TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#Gambella : በጋምቤላ ክልል 4 ወረዳዎች የጎርፍ አደጋ ተከስቷል።

ከ16 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ከመኖሪያ ቀያቸዉ ተፈናቅለዋል።

በሀገሪቱ ደጋማ አካባቢ በጣለው ከባድ ዝናብ ፦
- በጎግ፣
- በላሬ፣
- በጆርና
- በዋንቱዋ ወረዳዎች በሚገኙ ቀበሌዎች ላይ የጎርፍ መጥለቅለቅ ተከስቶ ነው ወገኖቻችን የተፈናቀሉት።

ተፈናቃዮቹን ለጊዜዉ ደረቃማ በሆኑ አካባቢዎች እንዲሰፍሩ ተደርጓል ተብሏል።

የጎርፍ አደጋዉ በቤት ዉስጥ ባሉ ቁሳቁሶች እንዲሁም በቁም እንስሳትና በሰብል ላይም ጉዳት ማድረሱን ገልፀዋል።

የጎርፍ መጥለቅለቁ በሚቀጥሉት ጊዜያት ከዚህ የከፋ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል ተብሏል። ለዚህም ነዋሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅትና ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንዲያደርጉ የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር አሳውቋል።

#GambellaRegionPressSec.

@tikvahethiopia