TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#USA

የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን #በአየር_ንብረትና #በጤና ዙርያ የቀረቡ ረቂቅ ሕጎች ላይ ፊርማቸውን እንዳኖሩ ቢቢሲ ዘግቧል።

ባይደን በፊርማቸው ያጸኑት ሕግ በሃብታሞች ላይ ጠንከር ያለ ግብር የሚጥል ነው።

ይህ ረቂቅ ሕግ ከፍተኛ ገቢ ባላቸው ኩባንያዎች ላይ ግብር በመጣል በአየር ንብረት ለውጥና በጤና ዙርያ ለሚሠሩ ሥራዎች የሚውል ገንዘብ የሚያስገኝ እንዲሆን የተዘጋጀ ነው ተብሏል።

ጆ ባይደን ትናንት በረቂቅ ሕጉ ላይ ፊርማቸውን በማኖር ሕግ እንዲሆን አጽንተውታል።

ይህ ሕግ ከዚህ ወዲያ በጤና ዙርያ በሐኪም የሚታዘዙ መድኃኒቶች ዋጋ እንዲስተካከል የሚያደርግ ነው።

የአሜሪካ የሕዝብ ተወካዮች ለዓመታት በሚታዘዙ መድኃኒቶች ዋጋ ላይ #ቅናሽ እንዲደረግ ሲወተውቱ የቆዩትን ጥያቄ ይመልሳል ተብሏል።

ተጨማሪ : https://telegra.ph/BBC-08-17

@tikvahethiopia