebels በሚመስል ነገር መንግስትን መጣል አይደለም መነቅነቅ እንኳን አይቻልም " አሉ።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ይህን ያሉት በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ከፍተኛ እና ታማኝ ግብር ከፋይ ባለሀብቶችን ሰብሰበው በመከሩበት ወቅት ነው።

ታማኝ ከፍተኛ ግብር ከፋዮቹ ለጠ/ ሚኒስትሩ በዛ ያሉ ጥያቄዎችን ያቀረቡላቸው ሲሆን በየአካባቢው ከሚታየው ሁኔታ አንፃር #የሰላም ጉዳይ ከጥያቄዎቹ አንዱ ነበር።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ " እኛ የምንፈልገው ሰላም ነው " ብለዋል።

ሰላምን በተመለከተ ያነሷቸው ሃሳቦች ሁሉ ጥሩ እንደሆነ ገልጸው " ሽማግሌ ነን እድሜያችን ልምዳችን ያላችሁ #ሸምግሉ " ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

" እኔ የማረጋግጥላችሁ ግን በሽፍትነት / rebels በሚመስል ነገር ከእንግዲህ በኃላ የኢትዮጵያን መንግስት መጣል ሳይሆን መነቅነቅ አይቻልም። በጣም የተለያየን ነን ብቃታችን አይደለም የሚለያየው ያለን conviction ይለያያል እሱ ብር ነው የሚሰበስበው እኛ ስራ ነው የምንሰራውን እናውቃለን እያደረግን ያለነውን በቀላሉ የሚሆን አይመስለኝም " ሲሉ ተደምጠዋል።

" እነሱ ሰዎች ልብ ገዝተው ከመጡ በጣም በጣም በደስታ ነው የምንቀበለው ፤ እናተም ሞክሩ በሁሉም በምትችሉት መንገድ ሞክሩ " ብለዋል።

@tikvahethiopia